TIKVAH-ETHIOPIA
1.52M subscribers
59.5K photos
1.52K videos
215 files
4.14K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
June 4, 2022
TIKVAH-ETHIOPIA
" ቲክቶክ " ኬንያ ውስጥ እንዲታገድ አቤቱታ ቀረበ። የኬንያ ፓርላማ " #ቲክቶክ " የተሰኘው የማኅበራዊ መገናኛ ዘዴ እንዲያግድ አቤቱታ እንደቀረበለት የኬንያ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል። " ወጣቶች ትምህርታቸውን ትተው የ 'ቲክቶክ' ቁራኛና የአዕምሮ ህመምተኛ እየሆኑ ነው " የሚለው አቤቱታው ፓርላማው አፋጣኝ ውሳኔ እንዲሰጥ ጠይቋል። የፓርላማው አፈጉባኤ ሞሰስ ዋታንጉላ፣ " ሁከትን እና የጥላቻ ንግግርን…
August 24, 2023
TIKVAH-ETHIOPIA
#ቲክቶክ ለምንድነው ሀገራት " ቲክቶክ " ን ለማገድ እየተንቀሳቀሱ ያሉት ? ከቅርብ ወራት ወዲህ አሜሪካ፣ አውሮፓ፣ ካናዳ ያሉ የህግ አውጪዎች ከፀጥታ እና ደህንነት ስጋት ጋር በማያያዝ ግዙፉን የአጫጭር ቪድዮዎች ማጋሪያ " ቲክቶክ " ን ለማገድ / ለመገደብ የሚያደርጉትን ጥረት ማጠናከራቸውን ኒውዮርክ ታይምስ አስነብቧል። ዋይትሃውስ እኤአ በፌብሩዋሪ 27 የፌዴራል  ኤጀንሲዎች አፕሊኬሽኑን ከመንግሥት…
December 16, 2023
March 22, 2024
April 20, 2024
TIKVAH-ETHIOPIA
" ቲክቶክ ላይት " ጥያቄ ቀረበበት። አዲሱ መተግበሪያው ' ቲክቶክ ላይት ' በፈረንሳይ እና ስፔይን አገልግሎት የጀመረው ቲክቶክ በህጻናት እና ተጠቃሚዎች የአዕምሮ ጤንነት ላይ ሊያስከትል ስለሚችለው አደጋ ያለውን ግምገማ በ24 ሰዓት ውስጥ እንዲያቀርብ ዛሬ የአውሮፓ ኮሚሽን ጠየቀ። ከዋናው ቲክቶክ መተግበሪያ አነስ ብሎ የወጣው የቲክቶክ መተገበሪያ ተጠቃሚዎች #ተከፍሏቸው የቪዲዮ ምስሎችን እንዲመለከቱ…
May 1, 2024
TIKVAH-ETHIOPIA
#Australia የአውስትራሊያ የተወካዮች ም/ቤት ከ16 ዓመት በታች ያሉ አዳጊዎች ማኅበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ የሚያግድ ሕግ አጸደቀ። ሕጉ በሃገሪቱ የእንደራሴዎች ም/ቤት (ሴኔት) ከጸደቀ በዓለም የመጀመሪያው ይሆናል። የተወካዮች ም/ቤቱ በ102 ድጋፍ እና 13 ተቃውሞ ድምጽ አጽድቆታል። በሃገሪቱ የሚገኙ ዋና ፓርቲዎች የደገፉት ሕግ ፦ ➡️ ቲክቶክ፣ ➡️ ፌስቡክ፣ ➡️ ስናፕቻት፣ ➡️ ሬዲት፣…
November 27, 2024
TIKVAH-ETHIOPIA
" ቲክቶክ የሰፈር ወሮበላ ነው " - ጠ/ሚ ኤዲ ራማ ከሳምንታት በፊት አልባንያ ውስጥ አንድ የ14 ዓመት ታዳጊ በስለት ተወግቶ መገደሉን ተከትሎ አልባንያ ቲክቶክን ለማገድ ልታስብ እንደምትችል መረጃ መለዋወጣችን ይታወሳል። አሁን ደግሞ የሀገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ኤዲ ራማ ሀገራቸው ለ1 ዓመት ቲክቶክን እንደምታግድ ተናግረዋል። ባለፈው ወር የ14 ዓመቱ ታዳጊ ከተገደለ በኋላ ማኅበራዊ ሚዲያ ልጆች ላይ…
January 15
TIKVAH-ETHIOPIA
#TikTok ' ቲክቶክ ' የተሰኘው መተግበሪያ አልባኒያ ውስጥ ለአንድ አመት እንደሚታገድ መገለጹ ይታወሳል። " እገዳው በኦንላይ የንግድ ስራ የሚሰሩ / ማርኬቲንግ ላይ ያሉ እንዲሁም የንግግርና ሃሳብ ነጻነት ላይ አሉታዊ ተፅእኖ ያመጣል " በሚል የመብት ተሟጋች ነን በሚሉ አካላት እገዳው ቢተችም የሀገሪቱ መንግሥት እገዳውን ተግባራዊ ያደርጋል ተብሏል። ቲክቶክ በቀጣይ ሳምንታት ይወርዳል ተብሏል። …
#TikTok📱

' ቲክቶክ ' አሜሪካ ውስጥ ከእሁድ ጀምሮ እስከ ወዲያኛው እንዲዘጋ ወይም እንዲሸጥ የሚለውን ውሳኔ የአሜሪካ ጠቅላይ ፍ/ቤት ደገፈ።

ዛሬ የአሜሪካ ጠቅላይ ፍ/ቤት ' ቲክቶክ ' በአሜሪካ እንዲዘጋ ካልሆነም እዲሸጥ ለሚጠይቀው የፌደራል ህግ ድጋፍ ሰጥቷል።

' ቲክቶክ ' ይግባኝ ቢጠይቅም ውድቅ ሆናል።

ከዚህ ቀደም መተግበሪያው " የአሜሪካውያንን የግል መረጃ ለቻይና መንግሥት አሳልፎ ይሰጣል በዚህ የብሔራዊ ጸጥታ አደጋ ደቅኗል "  በሚል እንዲታገድ ካልሆነም ለአሜሪካ ሰዎች እንዲሸጥ የሚል ውሳኔ መተላለፉ ይታወሳል።

ዛሬ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከዚህ ቀደም የተላለፈውን ውሳኔ ደግፏል።

ይህን ውሳኔ ተከትሎ ' ቲክቶክ ' ከእሁድ ጀምሮ ይታገዳል።

የእግዱ ተግባራዊነት ' ቲክቶክ 'ን ከአፕስቶር እና ፕሌይስቶር ላይ እንዲወገድ ያደርጋል።

አዲስ ተጠቃሚዎች ' ቲክቶክ ' ማውረድ አይችሉም ፤ ነባር ተጠቃሚዎች አፕዴት ማድረግ አይችሉም።

ተመራጩ ፕሬዜዳንት ዶናልድ ትራምፕ ' ቲክቶክ ' ን ለመታደግ እና የመታገዱ ውሳኔ እንዲዘገይ ለጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ጠይቀው የነበረ ቢሆንም ፍርድ ቤቱ ግን የመጨረሻ ያለውን ውሳኔ አሳልፏል።

እንሆ ስልጣኑ ያበቃው የባይደን አስተዳደር " ህጉን ማስተግበር የቀጣዩ አስተዳደር ኃላፊነት ነው " ብሏል።

የ' ቲክቶክ ' ን እገዳ ለማዘግየት የሞከሩት ትራምፕ ሰኞ ስልጣናቸውን ይረከባሉ። ህጉን ማስተግበርም በሳቸው ላይ ተጥሏል።

ትራምፕ ከፍርድ ቤቱ ውሳኔ በኃላ በሰጡት ቃል " ውሳኔውን እኔው ወስናለሁ ፤ ውሳኔው እኔ ጋር ነው ምን እንደማደርግ ታያላችሁ " ብለዋል።

170 ሚሊዮን ተጠቃሚ አሜሪካ ውስጥ ያለው ' ቲክቶክ ' እስከወዲያኛው ይታገድ ይሆን ? ወይስ ከዚህ በኃላ ትራምፕ ማድረግ የሚችሉት ነገር ይኖር ይሆን ? በቀጣይ ይታያል።

መረጃው ከኤፒ፣ ፎርብስ፣ ሲኤንኤን የተሰባሰበ ነው።

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
January 17