TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.2K photos
1.5K videos
211 files
4.1K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
" ለጉምሩክ ሰራተኞች ' ጉቦ ሰጥቼ መኪኖችህን አስለቅቃለሁ ' በሚል 1 ሚሊዮን ብር ቼክ ሲቀበል የነበረ ትራንዚተር እጅ ከፍንጅ ተይዟል " - ፌዴራል ፖሊስ

" ጉቦ ሰጥቼ መኪኖችህን አስለቅቅልሃለሁ " ብሎ ከባለ ጉዳይ የ1 ሚሊየን ብር ቼክ ሲቀበል የነበረ አንድ ትራንዚተር እጅ ከፍንጅ ተይዞ በቁጥጥር ሥር መዋሉን የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ።

" ጉቦ ሰጥቼ መኪኖችህን አስለቅቅልሃለሁ " ብሎ ከባለ ጉዳይ የ1 ሚሊየን ብር ቼክ ሲቀበል የነበረ አንድ #አስተላላፊ (ትራንዚተር) ህዳር 30 ቀን 2016 ዓ.ም ከነ-ኤግዚቢቱ በአዲስ አበበ ከተማ አቃቂ ቃልቲ ክፍለ ከተማ እጅ ከፍንጅ ተይዞ በቁጥጥር ሥር ውሎ ምርመራ እየተጣራበት እንደሚገኝ ተገልጿል።

ትራንዚተሩ የተያዘው " #ለጉምሩከ_ሠራተኞች ጉቦ ሰጥቼ በኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን የተያዙ መኪኖችህን አስለቅቅልሃለሁ " በማለት ጉቦ እንደሚሰጥ አስመስሎና አታሎ ከባለጉዳይ የ1 ሚልየን ብር ቼክ ሲቀበል የኢትዮጵያ ፌዳራል ፓሊስ ወንጃል ምርመራ ከኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን አባላት ጋር በመሆን ባደረጉት ክትትል እጅ ከፈንጅ ከነ-ቼኩ ተይዘው በቁጥጥር ሥር ሊውሉ ችለዋል።

ኅብረተሰቡ በመሠል ግለሰቦች እንዳይታለል ጥንቃቄ እንዲያደርግና በዚህ ተግባር ላይ የተሰማሩ ግለሰቦችና ቡድኖችንም ሲያገኝ ጥቆማ እንዲሰጥ የኢትዮጽያ ፌደራል ፖሊስ ጥሪ አቅርቧል።

@tikvahethiopia