#ኢንጪኒ
በኦሮሚያ ክልል ፤ በምዕራብ ሸዋ ዞን ፤ አደኣ በርጋ ወረዳ በተፈጸመ ጥቃት የኢንጪኒ ከተማ ባለሥልጣን እና የጸጥታ አስከባሪዎችን ጨምሮ ቁጥራቸው በውል የማይታወቅ ሰዎች መገደላቸውን ነዋሪዎችን ዋቢ አድርጎ ዶቼ ቨለ ሬድዮ ዘግቧል።
የከተማው ነዋሪዎች ምን አሉ ?
ስማቸው ለደህንነታቸው ሲባል እንዲገለፅ ያልፈለጉ ነዋሪ ፦
* የሰባት ሰዎች አስከሬን ዛሬ ጠዋት ተገኝቷል።
* ማረሚያ ቤት ተሰብሮ እስረኞች ተለቀዋል።
* ህዳር 28 ቀን ለ29 ቀን 2016 ዓ.ም. አጥቢያ ከሌሊቱ ስድስት ሰኣት ጀምሮ ነው ጥቃት የተፈፀመው።
* የወረዳው ማረሚያ ቤት ተሰብሮ በመቶዎች የሚቆጠሩ እስረኞች ተለቀዋል።
* በታጣቂዎቹ ጥቃት የከተማዋ አስተዳዳሪን (ብርሃኑ ሃብትዬ) ጨምሮ የሰዎች ህይወት አልፏል።
* በተለያዩ ጥበቃ ስራ የሚሰሩ እንዲሁም በማረሚያ ቤት ጥበቃ ላይ ነበሩ የተባሉ ፖሊሶችም መገደላቸውን ሰምተናል።
* ዛሬ ጠዋት ህዝቡ ከጸጥታ ሃይሎች ጋር ወጥቶ አስክረ ሲሰበሰብ ነበር። ቢያንስ ወደ ሰባት አስከሬን ተገኝተዋል፡፡ የተጎዱትም ወደ ሆስፒታል ተወስደዋል፡፡
* በግምት ከእኩለ ሌሊት ስድስት ሰዓት ጀምሮ እስከ ሰባት ሰዓት ሰምተን የማናውቅ አይነት የተኩስ እሩምታ ነው ስንሰማ ያደርነው።
ሌላኛው ነዋሪ ፦
- በወረዳው የፖሊስ ጣቢያ ላይም ጥቃት ደርሷል።
- የወረዳው መሳሪያ ግምጃ ቤትም ተሰብሯል መባሉን ጠዋት ሰምተናል፡፡
- ሲንቄ ባንክ ላይም ከፍተኛ የመሰባበር ጉዳት ደርሷል፡፡ ሌሎች ባንኮች ግን ምንም አልሆኑም፡፡
- ታጣቂዎቹ በያቅጣጫው ወደ ከተማው መግባታቸው ነው የተሰማው፡፡ እኛ ወጥተን ማየት ፈጽሞ የማይታሰብ ብሆንም ጠዋት እንደሰማነው ቁጥራቸው ከፍተኛ ነው ተብሏል፡፡
- የቆሰሉ ሰዎች ወደ ሆስፒታል ተወስደዋል፡፡ አንድ ከታጣቂዎች የሞተ ሰው ግን አስከረኑ እስከ ከሰኣት አልተነሳም፡፡ እኛ ጠዋት እንደተመለከትነው ሰባት አስከሬን ቆጥረናል።
ሌላኛዋ ለደህንነታቸው የሰጉና ስማቸው እንዳይጠቀስ ያልፈለጉ ነዋሪ ፦
• ታጣቂዎቹ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው እንደመሆናቸው በከተማው ውስጥ በነበሩ የመንግስት ጸጥታ ሃይል ሚመለሱ አልነበሩም።
• አሁን ከቤት ለመውጣትም ሰግተናል፡፡ ወንድ ወንዱ ብቻ እየወጣ የሞቱትን ማንሳት ለቅሶ መድረስ ነው ያለው፡፡
• ከተማዋ ጸጥ ብላለች፡፡ ሱቆችን ጨምሮ ምንም የተከፈተ ነገርም የለም።
ኃላፊዎች ምን አሉ ?
📞 ሬድዮ ጣቢያው ለወረዳው ፖሊስ መምሪያ ኃላፊ ኢንስፔክተር ፋና ረጋሳ ቢደውልም ምላሽ ለመስጠት ፈቃደኛ አልሆኑም።
☎ ለኦሮሚያ ኮሚዩኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ ኃይሉ አዱኛም ስልክ ቢመታላቸውም ስልካቸው አነሳም።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የዴቼቨለ ሬድዮ ጣቢያ መሆኑን ይገልጻል።
@tikvahethiopia
በኦሮሚያ ክልል ፤ በምዕራብ ሸዋ ዞን ፤ አደኣ በርጋ ወረዳ በተፈጸመ ጥቃት የኢንጪኒ ከተማ ባለሥልጣን እና የጸጥታ አስከባሪዎችን ጨምሮ ቁጥራቸው በውል የማይታወቅ ሰዎች መገደላቸውን ነዋሪዎችን ዋቢ አድርጎ ዶቼ ቨለ ሬድዮ ዘግቧል።
የከተማው ነዋሪዎች ምን አሉ ?
ስማቸው ለደህንነታቸው ሲባል እንዲገለፅ ያልፈለጉ ነዋሪ ፦
* የሰባት ሰዎች አስከሬን ዛሬ ጠዋት ተገኝቷል።
* ማረሚያ ቤት ተሰብሮ እስረኞች ተለቀዋል።
* ህዳር 28 ቀን ለ29 ቀን 2016 ዓ.ም. አጥቢያ ከሌሊቱ ስድስት ሰኣት ጀምሮ ነው ጥቃት የተፈፀመው።
* የወረዳው ማረሚያ ቤት ተሰብሮ በመቶዎች የሚቆጠሩ እስረኞች ተለቀዋል።
* በታጣቂዎቹ ጥቃት የከተማዋ አስተዳዳሪን (ብርሃኑ ሃብትዬ) ጨምሮ የሰዎች ህይወት አልፏል።
* በተለያዩ ጥበቃ ስራ የሚሰሩ እንዲሁም በማረሚያ ቤት ጥበቃ ላይ ነበሩ የተባሉ ፖሊሶችም መገደላቸውን ሰምተናል።
* ዛሬ ጠዋት ህዝቡ ከጸጥታ ሃይሎች ጋር ወጥቶ አስክረ ሲሰበሰብ ነበር። ቢያንስ ወደ ሰባት አስከሬን ተገኝተዋል፡፡ የተጎዱትም ወደ ሆስፒታል ተወስደዋል፡፡
* በግምት ከእኩለ ሌሊት ስድስት ሰዓት ጀምሮ እስከ ሰባት ሰዓት ሰምተን የማናውቅ አይነት የተኩስ እሩምታ ነው ስንሰማ ያደርነው።
ሌላኛው ነዋሪ ፦
- በወረዳው የፖሊስ ጣቢያ ላይም ጥቃት ደርሷል።
- የወረዳው መሳሪያ ግምጃ ቤትም ተሰብሯል መባሉን ጠዋት ሰምተናል፡፡
- ሲንቄ ባንክ ላይም ከፍተኛ የመሰባበር ጉዳት ደርሷል፡፡ ሌሎች ባንኮች ግን ምንም አልሆኑም፡፡
- ታጣቂዎቹ በያቅጣጫው ወደ ከተማው መግባታቸው ነው የተሰማው፡፡ እኛ ወጥተን ማየት ፈጽሞ የማይታሰብ ብሆንም ጠዋት እንደሰማነው ቁጥራቸው ከፍተኛ ነው ተብሏል፡፡
- የቆሰሉ ሰዎች ወደ ሆስፒታል ተወስደዋል፡፡ አንድ ከታጣቂዎች የሞተ ሰው ግን አስከረኑ እስከ ከሰኣት አልተነሳም፡፡ እኛ ጠዋት እንደተመለከትነው ሰባት አስከሬን ቆጥረናል።
ሌላኛዋ ለደህንነታቸው የሰጉና ስማቸው እንዳይጠቀስ ያልፈለጉ ነዋሪ ፦
• ታጣቂዎቹ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው እንደመሆናቸው በከተማው ውስጥ በነበሩ የመንግስት ጸጥታ ሃይል ሚመለሱ አልነበሩም።
• አሁን ከቤት ለመውጣትም ሰግተናል፡፡ ወንድ ወንዱ ብቻ እየወጣ የሞቱትን ማንሳት ለቅሶ መድረስ ነው ያለው፡፡
• ከተማዋ ጸጥ ብላለች፡፡ ሱቆችን ጨምሮ ምንም የተከፈተ ነገርም የለም።
ኃላፊዎች ምን አሉ ?
📞 ሬድዮ ጣቢያው ለወረዳው ፖሊስ መምሪያ ኃላፊ ኢንስፔክተር ፋና ረጋሳ ቢደውልም ምላሽ ለመስጠት ፈቃደኛ አልሆኑም።
☎ ለኦሮሚያ ኮሚዩኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ ኃይሉ አዱኛም ስልክ ቢመታላቸውም ስልካቸው አነሳም።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የዴቼቨለ ሬድዮ ጣቢያ መሆኑን ይገልጻል።
@tikvahethiopia