TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.7K photos
1.61K videos
216 files
4.36K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#OLF

በእስር ላይ የሚገኙት የኦሮሞ ነፃነት ግንባር አመራሮች ጉዳይ ላይ ፍርድ ቤት ትዕዛዝ አስተላልፏል።

በቡራዩ እስር ላይ ካሉ 7 የኦነግ አመራሮች 4ቱ ከእስር እንዲለቀቁ የቡራዩ ወረዳ ፍ/ቤት ትዕዛዝ አስተላልፏል።

ጠበቃ አቶ ደምሴ ፍቃዱ ጉዳዩን በተመለከተ ለ #ቪኦኤ_ሬድዮ በሰጡት ቃል አራቱ የኦነግ አመራሮች አካልን ነፃ የማውጣት አቤቱታ አቅርበው እንደነበር፤ አቤቱታ የቀረበለት የቡራዩ ከተማ ፍ/ ቤት ግለሰቦቹ በማን እና ለምን እንደታሰሩ ለመረዳት ለሶስት ተከታታይ ችሎት ጥሪ ሲያቀርብ ነበር።

ነገር ግን ፖሊስ ሆነ እስረኞች አልቀረቡም። አርብ ሀምሌ 8 የኦሮሚያ ክልል ጠቅላይ አቃቤ ህግ ማብራሪያ ሠጥቷል።

ጠበቃ ደምሴ ፍቃዱ ፦

" 1ኛ አመልካች የሆነው ሚካኤል በቀለ ከዚህ ቀደም የወንጀል መዝገብ ተጣርቶበት በወንጀል አንቀፅ 42 መሰረት የተጠረጠረበት ጉዳይ ወንጀል ነው ተብሎ የሚያስከስስ ባለመሆኑ መዝገቡ ተዘግቶ ፖሊስ ከእስር ቤት እንዲለቀው ትዕዛዝ ፅፈንለት ፖሊስ ግን አለቅም ማለቱን አቃቤ ህግ ገልጿል።

2ኛ እና 3ኛ አመልካቾች ለሚ ቤኛ እና ዳዊት አብደታን በተመለከተ በተጠረጠሩበት ወንጀል ተከሰው የአቃቤ ህግ ምስክሮች ከተሰሙ በኃላ ፍርድ ቤት ጉዳዩን መርምሮ የሚያስቀጣ አይደለም በማለት በነፃ ካሰናበታቸው በኃላ ፖሊስ በራሱ ስልጣን ነው ያሰረው ሲል አቃቤ ህግ ለፍ/ ቤት አመልክቷል።

4ኛ አመልካች ገዳ ገቢሳ የተጠረጠረበት ወንጀል አቃቤ ህግ ከመረመረ በኃላ አያስከስስም ብሎ መዝገቡን ዘግቶ ከእስር እንዲለቀቅ ለፖሊስ ትዕዛዝ መስጠቱን አብራርቷል።

ከአቃቤ ህግም ምንም መዝገብ የላቸውም ሲል ነው የኦሮሚያ ጠቅላይ አቃቤ ህግ ለፍ/ ቤት ያስረዳው። "

ፍ/ቤት ሀምሌ 11 ከእስር እንዲለቀቁ የወሰነ ቢሆንን ታሳሪዎቹ እስካሁን አልተለቀቁም።

@TIKVAHETHIOPIA
👍304😢47👏98🙏7🥰1