እስራኤል ዜጎቿን ከአማራ ክልል ወደ #ትግራይ ክልል ማስወጣቷን " ጄሩሳሌም ፖስት " ዘግቧል።
እስራኤል በአማራ ክልል ውስጥ ያለውን ግጭትና የታወጀውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በቅርበት እየተከታተለችው መሆኑ ተነግሯል።
ባለፈው ሰኞ ከአካባቢው የመንግሥት ኃላፊዎች ጋር በመሆን ተጓዥ ዜጎቿን ከአማራ ክልል ወደ ትግራይ እንዲወጡ ማድረጓ ተገልጿል።
ዘገባው ተካሂዷል ባለው የእስራኤል ዜጎችን ከግጭት ቀጠና የማስወጣት ኦፕሬሽን 13 ተጓዥ እስራኤላውያን እና ሌሎች 7 ሌሎች የውጭ ሀገር ዜጎች ከደባርቅ ወደ ትግራይ ሽረ ከተማ እንዲወጡ ተደርጓል።
ከሽረ ከተማም በአውሮፕላን በረራ ወደ አዲስ አበባ እንደሚጓዙ ተነግሯል።
በሌሎች የአማራ ክልል አካባቢዎች እስራኤላውያን መኖራቸው የተመላከተ ሲሆን ሀገሪቱ ክትትል እያደረገችና ከግጭት ቀጠና ደህንነታቸው ተጠብቆ ለማስወጣት በሚቻልበት ሁኔታ መንገድ እየተፈለገ መሆኑ ተነግሯል።
በአማራ ክልል በተለይም በጎንደር ከተማ ፤ ወደ እስራኤል ለመሄድ የሚጠባበቁ አባላት በርከታ ቤተእስራኤላውያን ማህበረሰብ አባላት አሉ።
#ጄሩሳሌም_ፖስት
@tikvahethiopia
እስራኤል በአማራ ክልል ውስጥ ያለውን ግጭትና የታወጀውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በቅርበት እየተከታተለችው መሆኑ ተነግሯል።
ባለፈው ሰኞ ከአካባቢው የመንግሥት ኃላፊዎች ጋር በመሆን ተጓዥ ዜጎቿን ከአማራ ክልል ወደ ትግራይ እንዲወጡ ማድረጓ ተገልጿል።
ዘገባው ተካሂዷል ባለው የእስራኤል ዜጎችን ከግጭት ቀጠና የማስወጣት ኦፕሬሽን 13 ተጓዥ እስራኤላውያን እና ሌሎች 7 ሌሎች የውጭ ሀገር ዜጎች ከደባርቅ ወደ ትግራይ ሽረ ከተማ እንዲወጡ ተደርጓል።
ከሽረ ከተማም በአውሮፕላን በረራ ወደ አዲስ አበባ እንደሚጓዙ ተነግሯል።
በሌሎች የአማራ ክልል አካባቢዎች እስራኤላውያን መኖራቸው የተመላከተ ሲሆን ሀገሪቱ ክትትል እያደረገችና ከግጭት ቀጠና ደህንነታቸው ተጠብቆ ለማስወጣት በሚቻልበት ሁኔታ መንገድ እየተፈለገ መሆኑ ተነግሯል።
በአማራ ክልል በተለይም በጎንደር ከተማ ፤ ወደ እስራኤል ለመሄድ የሚጠባበቁ አባላት በርከታ ቤተእስራኤላውያን ማህበረሰብ አባላት አሉ።
#ጄሩሳሌም_ፖስት
@tikvahethiopia