TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.8K photos
1.61K videos
216 files
4.36K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#NationalBankofEthiopia የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በዛሬው ዕለት የባንክ ስራን ለመቆጣጠር የሚያስችሉ 5 መመሪያዎችን እንዳሻሻለ አሳውቋል። እነዚህ መመሪያዎች በሁለት ዋና ዋና ክፍሎች የተመደቡ ናቸው። በመጀመሪያው ምድብ የሚካተቱት ፦ - “ የብድር ተጋላጭነት ጣሪያ ስለመወሰን”፤ - “ከባንኩ ጋር ዝምድና/ግንኙነት ባላቸው ወገኖች አማካኝነት ስለሚኖር የብድር ተጋላጭነት” - “ስለንብረት…
#NBE #Ethiopia

የብሔራዊ ባንክ የሕግ ማሻሻያ ፦

ከባንክ ጋር #ተዛማጅነት_ላላቸው_አካላት የሚሰጥ የብድር ተጋላጭነት ገደብ መመሪያ ላይ የሕግ ማሻሻያ ተደርጓል።

የዚህ መመሪያ ዓላማ አንድ ባንክ ተዛማጅነት ካላቸው አካላት ጋር በሚያደርገው ግንኑነት ብድር አግባብነት በሌለው መንገድ እንዳይሰጥ ለማድረግ ፣ የጥቅም ግጭት ለመቀነስ እንዲሁም ደግሞ ተዛማጅነት ካላቸው አካላት ጋር ባንኮች የሚያደርጉትን ማንኛውም ግብይት በተመለከተ በቂ የሆነ ክትትል ለማድረግ እና ያለ አድልዎ በተገቢው መንገድ የተሰጠ መሆኑን ለማረጋገጥ ነው።

ይህ መመሪያ በዋነኛነት ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን #ገደቦች_ጥሏል

ሀ) በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ከባንክ ጋር ተዛማጅነት ላላቸው አካላት በማንኛውም ጊዜ የሚኖረው አጠቃላይ የብድር ተጋላጭነት ከባንኩ ጠቅላላ ከፒታል ከ15% እንዳይበልጥ፤

ለ) በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ከባንክ ጋር ተዛማጅነት ላላቸው አካላት በሙሉ በማንኛውም ጊዜ የሚኖር አጠቃላይ የብድር ተጋላጭነት ከባንክ ጠቅላላ ካፒታል ከ35% እንዳይበልጥ፤

ሐ) አንድ ባንክ ተዛማጅ ከሆኑ ወገኖች ጋር ግብይት ሲፈጽም ከማናቸውም ተዛማጅ ካልሆኑ ወገኖች ጋር ግብይት ሲፈጽም ተግባራዊ በሚደረግ ሁኔታዎች ጋር ተመሳሳይ በሆነ መልክ እንዲሆን እና ከዚህ በተለየ ሁኔታ እንዳይፈጸም ይደነግጋል።

https://t.iss.one/tikvahethiopia/88218?single

#የኢትዮጵያ_ብሔራዊ_ባንክ

@tikvahethiopia
161🙏34🥰22🤔21🕊15😱14😡10😢6😭5