TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.2K photos
1.5K videos
211 files
4.1K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#JASIRI

Application for the Jasiri Talent Investor Program Cohort 6 is now open. Jasiri calls on aspiring entrepreneurs from Kenya, Rwanda, and Ethiopia to apply.

PRESS RELEASE : https://telegra.ph/ANNOUNCEMENT-01-15-3

Join us on telegram https://t.iss.one/jasiri4ethiopia

#jasiri4africa
“ ‘ የሚቀርቡት ነገሮች ሕዝብን በመንግሥት ላይ የሚያነሳሱ ናቸው ’ ተብለን ታግደናል ” - የቲክቫህ ኢትዮጵያ ምንጭ

በደራሲ አቶ በረከት በላይነህና ተዋናይ ግሩም ዘነበ አማካኝነት ዘወትር በሳምንት ሁለት ቀናት በዓለም ሲኒማ ሲቀርብ የነበረው “ እያዩ ፈንገስ፣ ቧለቲካ ” ቴያትር ከሐሙስ ጥር 2 ቀን 2016 ዓ/ም ጀምሮ እንዳይታይ “ታገደ” መባሉን ተከትሎ ከፊሎቹ ቁጣቸውን ከፊሎቹ ደግሞ መዘጋቱ ልክ እንደሆነ በማኀበራዊ ሚዲያዎች ሀሳብ ሲለዋወጡ ተስተውለዋል።

ቲያትሩ “ ታገደ ” ከተባለ በኋላ ከፊሎቹ ‘ ሌሎች ተውኔቶችስ ያለመዘጋት ዋስትናቸው ምንድነው?’፣ ከፊሎቹ ደግሞ ማንም እየተነሳ ‘መንግሥትን መተቸት አይችልም’ የሚሉት ሀሳቦች በየፊናቸው ሲወራወሯቸው ከነበሩት መካከል ተጠቃሽ ናቸው።

አንድ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስተያየታቸውን የሰጡ ቤተሰብ፣ “ ይህ ቲያትር እኮ መሬት ላይ ያለውን እውነታ በጨዋታ እያዋዛ ቁም ነገር የሚያስጨብጥ፣ መንግሥትም ቢሆን ሊማርበት የሚገባ ነበር እንጂ መዘጋቱ ስህተት ነው ” ብለዋል።

ሌላኛው አስተያየት ሰጪ በበኩላቸው፣ “ መንግሥትን በተዘዋዋሪ ከመተቸት በቀጥታ መንገር ይቻላል፣ ይህ የመንግሥትና የሕዝብን ግንኙነት ሲያሻክር የኖረ ቲያትር ነው ” ሲሉ ተናግረዋል።

ቲያትሩ ከመታገዱ ከአንድ ቀን በፊት በ “ እያዩ ፈንገስ፣ ቧለቲካ ” የማኀበራዊ ትስስር ገጽ እንደተገለጸው ከሆነ፣ ቲያትሩ እንዳይታይ የተከለከለው፣ “ የመንግሥት የጸጥታ አካላት ለዓለም ሲኒማ የሥራ ኃላፊዎች ባስተላለፉት ትእዛዝ ” መሠረት ነው።

በገለጻው መሠረት፣ “ ቴአትር ቤቱም ይህንኑ የመንግሥት የጸጥታ ኃላፊዎች ትእዛዝ ለቴያትሩ አዘጋጆቹ በማሳወቅ ውሉን ማቋረጡን ገልጿል። ” ተብሏል።

ይህንኑ መረጃ መሠረት በማድረግ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከዓለም ሲኒማ ማብራሪያ ለማግኘት ባደረገው ማጣራት፣ “ የሚቀርቡት ነገሮች ሕዝብን በመንግሥት ላይ የሚያነሳሱ ናቸው ተብለን ታግደናል ” የሚል ምላሽ ከአንድ ምንጭ ሰምቷል።

የቲክቫህ ኢትዮጵያ ምንጭ፣ ቲያትሩ መታዬት እንዳቆመ፣ ይህ የሆነው በቃል በተሰጣቸው ትዕዛዝ እንደሆነ፣ ሙሉውን መረጃ ደግሞ አቅራቢውንና ደራሲውን መጠየቅ እንደሚገባ ከመግለጽ ባለፈ ካላቸው ስጋት አንጻር ተጨማሪ ማብራሪያ ከመስጠት ተቆጥበዋል።

በተጨማሪም አቅራቢውና ደራሲው በጉዳዩ ዙሪያ ምን ምላሽ እንዳላቸለው ቲክቫህ ኢትዮጵያ ያደረገው ሙከራ አልተሳካም።

“ እያዩ ፈንገስ ” በመጋቢት ወር 2006 ዓ/ም መታየት እንደጀመረ፣ በዚህም በ “ እያዩ ፈንገስ ” ቁጥር 1 “ ፌስታሌን ”፣ ቁጥር 2 “ አጀንዳዬን ” ተውኔቶች እንደታዩበት፣ ከዚያ በኋላ ደግሞ ከጥቅምት 15/2016 ዓ/ም ጀምሮ ደግሞ “ እያዩያዩ ፈንገስ ” ቁጥር 3 “ ቧለቲካ ” በየሳምንቱ ሀሙስና እሁድ ለሕዝብ እይታ ሲቀርብ ነበር።

ዘገባውን የላከው የአ/አ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ነው።

@tikvahethiopia
#ቻይና

ኢትዮጵያ ለአንድ ቻይና ፖሊሲ አሁንም አቋሟ ያልተቀየረና የፀና መሆኑን አሳውቃለች።

የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር መለስ ዓለም (ዶ/ር) ለኢዜአ በሰጡት ቃል ፤ ኢትዮጵያ የአንድ ቻይና ፖሊሲ ላይ ያላት አቋም ዛሬም የጸና ነው ብለዋል።

ኢትዮጵያ የአንዲት ቻይና ፖሊሲን ለረጅም ዓመታት ስታራምድ መቆየቷን አስታውሰው ይህ አቋሟ በዘመናት መካከል መንግስታት አፅንተው የያዙት መሆኑን ገልጸዋል።

በመሆኑም ኢትዮጵያ የአንድ ቻይና ፖሊሲ ላይ ያላት አቋም ዛሬም የጸና መሆኑን አረጋግጠዋል።

በሌላ በኩል ፤ ከሰሞኑን ራሷን ከቻይና ነጥላ እንደ ነፃ ሀገር በምትቆጥረው ታይዋን ፕሬዜዳንታዊ ምርጫ ተደርጎ ነበር።

በዚህ ምርጫ ቻይና አትወዳቸውም የሚባሉት፣ አስቸጋሪና አደገኛ ሰው ብላቸው የምትጠራቸው በሙያቸው ሐኪም የሆኑት ዊሊያም ላይ ማሸነፋቸው ተዘግቧል።

ዶክተሩ " ለቻይና አንንበረከክም !! " በሚል አቋማቸው ነው የሚታወቁት።

ቻይና ከምርጫው በፊት አምርራ ለምትጠላው ለገዢው ዲሞክራቲክ ፕሮግረሲቭ ፓርቲ (ዲፒፒ) ህዝቡ ድምጽ እንዳይሰጡ አሳስባ የነበረ ቢሆንም የዚሁ ፓርቲ አባል የሆኑት የሕክምና ዶክተሩ ዊሊያም ላይ ቺንግ አሸንፈዋል።

ሰውየው በምርጫ ቅስቀሳ ወቅት " ታይዋን ነጻ አገር መሆኗን ማወጅ አያስፈልጋትም፣ ምክንያቱም ታይዋን ሉአላዊና ነጻ አገር ስለሆነች " ብለዋል።

ይህንን ምርጫ ተከትሎ ሀገራት አቋማቸውን እና አስተያየታቸውን ሲሰጡ ነበር።

አሜሪካ በምርጫው ላሸነፉት ፕሬዜዳንት በይፋ የ" እንኳን ደስ አልዎት " መልዕክት አስተላልፋ ፤ ከታይዋን እና ከገዢው ፓርቲ ጋር ያላትን ግንኙነት እንደምታጠናክር አሳውቃለች።

ከምርጫው በኃላ ፕሬዜዳንት ጆ ባይደን ፤ " እኛ ነፃነትን አንደግፍም ... " የሚል አስተያየት ሰጥተው ነበር።

አሜሪካ ከታይዋን ጋር ይፋዊ ያልሆኑ ግንኙነቶች ያሏት ሲሆን ታዋይም የአሜሪካ ድጋፍ እንዳላት በተለያየ ጊዜ ተናግራለች ፤ የአሁኑን ምርጫም ተከትሎ የቀድሞ ብሄራዊ ደህንነት አማካሪ ስቴፋን ሃድሌይ ጭምር ያሉበት ይፋዊ ያልሆነ ልዑክ ወደ ታይዋን ልካ ከአሁኑ ተመራጭ ፕሬዜዳንት እና ከቀድሞ ጋር ውይይት አድርጋለች።

ከአሜሪካ በተጨማሪ፣ ዩናይትድ ኪንግደም፣ የአውሮፓ ህብረት፣ እንዲሁም ካናዳ ፣ ጃፓን ለገዢው ፓርቲ ደስታ መልዕክት አስተለልፈዋል።

በሌላ በኩል፤ ሩስያ ምርጫውን ተከትሎ ታይዋን የቻይና አንድ አካል መሆኗን ገልጻለች። ኢራን ፣ ኢንዶኔዥያ፣ ቬትናም ፣ታጃኪስታን " የአንድ ቻይና " ፖሊሲን እንደምትደግፍ አረጋግጣለች።

ከአፍሪካ ደግሞ የኢትዮጵያ ጎረቤት ሶማሊያ ለአንድ ቻይና ፖሊሲ ድጋፍ በማሳየት ፤ ታይዋን የቻይና ግዛት ናት ስትል መግለጫ አውጥታለች። ከቀናት በፊት ቻይና " ሶማሌላንድ የሶማሊያ ግዛት ናት " ማለቷ ይታወሳል።

ኢትዮጵያ ስለምርጫው ምንም ባትልም አሁንም " የአንድ ቻይና " ፖሊሲዋ እንዳልተቀየረ አሳውቃለች።

ቻይና ታይዋንን " የራሷ ግዛት አድርጋ ነው የምታስባት፤ #ወደ_እናት_ሀገሯ መመለስ አለባትም ብላ ታምናለች ለዚህም ታይዋንን የሚደግፉ ሁሉ በሀገር አንድነት ላይ አደጋ ያመጡ አድርጋ ነው የምትወስዳቸው።

@tikvahethiopia
#አቢሲንያ_ባንክ

ለጥያቄና መልስ ውድድራችን ዝግጁ ነዎት?
7ኛ ዙር የጥያቄና መልስ ውድድር ሐሙስ ጥር 9 ከቀኑ 6:30 በቴሌግራም ቻናላችን ይደረጋል፡፡ ቀላል ጥያቄዎች በመመለስ ይሳተፉ፤ ይሸለሙ፡፡ በየሳምንቱ አምስት አምስት አሸናፊዎች ይሸለማሉ! ዛሬውኑ የቴሌግራም ቻናላችንን በመቀላቀል ይሸለሙ!

የቴሌግራም ሊንክ https://t.iss.one/BoAEth

#telegram #giveaway #contest #Boa #bankinginethiopia #banksinethiopia #bankofabyssinia #Ethiopia #የሁሉም_ምርጫ
" በር ዘግተው መፈተሽ ጀመሩ የተወሰነውን ሰው እቃውን ወሰዱ የተወሰነውን መታወቂያውን ኮፒ አደረጉ። ፖሊሶች ናቸው " - የባህል ልብስ ነጋዴ

" ለእኔ መረጃው አዲስ ነው፣ ..ከታወቀ በኋላ ቦታው ላይ ይደወላል" - ፓሊስ

ሽሮ ሜዳ የሚገኙ አንዲት የልብስ ነጋዴ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል፣ " አራት ሆነው መጥተው በሩን ዘጉት። በአንድ በኩል ብቻ በመሰላል መውጣት መግባት ይቻላል። ሌላውን በር ዘግተው መፈተሽ ጀመሩ የተወሰነውን ሰው እቃውን ወሰዱ የተወሰነውን መታወቂያውን ኮፒ አደረጉ " ብለዋል።

ፍተሻ ያደረጉት ሽሮ ሜዳ በሚገኘው የባህል ልበስ መሸጫ የሚገኙ ከ280 በላይ ሱቆችን ዘግተው እንደሆነ፣ ከዚህ ውስጥ ከ10 በላይ የሚሆኑ ነጋዴዎችን እቃ፣ መታወቂያ ኮፒ አድርገው እንደወሰዱ ገልጸዋል።

እንዲህ ያደረጉት እነማን ናቸው ? ተብሎ ለቀረበላቸው ጥያቄ፣ " ፓሊሶች ናቸው " የሚል ምላሽ ሰጥተው፣ " የኢትዮጵያ ባንዲራ እንሸጣለን። ባንዲራውን የምንሸጠው ለብቻው ሳይሆን ልብሱ ላይ ባንዲራ (ቲሸርቶች ላይ፣ የሀገር ባህል ልብስ ላይ) ነው " ሲሉ አስረድተዋል።

የፓሊስ አባላቶች ምን እንድታደርጉ ነው የፈለጉት ? አታድርጉ የተባላችሁት ጉዳይ አለ ? ተብለው ሲጠየቁም፣ " ሥራውን አቁሙ አይሉም። ፍተሻ ይፈትሻሉ 'ባንዲራ አለወይ' ይላሉ ዞርዞር ብለው ያያሉ ያገኙባቸውን ሰዎች 'ምንድን ነው?' ይላሉ ነጋዴዎቹ ደግሞ 'የባንዲራ ልብስ ነው' ይላሉ። ከዚያ መታወቂያ ኮፒ ያደርጋሉ መታወቂያ፣ ስልክ ቁጥር ተቀብለው መዝግበው ይሄዳሉ " ብለዋል። 

ሌላኛዋ ቅሬታ አቅራቢ በበኩላቸው፣ " የባንዲራ ኅትመት ቲሸርት፣ የባህል ልብስ መሸጥ የጀመርነው ዛሬ አይደለም። ወይ አትሽጡ ብለው ማስጠንቀቂያ አልሰጡም፣ ሲጀመር መሸጣችንም ወንጀል አይደለም። ነገር ግን በፍተሻ ሰበብ ልብስ እየተወሰደብን ነው " ሲሉ አማረዋል።

የመጀመሪያዋ ቅሬታ አቅራቢ በበኩላቸው፣ "በህግ ላይ ያላቸው ግንዛቤ ምድነው? ህዝብ የሚያስተዳድሩት በህግ ነው ሌላ ምንም ሊሆን አይችልም አይደል? ህዝብን ማስተዳደር የሚችለው አካል ግን ምንድነው እንዲህ ብጭርቅ ያለ ሀሳብ?" ሲሉ ጠይቀዋል።

አክለውም፣ "እንዲህ አይነት ነገር ሲደረግ ቅድመ ማስጠቀቂያ አይኖረውም ወይ? ኖርማሊ ባንዲራ መሸጥ በምን ዓይነት ህግ ነው ሰውን ሊያስጠይቅ የሚችለው?" የሚል ጥያቄ አንስተዋል።

ነጋዴዎቹ፣ "ሌጋሊ የሆነ አሰራር ከሆነ እኛም ከመንግሥት ጋር እሰጣ አገባ አንፈልግምም፤ እንዲህ አይነት ነገር ሲደረግ ቅድመ ማስጠቀቂያ አይኖረውም? ግን የባህል ልብስ ላይ አድርጎ ባንድራ መሸጥ በምን ዓይነት ህግ ነው ሰውን ሊያስጠይቅ የሚችለው?" ሲሉ ጠይቀው፣ የአዲስ አበባ ፓሊስ መፍትሄ እንዲሰጣቸው አሳስበዋል።

ለተነሳው ቅሬታ ምን ምላሽ እንዳላቸው ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ጥያቄ የቀረበላቸው የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የሕዝብ ግንኙነት ምክትል ኮማንደር ማርቆስ ታደሰ፣ "ለእኔ መረጃው አዲስ ነው" የሚል አጭር ምላሽ ሰጥተዋል።

አክለውም፣ "የአዲስ አበባ ፓሊስ ነው? የፌደራል ነው? ወይስ ከሌላ ቦታ የመጣ ፓሊስ ነው? የሚለው ከታወቀ በኋላ ቦታው ላይ ይደወላል” ብለዋል።

ቅሬታ አቅራቢዎቹ በበኩላቸው እንዲህ የሚያደርጉት በወረዳው የሚገኙ የአዲስ አበባ ፓሊስ ኮሚሽን አባላት መሆናቸውን አስረድተዋል።

ዘገባውን የላከው የአ/አ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ነው።

ፎቶ ፦ ፋይል

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#EOTC " ሀገራችን ሰላም ትሁን፤ የሃይማኖት ሰዎች እንደ ሃይማኖት እናስብ፣ እንደ ሃይማኖት እንናገር፣ አላስፈላጊ ጀግንነትን እንርሳው " - ብፁዕነታቸው ብፁዕ አቡነ አብርሃም የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ ምን አሉ ? - የማይደፈር ሲደፈር አይተናል፤ ቤተክርስቲያን ስትደፈር ዝም አንልም። - " ፖለቲካው የፖለቲካው መስመር ሲደፈር ዝም እንደማይል ሁሉ እኔም ደግሞ የመጀመሪያዋም የመጨረሻዋም…
#ጥምቀት

" በተለያዩ ማኅበራዊ ሚዲያዎች እየተላለፈ ያለውን የበዓል አከባበር ክልከላን የሚገልጹ የሐሰት ዜናዎች ቤተክርስቲያንን አይወክሉም " - ብፁዕ አቡነ አብርሃም

በዓለ ጥምቀትን አስመልክቶ የሚተላለፉ መልእክቶች የቤተክርስቲያንን አስተምህሮ ላይ ብቻ ያተኮሩ እንዲሆኑ ብፁዕ አቡነ አብርሃም የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የባህር ዳርና የሰሜን ጎጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ መመሪያ አስተላልፈዋል።

ብፁዕነታቸው በተለያዩ ቋንቋዎች ለተለያዩ የቴሌቪዥን ጣቢያዎች ቃለ መጠይቅና ምላሽ እንዲሰጡ ለተመረጡ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን በሰጡት አባታዊ መመሪያ የቅድስት ቤተክርስቲያን መልእክት የሚተላለፈው በማእከል በመሆኑ የማእከሉን መልእክት ብቻ እንዲያስተላልፉ መመሪያ የሰጡ ሲሆን ከግል አስተያየት መቆጠብ እንደሚገባም አበክረው አሳስበዋል።

ቤተክርስቲያኗ የሰላም ሰባኪ እንደመሆኗ መጠን የቤተክርስቲያን መልእክት ሲተላለፍ ሰላም ላይ ማተኮርና በዓል ለማክበር የሚወጡ ምእመናን በዓሉ በሰላም አክብረው እንዲመለሱ መልእክት ማስተላለፍ እንደሚገባ ግልጽ መመሪያ ሰጥተዋል።

ሀገራችን ኢትዮጵያዊ ሁሉም ሃይማኖቶች ተከባብረው የሚኖሩባት ሀገር መሆኗ ከሚገለጽባቸው መንገዶች አንዱ ይህ በዓል የሚከበርባቸውን ቦታዎች ለማጽዳትና ሥርዓት ለማስከበር ጥረት እያደረጉ ያሉ የሌሎች ሃይማኖት አባላትን በአባትነት ያመሰገኑት ብፁዕነታቸው ታቦታቱ በሚያልፉባቸው መንገዶች የሚገኙ የሌሎች ቤተ እምነቶችን ማክበር እንደሚገባ ለሁሉም ካህናትና ምእመናን አባታዊ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።

በተለያዩ ማኅበራዊ ሚዲያዎች እየተላለፈ ያለውን የበዓል አከባበር ክልከላን የሚገልጹ የሐሰት ዜናዎች ቤተክርስቲያንን የማይወክሉና ቤተክርስቲያናችን በዓሉን በሰላም ለማክበር ከሚመለከታቸው የመንግሥት አካላት ጋር እያደረገች ያለውን ጥረት ከግንዛቤ ያላስገባ መሆኑን ብፁዕነታቸው አሳውቀዋል።

#EOTCTV

@tikvahethiopia
#MoE

ከ2015 የትምህርት ዘመን ጀምሮ በሁሉም በቅድመ ምረቃ ፕሮግራሞች ለእጩ ተመራቂ ተማሪዎች የከፍተኛ ትምህርት የመውጫ ፈተና እየተሰጠ መሆኑ ይታወቃል፡፡

ትምህርት ሚኒስቴር በ2016 ዓ.ም #አጋማሽ ላይ የመውጫ ፈተናን ለመፈተን በመጠባበቅ ላይ ላሉ ተፈታኞች በሙሉ ፈተናው ከጥር 27- የካቲት 1/2016 ዓ.ም የሚሰጥ ይሆናል ብሏል።

በሐምሌ ወር 2015 ዓ.ም የመውጫ ፈተናውን ተፈትነው ያላለፉ እና ከጥር 27 - የካቲት 1/ 2016 ዓ.ም ድረስ የመውጫ ፈተናውን በድጋሚ (Re-exam) ለመውሰድ በመጠባበቅ ላይ ያሉ ተፈታኞች በሙሉ ምዝገባ የሚያካሂዱት የመፈተኛ ተቋም (የመንግስት ዩኒቨርሲቲ) የሚመርጡት በዚህ ማስፈንጠሪያ (Link)
(https://exam.ethernet.edu.et)  ነው።

ስለሆነ ከጥር 08 እስከ ጥር 15 ቀን 2016 ዓ.ም ድረስ የምዝገባ ክፍያ 500.00 ብር በ " ቴሌ ብር " ብቻ በመክፈል መመዝገብ እንደሚችሉ ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል።

አመልካቾች ተጨማሪ ድጋፍ የሚፈልጉ ከሆነ በስልክ ቁጥር +251 118 13 21 76 ወይም በኢሜይል [email protected] በኩል ድጋፍ ማግኘት የሚችሉ መሆኑ ተገልጿል።

ትምህርት ሚኒስቴር ፤ ለመጀመሪያ ጊዜ የመዉጫ ፈተና የሚፈቱ እጩ ተመራቂዎች ምዝገባ የሚያካሂዱትና  እና የአገልግሎት ክፍያ የሚፈፅሙት በተቋማቸው በኩል መሆኑን ገልጾ አስፈላጊው የመፈተኛ መረጃዎች በተቋማቸው በኩል እንደሚደርሳቸው አመልክቷል።

@tikvahethiopia
Forwarded from Ethio telecom
ባህር ማዶ ካለ ወዳጅ ዘመድ የሞባይል ጥቅል ሲላክልዎ እስከ 20% ቅናሽ ማድረጋችንን በደስታ እንገልጻለን !

እነዚህን ከመደበኛ ጥቅል እስከ 20 % ቅናሽ የተደረገባቸውን ጥቅሎች ሲሞሉልዎ እስከ 100 % የሚደርስ ተጨማሪ ስጦታ ይበረከትልዎታል!

#Ethiotelecom #telebirr #RealizingDigitalEthiopia
#ተመስገን_ደሳለኝ

ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ዛሬ ጥር 7 ቀን 2016 ዓ/ም ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰሚ ችሎት በቀረቡበት ወቅት፣ “ትክክለኛ ፍትህ ይሰጣሉ ብዬ ስለማላምን” ያሏቸውን የጠቅላይ ፍርድ ቤት ዳኛ ከችሎት እንዲነሱ ጠይቀዋል።

ጋዜጠኛው ይህን ጥያቄ ያቀረቡት ዛሬ ቀጠሮ ተሰጥቶበት የነበረው ጉዳያቸው ከመታየቱ በፊት የሚያቀርቡት አቤቱታ እንዳላቸው ለዕለቱ ዳኞች ጥያቄ በማቅረብ ነው።

ስለሚያቀርቡት አቤቱታ ችሎቱ ለጋዜጠኛ ተመስገን አቤቱታቸውን እንዲገልጹ ከፈቀደላቸው በኋላ፣ “የግራ ዳኛ የሆኑት ክቡር አቶ አሕመድ መሐመድ ትክክለኛ ፍትህ ይሰጣሉ ብዬ ስለማላምን በዚህ ጉዳይ ከችሎት እንዲነሱልኝ ምክንቻቶቼን አቀርባለሁ” ሲሉ ተደምጠዋል።

ጋዜጠኛ ተመስገን ይህን ከገለጹ በኋላ የቀኝና የመሀል ዳኛ የለሆሳስ ንግግር አድርገው አቤቱታቸውን በፅሑፍ እንዲያቀርቡ ማሳሰቢያ የሰጡ ሲሆን፣ ጋዜጠኛ ተመስገንም ፈቃድ ካገኙ በኋላ፣ “በእዚህ ችሎት በርካታ ጋዜጠኞች ስላሉ አቤቱታዬን በንባብ እንዳሰማ ሊፈቀድልኝ ይገባል” ብለውሸ ሲገልጹ፣ ፅሑፉን ባጭሩ እንዲያቀርቡ ማሳሰቢያ ተሰጥተዋል።

አሳጥረው እንዲያቀርቡ ዳኞች በፈቀዱላቸው መሠረት ያነበቡት ፅሑፉ በዝርዝር ምን ይላል?

“ዐቃቤ ሕግ ጥቅምት 1/2015 ዓ.ም ባቀረበው የይግባኝ ቅሬታ 2ኛ ክስን በሚመለከት 3ኛ እና 4ኛ ፍሬ ነገሮች፤ እንዲሁም 3ኛ ክስን የይግባኝ ቅሬታ ያላቀረበበት መሆኑን ጠቅሶ ወደፊት፦ ፍርድ ከተሰጠ በኋላ ውጤቱን ተመልክቶ የይግባኝ ቅሬታ እንደሚያቀርብበት በይግባኝ ማመልከቻው ላይ በግልጽ አመላክቶ እያለ፣ 

* ታህሳስ 17/2015 ዓ/ም መልስ ሰጪን ያስቀርባል በሚል ትዕዛዝ ከሰጡት ዳኞች መካከል አቶ መሐመድ አሕመድ የሚገኙበት መሆኑን አረጋግጫለሁ፡፡በችሎቱ የተሰጠው ትዕዛዝም ዐቃቤ ሕግ በ2ኛ ክስ ቅሬታ ያላቀረበባቸውን 3ኛ እና 4ኛ ፍሬ ነገሮችን በመጨመር፤ 

* እንዲሁም 3ኛ ክስን በማካተት በ1ኛ እና 2ኛ ክሶች መከላከል ሳያስፈልገው በነፃ እንዲሰናበት፣ 3ኛ ክስን በሚመለከት ክስ የቀረበበት ድንጋጌ ወደ ጥላቻ ንግግር ወይም የሀሰተኛ መረጃ ስርጭትን ለመከለከል እና ለመቆጣጠር የወጣውን አዋጅ ቁጥር 1185/2012 አንቀጽ 4 በመለወጥ እንዲከላከል በአብላጫ ድምጽ የተሰጠውን ብይን፤ 

*እንዲሁም የተጠቀሰውን አዋጅ ለጉዳዩ ያለውን አግባብነት መጣራት ያለበት መሆኑን ስለታመነበት መልስ ሰጪ ይቅረብ ብለናል በሚል ትዕዛዝ ተሰጥቷል፡፡” የሚል ነው።

ጋዜጠኛ ተመስገን ያነበቡትና ቲክቫህ ኢትዮጵያ የተመለከተው ይኼው ሰነድ አክሎም፣ “ይህ ትዕዛዝ ዐቃቢ ህግ በይግባኝ አቤቱታው ከጠየቀው ዳኝነት በማለፍ የተሰጠ ትዕዛዝ መሆኑን መረዳት የሚቻል ከመሆኑም በላይ የመልስ ሰጪን መብት በብርቱ የሚጎዳ አድራጎት ነው” ይላል።

በተጨማሪ ፣ “ከላይ ስማቸውን የጠቀስኩት ዳኛ በዚህ ጉዳይ ከችሎት ሳይነሱ ይቀጥሉ ቢባል ጉዳዩ ፓለቲካዊ ይዘት ያለው እንደመሆኑ መጠን በመዝገቡ ላይ ትክክለኛ ፍትህ ይሰጣሉ ብዬ የማላምንና ወደ ፊትም የሚሰጠው ፍርድ ነጻና ገለልተኛ ይሆናል ብዬ ስለማላምን በአዋጅ ቁጥር 1234/2013 አንቀጽ 33/1/ሠ መሠረት የግራ ዳኛ የሆኑት ክቡር አቶ መሐመድ አሕመድ በዚህ ጉዳይ ከችሎቱ እንዲነሱልኝ በታላቅ ትህትና እጠይቃለሁ” ሲል ያትታል።

በመጨረሻም፣ የጋዜጠኛውን አቤቱታ ካደመጠ በኋላ ችሎቱ፣ የዳኛውን ከችሎት መነሳትና አለመነሳት ጥያቄን በተመለከተ ለመወሰን፣ እንዲሁም ጋዜጠኛ ተመስገን በዋናው ክሳቸው ይሰጣሉ ተብሎ የሚጠበቀውን መለስ ለመቀበል ለጥር 28 ቀን 2016 ዓ/ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡

ዘገባውን የላከው የአ/አ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ኢዮብ ትኩዬ ነው።

@tikvahethiopia
#እንድታውቁት  #ነዳጅ

የህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ስጪ በሆኑ ተሽከርካሪዎች ላይ የነዳጅ ድጎማ መጠን ላይ በተደርገ ማሻሻያ ቀደም ሲል ሲሰጥ ከነበረው የድጎማ መጠን ዝቅ አንዲል መደረጉን የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታውቋል።

የነዳጅ ድጎማ መጠን ላይ ማሻሻያ የተደረገው ፦
- በአገር አቋራጭ አውቶብሶች ፣
- የከተማ አውቶብሶች
- ፐብሊክ ባስ
- ሚዲባስ፣ ሚኒባስ፣ ታክሲዎችና ባለሶስት እግር ተሽከርካሪዎች ላይ መሆኑን ሚኒስቴሩ አሳውቋል።

በየ6 ወሩ የነዳጅ ድጎማ ተጠቃሚ ተሽከርካሪዎች የድጎማ መጠን ማስተካከያ የሚደረግ ሲሆን ከጥር 1 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ሰኔ 30 ቀን 2016ዓ.ም ለሚቀጥሉት 6 ወራት ፦

* ለቤንዚን ተጠቃሚ አገር አቋራጭ አውቶብሶች ፣የከተማ አውቶብሶች እና ፐብሊክ ባስ ብር 22.36 በሊትር ሲሰጥ የነበረውን ድጎማ ወደ 19.16 በሊትር ዝቅ እንዲል፣

* ለነጭ ናፍጣና ለኬሮሲን ሲሰጥ የነበረው ብር 23.21 በሊትር ድጎማ በሊትር 19.89 ዝቅ እንዲል ተደርጓል፡፡

የታለመ ድጎማ ተጠቃሚ የሆኑ ሚዲባስ፣ ሚኒባስ፣ ታክሲዎችና ባለሶስት እግር የሚሰጠው ድጎማ በየሶስት ወሩ የሚከለስ መሆኑ ተመላክቷል፡፡

በዚህም ፦

* ከጥር 1 ቀን 2016ዓ.ም እስከ መጋቢት 30 ቀን 2016ዓ.ም ድረስ ለቤንዚን ተጠቃሚዎች ሲስጥ የነበረው ብር 12.78 በሊትር ድጎማ ወደ 6.39 በሊትር፣

* ለነጭ ናፍጣና ለኬሮሲን ሲስጥ የበነረው የብር 13.27 ድጎማ ወደ ብር 6.63 በሊትር ተቀናሽ እንዲሆን የተወሰነ መሆኑ ተገልጿል፡፡

መረጃው የንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር / ኤፍ ቢ ሲ ነው።

@tikvahethiopia
ፎቶ ፦ #ኢትዮጵያ የአየር ክልሏን ከማንኛውም ጥቃት ሊከላከሉ የሚችሉ ዘመናዊ የውጊያ ትጥቆችን እየታጠቀች መሆኑና ይህም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የኢትዮጵያ የሀገር መከላከያ ሰራዊት አሳውቋል።

የኢትዮጵያ አየር ሀይል ዛሬ እጅግ ዘመናዊ የሆነውን የsu-30 ተዋጊ ጀቶችንና የስትራቴጂክ ሰው አልባ ተዋጊ አውሮፕላኖችን በመረከብ መታጠቁን ገልጿል።

ይህ የመጀመሪያ ዙር ሲሆን ሌሎች በሂደት እንደሚገቡ ተነግሯል።

ዛሬ የአየር ኃይሉ የታጠቃቸው የsu-30 እና የስትራቴጂክ ሰው አልባ አውሮፕሎች እጅግ ዘመናዊ፣ የ5ኛው ትውልድ አካል የሆኑ በሀገር ላይ ሊቃጡ የሚሞከሩ ጥቃቶችን ለማክሸፍ ወሳኝ የሆኑ ናቸው ተብሏል።

@tikvahethiopia