TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.3K photos
1.51K videos
212 files
4.11K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ረቂቅ ህገ-መንግስት በጉባኤው አባላት በአብላጫ ድምጽ መፅደቁ ተነግሯል። ዛሬ ጠዋት በአርባ ምንጭ ከተማ መካሄድ በጀመረው የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ህገ-መንግስት አጽዳቂ ኮሚሽን ጉባኤ የቀረበው ረቂቅ ህገ-መንግስት በ10 ተቃውሞ በ2 ድምጸ ተአቅቦ በአብላጫ ድምጽ መፅደቁ ተነግሯል። የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል  ረቂቅ ህገ-መንግስቱ 11 ምዕራፎች፣ 141 ዋና ዋና አንቀጾች…
#Update

የቀድሞው የጋሞ ጎፋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ጥላሁን ከበደ " ደቡብ ኢትዮጵያ ክልል "ን በርዕሰ መስተዳደርነት እንዲመሩ ተሾሙ።

የ44 ዓመቱ ገልማሳ አቶ ጥላሁን ከዚህ ቀደም ፦
- በሃዲያ ዞን ሶሮ ወረዳ የጤና ጣቢያ ኃላፊ፣
- በቀድሞ ጋሞ ጎፋ ዞን የውባ ደብረፃይ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ፣
- በቀድሞ ጋሞ ጎፋ ዞን ንግድ እና ኢንዱስትሪ መምሪያ ኃላፊ፣
- በቀድሞ ጋሞ ጎፋ ዞን የድርጅት አደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ ፣
- የቀድሞ ጋሞ ጎፋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ፣
- በደቡብ ክልል በምክትል ርዕሰ መስተዳደር ማዕረግ የግብርና እና ገጠር ልማት ክላስተር አስተባባሪ እንዲሁም የእርሻ እና ተፈጥሮ ሃብት ቢሮ ኃላፊ
- የደቡብ ክልል የብልፅግና ፓርቲ ፅ/ቤት ኃላፊ ሆነው መስራታቸው ተገልጿል።

አመራሩ በትምህርት ደረጃቸው በከተማ ልማት አስተዳደር ሁለተኛ ዲግሪ ያላቸው ሲሆን ከዚህ ቀደም በተመደቡበት ቦታ ህዝባቸውን #በንፅህና በእኩልነት የመሩ ናቸው ተብሏል።

@tikvahethiopia