የቀድሞ የኢትዮጵያ ሰራዊት የድጋፍና ልማት ማህበር ፤ ድጋፍ ይደረግለት ዘንድ ጥሪ አቀረበ።
ማህበሩ ለቲክቫህ በላከው ደብዳቤ ባለፉት ሶስት አመታት ከ300 በላይ በሆኑ ወረዳዎች የሚገኙ ከ330 ሺህ በላይ የቀድሞ ሰራዊር አባላት አጠቃላይ ወደ 1 ሚሊዮን የሚጠጉ የቀድሞ የኢትዮጵያ ሰራዊት አባላት፣ ቤተሰቦቻቸው እና ወዳጆቻቸውን በማቀፍ እና በማሰባሰብ በልማትና ድጋፍ ልየ ልዩ ተግባራት ስራ ላይ ተሰማርቶ እንደሚገኝ ገልጿል።
" ይህ በሀገሩ ባይተዋር ተደርጎ የነበረው የቀድሞ የኢትዮጵያ ሰራዊት በደረሰበት ፓለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ መገለል ምክንያት ከፍተኛ ችግሮች ውስጥ የሚገኝ የህብረተሰብ አካል ነው " ያለው ማህበሩ ይህንን የቀድሞ ሰራዊት አባላትና ቤተሰቦቻቸውን ገፍቶ የነበረውን ሁኔታ በመለወጥ ሰራዊቱንና ቤተሰቦቹን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በርካታ ተግባራትን እያከናወነ እንደሚገኝ አስረድቷል።
በኢኮኖሚ መስክ ጠንካራ የልማት ርብርብ ለማድረግ እንዲሁም አንገቱን ዝቅ አድርጎ የነበረውን የሀገር ባለውለታ ሠራዊት በልማቱ በሀገሩ ተሰማርቶ ለሚያከናነው ከፍተኛ አስተወፅኦ የልማት አጋር ለመሆን ድጋፍ እንዲደረግ ማህበሩ ይፋዊ ጥሪ አቅርቧል።
ድጋፉ በቀድሞ የኢትዮጵያ ሠራዊት የልማትእና የድጋፍ ማህበር ስም በተከፈተው የሂሳብ ቁጥር 1000552221102 (ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ) በመጠቀም የሚደረግ ሲሆን ሁሉም ዜጋ የተቻለውን እንዳያደርግ ማህበሩ ጥሪውን አቅርቧል።
ዜጎች ለሚያደርጉት ድጋፍ ተጨማሪ ማብራሪያ በ 0921433163 እና 0911965296 በመደወል መጠይቅ ይቻሉ ሲል አሳውቋል።
@tikvahethiopia
ማህበሩ ለቲክቫህ በላከው ደብዳቤ ባለፉት ሶስት አመታት ከ300 በላይ በሆኑ ወረዳዎች የሚገኙ ከ330 ሺህ በላይ የቀድሞ ሰራዊር አባላት አጠቃላይ ወደ 1 ሚሊዮን የሚጠጉ የቀድሞ የኢትዮጵያ ሰራዊት አባላት፣ ቤተሰቦቻቸው እና ወዳጆቻቸውን በማቀፍ እና በማሰባሰብ በልማትና ድጋፍ ልየ ልዩ ተግባራት ስራ ላይ ተሰማርቶ እንደሚገኝ ገልጿል።
" ይህ በሀገሩ ባይተዋር ተደርጎ የነበረው የቀድሞ የኢትዮጵያ ሰራዊት በደረሰበት ፓለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ መገለል ምክንያት ከፍተኛ ችግሮች ውስጥ የሚገኝ የህብረተሰብ አካል ነው " ያለው ማህበሩ ይህንን የቀድሞ ሰራዊት አባላትና ቤተሰቦቻቸውን ገፍቶ የነበረውን ሁኔታ በመለወጥ ሰራዊቱንና ቤተሰቦቹን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በርካታ ተግባራትን እያከናወነ እንደሚገኝ አስረድቷል።
በኢኮኖሚ መስክ ጠንካራ የልማት ርብርብ ለማድረግ እንዲሁም አንገቱን ዝቅ አድርጎ የነበረውን የሀገር ባለውለታ ሠራዊት በልማቱ በሀገሩ ተሰማርቶ ለሚያከናነው ከፍተኛ አስተወፅኦ የልማት አጋር ለመሆን ድጋፍ እንዲደረግ ማህበሩ ይፋዊ ጥሪ አቅርቧል።
ድጋፉ በቀድሞ የኢትዮጵያ ሠራዊት የልማትእና የድጋፍ ማህበር ስም በተከፈተው የሂሳብ ቁጥር 1000552221102 (ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ) በመጠቀም የሚደረግ ሲሆን ሁሉም ዜጋ የተቻለውን እንዳያደርግ ማህበሩ ጥሪውን አቅርቧል።
ዜጎች ለሚያደርጉት ድጋፍ ተጨማሪ ማብራሪያ በ 0921433163 እና 0911965296 በመደወል መጠይቅ ይቻሉ ሲል አሳውቋል።
@tikvahethiopia
Audio
#ይደመጥ
የትምህርት ሚኒስቴር ፤ ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ሳሙኤል ክፍሌ የ " መውጫ ፈተና " ን በተመለከተ ለፋና ቴሌቪዥን የሰጡት ዝርዝር ማብራሪያ ከላይ ተያይዟል።
በዚህ ማብራሪያ ፦
- የፈተናውን አይነት
- የውጤት አገላለፅ
- የጤና ተማሪዎች ፈተና / የሙያቸው እና የመውጫው
- እንደው ተማሪዎች ፈተናውን ባያልፉ መቼ እና የት ? እስከ ስንት ጊዜ ድረስ ድጋሚ መውሰድ እንደሚችሉ
- የፈተናው ደህንነት
- የተማሪዎች ምረቃ / ውጤት ያላመጡ ምረቃ ላይ ይሳተፋሉ በሚለው ላይ የትምህርት ሚኒስቴር አቋም ምን እንደሆነ
.
.
. ሌሎችንም ምላሽ የሚፈልጉ ጉዳዮችን በዝርዝር ለመላው ተፈታኝ ተማሪዎች፣ ለተማሪ ወላጆች፣ ለሁሉም የህብረተሰብ ክፍል አስረድተዋል።
ፋይሉ 28.2 MB ነው።
Credit : #FBC
@tikvahethiopia
የትምህርት ሚኒስቴር ፤ ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ሳሙኤል ክፍሌ የ " መውጫ ፈተና " ን በተመለከተ ለፋና ቴሌቪዥን የሰጡት ዝርዝር ማብራሪያ ከላይ ተያይዟል።
በዚህ ማብራሪያ ፦
- የፈተናውን አይነት
- የውጤት አገላለፅ
- የጤና ተማሪዎች ፈተና / የሙያቸው እና የመውጫው
- እንደው ተማሪዎች ፈተናውን ባያልፉ መቼ እና የት ? እስከ ስንት ጊዜ ድረስ ድጋሚ መውሰድ እንደሚችሉ
- የፈተናው ደህንነት
- የተማሪዎች ምረቃ / ውጤት ያላመጡ ምረቃ ላይ ይሳተፋሉ በሚለው ላይ የትምህርት ሚኒስቴር አቋም ምን እንደሆነ
.
.
. ሌሎችንም ምላሽ የሚፈልጉ ጉዳዮችን በዝርዝር ለመላው ተፈታኝ ተማሪዎች፣ ለተማሪ ወላጆች፣ ለሁሉም የህብረተሰብ ክፍል አስረድተዋል።
ፋይሉ 28.2 MB ነው።
Credit : #FBC
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ይደመጥ የትምህርት ሚኒስቴር ፤ ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ሳሙኤል ክፍሌ የ " መውጫ ፈተና " ን በተመለከተ ለፋና ቴሌቪዥን የሰጡት ዝርዝር ማብራሪያ ከላይ ተያይዟል። በዚህ ማብራሪያ ፦ - የፈተናውን አይነት - የውጤት አገላለፅ - የጤና ተማሪዎች ፈተና / የሙያቸው እና የመውጫው - እንደው ተማሪዎች ፈተናውን ባያልፉ መቼ እና የት ? እስከ ስንት ጊዜ ድረስ ድጋሚ መውሰድ እንደሚችሉ - የፈተናው…
#ExitExam
ዶ/ር ሳሙኤል ክፍሌ ምን አሉ ?
የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ሳሙኤል ክፍሌ ለመጀመሪያ ጊዜ የሚሰጠውን የመውጫ ፈተናን በተመለከተ ለፋና ቴሌቪዥን ዝርዝር ማብራሪያ ሰጥተዋል።
በማብራሪያቸው ምን አሉ ?
- የፈተናው አይነት " የምርጫ ጥያቄ " መሆኑን ገልፀዋል።
- የፈተናው ጥያቄ ብዛት በተመለከተ ጊዜው ሲደርስ እንደሚገለፅ፤ የጥየቄው ብዛት ግን ከ50 በላይ እንደሆነ ፤ በአብዛኛው ፕሮግራም 100 ጥያቄ እንደሚኖር አሳውቀዋል።
- በአብዛኛው ፕሮግራም 100 ጥያቄ ነው ፈተናው ፤ በተወሰኑ መስኮች ምርጫውን ለመሙላት ብዙ ሂሳብ ስለሚሰሩ የጥያቄ ቁጥሩ ከ100 ሊያንስ ይችላል።
- ተማሪዎች ፈተናውን እንደተፈተኑ ውጤታቸውን ወዲያው መላክ የሚያስችል ቴክኖሎጂ ቢሮርም የመጀመሪያ ቀን የተፈተኑ ተማሪዎች ውጤት ቢገለፅ ሌሎች ላይ ከሚያሳድረው ጫና አንፃር ወይም ፈተናው ቀለል / ከባድ ነው ብሎ እንዳይዘናጋ / እንዳይጨነቅ ወዲያው አይገለፅም። የፈተናው ውጤት የሚገለፀው የመጨረሻው ፈተና ከተሰጠ ከአንድ ቀን በኃላ ነው።
- ውጤት አልፏል ወድቋል ብቻ ሳይሆን ተማሪው ያመጣው ውጤት ይገለፃል።
- የጤና ተማሪዎች ፈተና ሰኔ 30 ይጀምራል እስከ ሐምሌ 8 ድረስ ይዘልቃል። የጤና ተማሪዎች ቀድመው የሚፈተኑበት ምክንያት ቀኑን ሙሉ ፈተናውን ስለሚወስዱ ነው። ጥዋት ላይ ከሙያቸው ጋር የተያያዘውን ይፈታናሉ ፤ ከሰዓት ላይ የመውጫውን ፈተና ይወስዳሉ / በተቃራኒው / ።
- ፈተናው በከፍተኛ ጥንቃቄ ነው የተዘጋጀው ፤ በውስን ኃላፊዎች ብቻ እንዲታወቅ ተደርጓል፤ ስለማይታተም፣ እጅም ስለሌለበት ደህንነቱ አያሰጋንም።
- ፈተናውን ከመስጫው ሰከንድ በፊት ማየት የሚችል ሰው አይኖርም። ፈተናው ካለቀበት ሰከንድ በኃላ መስራት የሚችል ሰው አይኖርም። ይህ በማዕከል ነው ቁጥጥር የሚደረገው።
- የማለፊያው ነጥብ 50 % እና በላይ ሲሆን ይህን ያላለፉ (ኮርስ ያልጨረሱ) ከ5 / ከ6 ወር በኃላ ጥር እና የካቲት ላይ የሚሰጠውን የመውጫ ፈተና መውሰድ ይችለሉ። በዚህም ከለተሳካ ከቀጣይ አመት ተፈታኞች ጋር መውሰድ ይቻላል። በዓመት ሁለት ጊዜ ለመስጠት ታቅዷል።
- አብዛኛው ተማሪ በመጀመሪያው ዙር ያልፋል የሚል እምነት እንዳላቸው ገልጸዋል፤ ካልሆነ ግን በሁለተኛው ዙር ተፈትኖ ያልፋል። ሁለቴ ተፈትኖ ማለፍ ያልቻለ እስከሚያልፍ / 50 % እና ከዚያ በላይ ማምጣቱ እስኪረጋገጥ ፈተናውን መውሰድ ይችላል።
- ፈተናው ተማሪዎች አልተሳካላቸውም ብሎ የማሸማቀቅ ዓለማ ስለሌለው እስኪያልፉ ድረስ መፈተን ይችላሉ።
- ምናልባት ያላለፉ ተማሪዎች ዳግም ፈተና ለመውሰድ መጀመሪያ ሲማሩበት ወደነበረበት ተቋም መሄድ አይጠበቅባቸውም ፤ ባሉበት አካባቢ ባሉ ተቋማት ፈተናውን እንደሚወስዱ የሚደረግበት ሁኔታ ይኖራል።
- ከ50 በመቶ በታች ያመጡ ተማሪዎች በምረቃ ፕሮግራም ላይ ይሳተፋሉ ? ትምህርት ሚኒስቴር የምረቃ ፕሮግራም በተመለከተ በፖሊሲው ላይ እንደማይፅፍ ገልፀዋል። ጉዳዩ የተቋማት ነው ብለዋል። ሚኒስቴሩ በፖሊሲ የሚያስገድደው ግን የመውጫ ፈተናው የስርዓተ ትምህርቱ አካል ስለሆነ ይህን ያላለፈ ዲግሪ/ጊዜያዊ ጭምር፣ ትራንስክሪብት አይሰጠውም። የምረቃ ፕሮግራም ከማዕከል አይመራም ይህ የተቋማቱ ጉዳይ ነው። እኛ የምንከታተለው ፈተናውን ሳያልፉ ዲግሪ እንዳይሰጣቸው ነው።
- የምረቃ ጉዳይ እና በዕለቱ በምረቃ ላይ የሚሳተፉ ተማሪዎች ጉዳይ የሴኔት ነው ትምህርት ሚኒስቴር አይመለከተውም። ነገር ግን የመውጫ ፈተናው እየተሰጠ/ ሳይሰጥ በፊት ምረቃ ማድረግ በፍፁም አይቻልም።
- የመውጫ ፈተና ያላለፈ ተማሪ በፍፁም ዲግሪ፣ ቴምፖራሪ ዲግሪ፣ ሰርተፊኬት እንደማይሰጠው አስገንዝበዋል።
@tikvahethiopia
ዶ/ር ሳሙኤል ክፍሌ ምን አሉ ?
የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ሳሙኤል ክፍሌ ለመጀመሪያ ጊዜ የሚሰጠውን የመውጫ ፈተናን በተመለከተ ለፋና ቴሌቪዥን ዝርዝር ማብራሪያ ሰጥተዋል።
በማብራሪያቸው ምን አሉ ?
- የፈተናው አይነት " የምርጫ ጥያቄ " መሆኑን ገልፀዋል።
- የፈተናው ጥያቄ ብዛት በተመለከተ ጊዜው ሲደርስ እንደሚገለፅ፤ የጥየቄው ብዛት ግን ከ50 በላይ እንደሆነ ፤ በአብዛኛው ፕሮግራም 100 ጥያቄ እንደሚኖር አሳውቀዋል።
- በአብዛኛው ፕሮግራም 100 ጥያቄ ነው ፈተናው ፤ በተወሰኑ መስኮች ምርጫውን ለመሙላት ብዙ ሂሳብ ስለሚሰሩ የጥያቄ ቁጥሩ ከ100 ሊያንስ ይችላል።
- ተማሪዎች ፈተናውን እንደተፈተኑ ውጤታቸውን ወዲያው መላክ የሚያስችል ቴክኖሎጂ ቢሮርም የመጀመሪያ ቀን የተፈተኑ ተማሪዎች ውጤት ቢገለፅ ሌሎች ላይ ከሚያሳድረው ጫና አንፃር ወይም ፈተናው ቀለል / ከባድ ነው ብሎ እንዳይዘናጋ / እንዳይጨነቅ ወዲያው አይገለፅም። የፈተናው ውጤት የሚገለፀው የመጨረሻው ፈተና ከተሰጠ ከአንድ ቀን በኃላ ነው።
- ውጤት አልፏል ወድቋል ብቻ ሳይሆን ተማሪው ያመጣው ውጤት ይገለፃል።
- የጤና ተማሪዎች ፈተና ሰኔ 30 ይጀምራል እስከ ሐምሌ 8 ድረስ ይዘልቃል። የጤና ተማሪዎች ቀድመው የሚፈተኑበት ምክንያት ቀኑን ሙሉ ፈተናውን ስለሚወስዱ ነው። ጥዋት ላይ ከሙያቸው ጋር የተያያዘውን ይፈታናሉ ፤ ከሰዓት ላይ የመውጫውን ፈተና ይወስዳሉ / በተቃራኒው / ።
- ፈተናው በከፍተኛ ጥንቃቄ ነው የተዘጋጀው ፤ በውስን ኃላፊዎች ብቻ እንዲታወቅ ተደርጓል፤ ስለማይታተም፣ እጅም ስለሌለበት ደህንነቱ አያሰጋንም።
- ፈተናውን ከመስጫው ሰከንድ በፊት ማየት የሚችል ሰው አይኖርም። ፈተናው ካለቀበት ሰከንድ በኃላ መስራት የሚችል ሰው አይኖርም። ይህ በማዕከል ነው ቁጥጥር የሚደረገው።
- የማለፊያው ነጥብ 50 % እና በላይ ሲሆን ይህን ያላለፉ (ኮርስ ያልጨረሱ) ከ5 / ከ6 ወር በኃላ ጥር እና የካቲት ላይ የሚሰጠውን የመውጫ ፈተና መውሰድ ይችለሉ። በዚህም ከለተሳካ ከቀጣይ አመት ተፈታኞች ጋር መውሰድ ይቻላል። በዓመት ሁለት ጊዜ ለመስጠት ታቅዷል።
- አብዛኛው ተማሪ በመጀመሪያው ዙር ያልፋል የሚል እምነት እንዳላቸው ገልጸዋል፤ ካልሆነ ግን በሁለተኛው ዙር ተፈትኖ ያልፋል። ሁለቴ ተፈትኖ ማለፍ ያልቻለ እስከሚያልፍ / 50 % እና ከዚያ በላይ ማምጣቱ እስኪረጋገጥ ፈተናውን መውሰድ ይችላል።
- ፈተናው ተማሪዎች አልተሳካላቸውም ብሎ የማሸማቀቅ ዓለማ ስለሌለው እስኪያልፉ ድረስ መፈተን ይችላሉ።
- ምናልባት ያላለፉ ተማሪዎች ዳግም ፈተና ለመውሰድ መጀመሪያ ሲማሩበት ወደነበረበት ተቋም መሄድ አይጠበቅባቸውም ፤ ባሉበት አካባቢ ባሉ ተቋማት ፈተናውን እንደሚወስዱ የሚደረግበት ሁኔታ ይኖራል።
- ከ50 በመቶ በታች ያመጡ ተማሪዎች በምረቃ ፕሮግራም ላይ ይሳተፋሉ ? ትምህርት ሚኒስቴር የምረቃ ፕሮግራም በተመለከተ በፖሊሲው ላይ እንደማይፅፍ ገልፀዋል። ጉዳዩ የተቋማት ነው ብለዋል። ሚኒስቴሩ በፖሊሲ የሚያስገድደው ግን የመውጫ ፈተናው የስርዓተ ትምህርቱ አካል ስለሆነ ይህን ያላለፈ ዲግሪ/ጊዜያዊ ጭምር፣ ትራንስክሪብት አይሰጠውም። የምረቃ ፕሮግራም ከማዕከል አይመራም ይህ የተቋማቱ ጉዳይ ነው። እኛ የምንከታተለው ፈተናውን ሳያልፉ ዲግሪ እንዳይሰጣቸው ነው።
- የምረቃ ጉዳይ እና በዕለቱ በምረቃ ላይ የሚሳተፉ ተማሪዎች ጉዳይ የሴኔት ነው ትምህርት ሚኒስቴር አይመለከተውም። ነገር ግን የመውጫ ፈተናው እየተሰጠ/ ሳይሰጥ በፊት ምረቃ ማድረግ በፍፁም አይቻልም።
- የመውጫ ፈተና ያላለፈ ተማሪ በፍፁም ዲግሪ፣ ቴምፖራሪ ዲግሪ፣ ሰርተፊኬት እንደማይሰጠው አስገንዝበዋል።
@tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ገንዘብ ወደየት ማስተላለፍ ይፈልጋሉ ?
ከአፖሎ ዲጂታል አካውንትዎ ገንዘብ ወደ አቢሲንያ ባንክ ሂሳብዎ እንዲሁም ወደ ሌሎች የተለያዩ ባንኮች እና ፋይናንስ ተቋማት በቀላሉ ማስተላለፍ ይችላሉ፡፡ ለዛሬ ከአፖሎ ዲጂታል አካውንትዎ ወደ አቢሲንያ ባንክ ሂሳብዎ እንዴት ማስተላለፍ እንደሚችሉ የሚያሳየውን ቪዲዮ ይመልከቱ፡፡
መተግበሪያውን ለማውረድ ሊንኩን ይጠቀሙ።
https://apollo.bankofabyssinia.com/download-apollo
#Apollodigitalproduct #AbyssiniaDigital #TransferToOthers #poweredbybankofabyssinia #BankofAbyssinia #የሁሉም_ምርጫ #The_Choice_For_all
ከአፖሎ ዲጂታል አካውንትዎ ገንዘብ ወደ አቢሲንያ ባንክ ሂሳብዎ እንዲሁም ወደ ሌሎች የተለያዩ ባንኮች እና ፋይናንስ ተቋማት በቀላሉ ማስተላለፍ ይችላሉ፡፡ ለዛሬ ከአፖሎ ዲጂታል አካውንትዎ ወደ አቢሲንያ ባንክ ሂሳብዎ እንዴት ማስተላለፍ እንደሚችሉ የሚያሳየውን ቪዲዮ ይመልከቱ፡፡
መተግበሪያውን ለማውረድ ሊንኩን ይጠቀሙ።
https://apollo.bankofabyssinia.com/download-apollo
#Apollodigitalproduct #AbyssiniaDigital #TransferToOthers #poweredbybankofabyssinia #BankofAbyssinia #የሁሉም_ምርጫ #The_Choice_For_all
ለፈጣሪ የመታዘዝ እና የጽኑ እምነት ምሳሌ ለሆነው ኢድ አል- አድሃ (አረፋ) በዓል ከወዲሁ እንኳን በሰላም አደረሰዎ እያልን እስከ 32% ቅናሽ ያደረግንበትን አስደሳች ልዩ የኢድ አል- አድሃ (አረፋ) የሞባይል ጥቅል አቅርበናል!
በቴሌብር ሱፐርአፕ፣ ማይ ኢትዮቴል መተግበሪያዎች ወይም *999#
የበዓሉን ጥቅል ይግዙ፤ ወዳጅ ዘመድዎን ይዘይሩ!
(ኢትዮ ቴሌኮም)
በቴሌብር ሱፐርአፕ፣ ማይ ኢትዮቴል መተግበሪያዎች ወይም *999#
የበዓሉን ጥቅል ይግዙ፤ ወዳጅ ዘመድዎን ይዘይሩ!
(ኢትዮ ቴሌኮም)
Preliminary_Report_by_CECOE_Referendum_rerun_in_the_Wolaita_zone.pdf
649.8 KB
#CECOE : የኢትዮጵያ የሲቪል ማህበራት ድርጀቶች ኅብረት ለምርጫ (ኅብረት ለምርጫ) በወላይታ ዞን የተካሄደውን የድጋሚ ሕዝበ ውሳኔ የመራጮች ምዝገባና የድምጽ አሰጣጥ ሂደትን አስመልክቶ የሰጠው የመጀመሪያ ደረጃ የትዝብት ሪፖርት ልኮልናል።
በዚሁ የመጀመሪያ ደረጀ ሪፖርት ላይ ከድምፅ አሰጣጹ ጋር ተያይዞ አሳሳቢ ኹነቶች ተብለው የተዘረዘሩት ጉዳዮች ያሉ ሲሆን ከእነዚህም ውስጥ ፤ በተከለከሉ ቦታዎች ላይ የተቋቋመ የምርጫ ጣቢያዎች ፣ ያልተፈቀደላቸው ሰዎች በምርጫ ጣቢያዎች መገኘታቸው፣ የመራጮች ምዝገባ እና ድምፅ አሰጣት ሂደት የመቋረጥ ጉዳይ፣ የቁሳቁስ አለመሟላት የመሳሰሉት ይገኙበታል።
ሙሉ ሪፖርቱን ያንብቡ።
@tikvahethiopia
በዚሁ የመጀመሪያ ደረጀ ሪፖርት ላይ ከድምፅ አሰጣጹ ጋር ተያይዞ አሳሳቢ ኹነቶች ተብለው የተዘረዘሩት ጉዳዮች ያሉ ሲሆን ከእነዚህም ውስጥ ፤ በተከለከሉ ቦታዎች ላይ የተቋቋመ የምርጫ ጣቢያዎች ፣ ያልተፈቀደላቸው ሰዎች በምርጫ ጣቢያዎች መገኘታቸው፣ የመራጮች ምዝገባ እና ድምፅ አሰጣት ሂደት የመቋረጥ ጉዳይ፣ የቁሳቁስ አለመሟላት የመሳሰሉት ይገኙበታል።
ሙሉ ሪፖርቱን ያንብቡ።
@tikvahethiopia
#እንዳትደናገጡ
ነገ የሚከበረውን የኢድ-አል አድሃ (አረፋ) በዓልን ምክንያት በማድረግ ነገ ማለዳ 9 ጊዜ መድፍ እንደሚተኮስ የመከላከያ ሚኒስቴር አስታውቋል።
@tikvahethiopia
ነገ የሚከበረውን የኢድ-አል አድሃ (አረፋ) በዓልን ምክንያት በማድረግ ነገ ማለዳ 9 ጊዜ መድፍ እንደሚተኮስ የመከላከያ ሚኒስቴር አስታውቋል።
@tikvahethiopia
ማሕበር ሕውነት ደቂ ሰብ ፤ በማሳደጊያው ውስጥ ያሉትን ከ60 በላይ ህፃናት እና ከድርጅቱ ውጪ የሚኖሩ በቀጥታ ድርጅቱ ድጋፍ ያደርግላችው የነበሩ ጧሪ የሌላቸውን ኣረጋውያን በሚገባቸው ልክ ሊደረስላቸው ስላልቻለ የእኛ የልጆቻቸውን ድጋፍ ጠይቋል።
ማሕበር ሕውነት ደቂ ሰብ ጥያቄውን ያቀረበው ለመላው የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰቦችና ለቀድሞ የመቐለ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ባስተለለፈው መልዕክት ነው።
የቀድሞ የመቐለ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በመቐለ ቆይታቸው በማሕበር ሕውነት ደቂ ሰብ (Human Beings Assocations of Brothers Hood) በመመላለስ የተለያዩ ማህበራዊ ግልጋሎቶችን በመስጠት ከድርጅቱ ጎን በመቆም በብዙ ቤተሰባዊ ፍቅር መልካም ጊዜያትን ከድርጅቱ ጋር አሳልፈዋል።
አሁን ላይ ድርጅቱ በወቅታዊው ሀገራዊ ሁኔታ ምክንያት በድርጅቱ ማሳደጊያ ውስጥ ያሉ ከ60 በላይ ህፃናት እና ከድርጅቱ ውጪ የሚኖሩ በቀጥታ ድርጅቱ ድጋፍ ያደርግላችው የነበሩ ጧሪ የሌላቸውን ኣረጋውያን በሚገባቸው ልክ መደገፍ ስላልቻለ የቲክቫህ ቤተሰቦች እንዲሁም የቀድሞ የመቐለ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ድጋፍ እንዲደርጉ ጥሪ አቅርቧል።
ድጋፉ የገንዘብ እና የኣይነት መሆን ይችላል።
የገንዘብ ድጋፉን " #ሕጋዊ በሆነው " በድርጅቱ የንግድ ባንክ ኣካውንት (Human Beings Assocation of Brothers Hood 👉1000016160664 በኩል ማድረግ ይቻላል።
የኣይነት ድጋፉን በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል ማድረስ ይቻላል።
የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት ከዓመታት በፊት በፀረ ጥላቻ ንግግር ዘመቻ የሰላም ጉዞ ወቅት ማሕበር ሕውነት ደቂ ሰብን ጎብኝተው ድርጅቱ ከሚያሳድጋቸው ልጆችም ጋር ጊዜ አሳልፈው ነበር።
ይህ መልዕክት የሚደርሳችሁ የቀድሞ የመቐለ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች መልዕክቱን ለሌሎች እንድታጋሩና በምትችሉት አቅም ድጋፋችሁን እንድታደርጉ እንጠይቃለን።
@tikvahethiopia
ማሕበር ሕውነት ደቂ ሰብ ጥያቄውን ያቀረበው ለመላው የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰቦችና ለቀድሞ የመቐለ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ባስተለለፈው መልዕክት ነው።
የቀድሞ የመቐለ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በመቐለ ቆይታቸው በማሕበር ሕውነት ደቂ ሰብ (Human Beings Assocations of Brothers Hood) በመመላለስ የተለያዩ ማህበራዊ ግልጋሎቶችን በመስጠት ከድርጅቱ ጎን በመቆም በብዙ ቤተሰባዊ ፍቅር መልካም ጊዜያትን ከድርጅቱ ጋር አሳልፈዋል።
አሁን ላይ ድርጅቱ በወቅታዊው ሀገራዊ ሁኔታ ምክንያት በድርጅቱ ማሳደጊያ ውስጥ ያሉ ከ60 በላይ ህፃናት እና ከድርጅቱ ውጪ የሚኖሩ በቀጥታ ድርጅቱ ድጋፍ ያደርግላችው የነበሩ ጧሪ የሌላቸውን ኣረጋውያን በሚገባቸው ልክ መደገፍ ስላልቻለ የቲክቫህ ቤተሰቦች እንዲሁም የቀድሞ የመቐለ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ድጋፍ እንዲደርጉ ጥሪ አቅርቧል።
ድጋፉ የገንዘብ እና የኣይነት መሆን ይችላል።
የገንዘብ ድጋፉን " #ሕጋዊ በሆነው " በድርጅቱ የንግድ ባንክ ኣካውንት (Human Beings Assocation of Brothers Hood 👉1000016160664 በኩል ማድረግ ይቻላል።
የኣይነት ድጋፉን በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል ማድረስ ይቻላል።
የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት ከዓመታት በፊት በፀረ ጥላቻ ንግግር ዘመቻ የሰላም ጉዞ ወቅት ማሕበር ሕውነት ደቂ ሰብን ጎብኝተው ድርጅቱ ከሚያሳድጋቸው ልጆችም ጋር ጊዜ አሳልፈው ነበር።
ይህ መልዕክት የሚደርሳችሁ የቀድሞ የመቐለ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች መልዕክቱን ለሌሎች እንድታጋሩና በምትችሉት አቅም ድጋፋችሁን እንድታደርጉ እንጠይቃለን።
@tikvahethiopia
#MoE
ምንም እንኳን የተመራቂ ተማሪዎች " የመውጫ ፈተና " ሊሰጥ እጅግ አጭር ጊዜ የቀረው ቢሆንም እስካሁን ድረስ ፦
- ለተማሪዎቻቸው በቂ መረጃ ያላደረሱ፣
- የትና መቼ እንደሚፈተኑ ያላሳወቁ፣
- ተማሪዎቻቸው ከሚፈተኑባቸው የመንግስት ተቋማት ሥራ ኃላፊዎች ጋር ያልተወያዩ አንዳንድ የግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት መኖራቸውን እንደደረሰበት ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል።
ሚኒስቴሩ ይህን ያሳወቀው ፤ ለግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ባለቤቶችና አመራሮች ባሰራጨው አስቸኳይ መልዕክት ነው።
የመጀመሪያ ድግሪ የመውጫ ፈተና ከሐምሌ 3 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ ለመስጠት ዝግጅት መደረጉን ያስታወሰው ትምህርት ሚኒስቴር ፤ አንዳንድ ተቋማት እስካሁን ለተማሪዎቻቸው በቂ መረጃ ያላደረሱ፣ የትና መቼ እንደሚፈተኑ ያላሳወቁ፣ ተማሪዎቻቸው ከሚፈተኑባቸው የመንግስት ተቋማት ሥራ ኃላፊዎች ጋር ያልተወያዩ...ወዘተ ጉድለት እንዳለባቸው ባደረገው ክትትል እንዳወቀ ገልጿል።
እነኚህ ክፍተቶች በአጭር ጊዜ እንዲታረሙ ያሳሰበው ትምህርት ሚኒስቴር ፤ " ተማሪዎች መረጃ ባለማግኘት ለሚደርስባቸው እንግልትና ለሚከሰተው ችግር ኃላፊነቱ የተቋማቱ ነው " ሲል አስገንዝቧል።
ሚኒስቴሩ ጉድለት እንዳለባቸው በክትትል የደረሰባቸውን የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በስም አልጠቀሰም።
ተቋማቱ ለማንኛውም ድጋፍና ማብራሪያ ጡሪ ጭምዴሳ - 0911780497 ፣ ታምራት ከበደ - 0913566717 ፣ ብሩክ አሰፋ - 0913307730 ፣ አዲስ አለማየሁ- 0913715772 ፣ ፈሲል ፀጋዬ - 0911335683 የተባሉ ባለሙያዎችና ኃላፊዎች ማግኘት እንደሚችሉ ተገልጿል።
@tikvahethiopia
ምንም እንኳን የተመራቂ ተማሪዎች " የመውጫ ፈተና " ሊሰጥ እጅግ አጭር ጊዜ የቀረው ቢሆንም እስካሁን ድረስ ፦
- ለተማሪዎቻቸው በቂ መረጃ ያላደረሱ፣
- የትና መቼ እንደሚፈተኑ ያላሳወቁ፣
- ተማሪዎቻቸው ከሚፈተኑባቸው የመንግስት ተቋማት ሥራ ኃላፊዎች ጋር ያልተወያዩ አንዳንድ የግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት መኖራቸውን እንደደረሰበት ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል።
ሚኒስቴሩ ይህን ያሳወቀው ፤ ለግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ባለቤቶችና አመራሮች ባሰራጨው አስቸኳይ መልዕክት ነው።
የመጀመሪያ ድግሪ የመውጫ ፈተና ከሐምሌ 3 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ ለመስጠት ዝግጅት መደረጉን ያስታወሰው ትምህርት ሚኒስቴር ፤ አንዳንድ ተቋማት እስካሁን ለተማሪዎቻቸው በቂ መረጃ ያላደረሱ፣ የትና መቼ እንደሚፈተኑ ያላሳወቁ፣ ተማሪዎቻቸው ከሚፈተኑባቸው የመንግስት ተቋማት ሥራ ኃላፊዎች ጋር ያልተወያዩ...ወዘተ ጉድለት እንዳለባቸው ባደረገው ክትትል እንዳወቀ ገልጿል።
እነኚህ ክፍተቶች በአጭር ጊዜ እንዲታረሙ ያሳሰበው ትምህርት ሚኒስቴር ፤ " ተማሪዎች መረጃ ባለማግኘት ለሚደርስባቸው እንግልትና ለሚከሰተው ችግር ኃላፊነቱ የተቋማቱ ነው " ሲል አስገንዝቧል።
ሚኒስቴሩ ጉድለት እንዳለባቸው በክትትል የደረሰባቸውን የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በስም አልጠቀሰም።
ተቋማቱ ለማንኛውም ድጋፍና ማብራሪያ ጡሪ ጭምዴሳ - 0911780497 ፣ ታምራት ከበደ - 0913566717 ፣ ብሩክ አሰፋ - 0913307730 ፣ አዲስ አለማየሁ- 0913715772 ፣ ፈሲል ፀጋዬ - 0911335683 የተባሉ ባለሙያዎችና ኃላፊዎች ማግኘት እንደሚችሉ ተገልጿል።
@tikvahethiopia
#እንድታውቁት #AddisAbaba
ከለሊት 11:30 ጀምሮ መንገዶች ይዘጋሉ።
1444ኛው የኢድ አል አድሃ (አረፋ) በዓል ነገ ይከበራል፡፡
በዓሉን አስመልክቶ በ " አዲስ አበባ ስታዲዮም " ሃይማኖታዊ ስነ-ስርአት የሚካሄድ ሲሆን ይህ ስነስርዳት ተጀምሮ እሰከሚጠናቀቀ የትራፊክ መጨናነቅ እንደይፈጠር ለተሸከርካሪ ዝግ የሚሆኑ መንገዶችን አዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታውቋል፡፡
የሚዘጉ መንገዶች ፦
- ከፒያሳ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው ዋናው መንገድ ቴድሮስ አደባባይ
- ከጎተራ ፣ አጎና ሲኒማ ፣ ሪቼ የሚወስደው መንገድ ለከባድ ተሽከርካሪዎች አጎና ሲኒማ እንዲሁም ለአነስተኛ ተሽከርካሪዎች ጥላሁን አደባባይ ወይም የቀድሞ 4ኛ ክፍለ ጦር ጋር
- ከኬኬር ህንፃ ጀርባ ወደ ለገሃር የሚወስደው መንገድ የድሮ ለገሃር ግምሩክ
- ከከፍተኛ ፍርድ ቤት ፣ በፖሊስ ሆስፒታል ወደ ሜክሲኮ የሚወስደው መንገድ አል ሳም ጨለቅለቅ በስርና በላይ መንገድ
- ከጎማ ቁጠባ ወደ ለገሃር የሚወስደው መንገድ ሰንጋ ተራ 40/60 የጋራ መኖሪያ ቤት አካባቢ
- ከጎማ ቁጠባ ወደ ብሔራዊ ቴአትር የሚወስደው መንገድ ጎማ ቁጠባ መብራት
- ከሜትሮሎጂ በጥቁር አንበሳ ወደ ፖስታ ቤት የሚወስደው መንገድ ሜትሮሎጂ መ/ቤት
- ከንግድ ማተሚያ ቤት ወደ ኦርማ ጋራዥ የሚወስደው መንገድ ንግድ ማተሚያ ቤት
- ከአራት ኪሎ እና ከእሪ በከንቱ የሚመጡ መንገዶች ፓርላማ መብራት ጋር
- ከሲግናል ወደ ካዛንቺስ የሚወስደው መንገድ ሴቶች አደባባይ
- ከቦሌ አየር መንገድ በሚሊኒዬም አዳራሽ ወደ ስታዲዩም የሚወስደው መንገድ ኦሎምፒያ ወይም ደንበል ሲቲ ሴንተር
- ከመገናኛ ፣ በሃያ ሁለት ወደ መስቀል አደባባይ እንዲሁም ከቦሌ መድሃኒያለም፣ በአትላስ ሆቴል ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ቅድስ ዑራኤል ቤተ-ክርስቲያን መስቀለኛ ላይ ከላይና ከታች
- ከተክለ ኃይማኖት ፣ በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ኢሚግሬሽን የሚወስደው መንገድ ጥቁር አንበሳ ሼል
- ከተክለ ሃይማኖት ጎላ ሚካኤል የሚወስደው መንገድ ጎላ ሚካኤል መስቀለኛ
- ከጎፋ ፣ በቅዱስ ቂርቆስ ቤ/ክ ወደ ለገሐር የሚወስደው አዲሱ መንገድ ቅዱስ ቂርቆስ ቤ/ክ መስቀለኛው ይለፍ ለሌላቸው ተሽከርካሪዎች ከለሊት 11፡00 ሰዓት ጀምሮ ዝግጅቱ እስከሚጠናቀቅ ድረስ ዝግ ይሆናሉ፡፡
ህብረተሰቡ ከፖሊስ የተሰጠውን መረጃ ተገንዝቦ የትራፊክ ፖሊስ አባላት በሚጠቁሙት አማራጭ መንገዶችን እንዲጠቀም ጥሪ ቀርቧል።
NB. የእምንቱ ተከታዮች በዓሉን ለማክበር ወደ አዲስ አበባ ስታዲዮም ሲመጡ ለጋራ ደህንነት ሲባል ፍተሻ መኖሩን ተረድተው እንደወትሮው ሁሉ ትብብር እንዲያደርጉ ተጠይቋል።
ማንኛውም አጠራጣሪ ነገሮች ሲያጋጥሙ ወይም የፖሊስ አገልግሎት ለማግኘት በአዲስ አበባ ፖሊስ የመረጃ ስልኮች 011-1 11-01-11 ወይም በነፃ የስልክ መስመር 991 መረጃ መስጠት ይቻላል።
@tikvahethiopia
ከለሊት 11:30 ጀምሮ መንገዶች ይዘጋሉ።
1444ኛው የኢድ አል አድሃ (አረፋ) በዓል ነገ ይከበራል፡፡
በዓሉን አስመልክቶ በ " አዲስ አበባ ስታዲዮም " ሃይማኖታዊ ስነ-ስርአት የሚካሄድ ሲሆን ይህ ስነስርዳት ተጀምሮ እሰከሚጠናቀቀ የትራፊክ መጨናነቅ እንደይፈጠር ለተሸከርካሪ ዝግ የሚሆኑ መንገዶችን አዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታውቋል፡፡
የሚዘጉ መንገዶች ፦
- ከፒያሳ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው ዋናው መንገድ ቴድሮስ አደባባይ
- ከጎተራ ፣ አጎና ሲኒማ ፣ ሪቼ የሚወስደው መንገድ ለከባድ ተሽከርካሪዎች አጎና ሲኒማ እንዲሁም ለአነስተኛ ተሽከርካሪዎች ጥላሁን አደባባይ ወይም የቀድሞ 4ኛ ክፍለ ጦር ጋር
- ከኬኬር ህንፃ ጀርባ ወደ ለገሃር የሚወስደው መንገድ የድሮ ለገሃር ግምሩክ
- ከከፍተኛ ፍርድ ቤት ፣ በፖሊስ ሆስፒታል ወደ ሜክሲኮ የሚወስደው መንገድ አል ሳም ጨለቅለቅ በስርና በላይ መንገድ
- ከጎማ ቁጠባ ወደ ለገሃር የሚወስደው መንገድ ሰንጋ ተራ 40/60 የጋራ መኖሪያ ቤት አካባቢ
- ከጎማ ቁጠባ ወደ ብሔራዊ ቴአትር የሚወስደው መንገድ ጎማ ቁጠባ መብራት
- ከሜትሮሎጂ በጥቁር አንበሳ ወደ ፖስታ ቤት የሚወስደው መንገድ ሜትሮሎጂ መ/ቤት
- ከንግድ ማተሚያ ቤት ወደ ኦርማ ጋራዥ የሚወስደው መንገድ ንግድ ማተሚያ ቤት
- ከአራት ኪሎ እና ከእሪ በከንቱ የሚመጡ መንገዶች ፓርላማ መብራት ጋር
- ከሲግናል ወደ ካዛንቺስ የሚወስደው መንገድ ሴቶች አደባባይ
- ከቦሌ አየር መንገድ በሚሊኒዬም አዳራሽ ወደ ስታዲዩም የሚወስደው መንገድ ኦሎምፒያ ወይም ደንበል ሲቲ ሴንተር
- ከመገናኛ ፣ በሃያ ሁለት ወደ መስቀል አደባባይ እንዲሁም ከቦሌ መድሃኒያለም፣ በአትላስ ሆቴል ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ቅድስ ዑራኤል ቤተ-ክርስቲያን መስቀለኛ ላይ ከላይና ከታች
- ከተክለ ኃይማኖት ፣ በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ኢሚግሬሽን የሚወስደው መንገድ ጥቁር አንበሳ ሼል
- ከተክለ ሃይማኖት ጎላ ሚካኤል የሚወስደው መንገድ ጎላ ሚካኤል መስቀለኛ
- ከጎፋ ፣ በቅዱስ ቂርቆስ ቤ/ክ ወደ ለገሐር የሚወስደው አዲሱ መንገድ ቅዱስ ቂርቆስ ቤ/ክ መስቀለኛው ይለፍ ለሌላቸው ተሽከርካሪዎች ከለሊት 11፡00 ሰዓት ጀምሮ ዝግጅቱ እስከሚጠናቀቅ ድረስ ዝግ ይሆናሉ፡፡
ህብረተሰቡ ከፖሊስ የተሰጠውን መረጃ ተገንዝቦ የትራፊክ ፖሊስ አባላት በሚጠቁሙት አማራጭ መንገዶችን እንዲጠቀም ጥሪ ቀርቧል።
NB. የእምንቱ ተከታዮች በዓሉን ለማክበር ወደ አዲስ አበባ ስታዲዮም ሲመጡ ለጋራ ደህንነት ሲባል ፍተሻ መኖሩን ተረድተው እንደወትሮው ሁሉ ትብብር እንዲያደርጉ ተጠይቋል።
ማንኛውም አጠራጣሪ ነገሮች ሲያጋጥሙ ወይም የፖሊስ አገልግሎት ለማግኘት በአዲስ አበባ ፖሊስ የመረጃ ስልኮች 011-1 11-01-11 ወይም በነፃ የስልክ መስመር 991 መረጃ መስጠት ይቻላል።
@tikvahethiopia