TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.1K photos
1.58K videos
216 files
4.31K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
CECOE-2021-Voter-Registration-Observation-Report.pdf
238.2 KB
#CECOE

ከ175 በላይ በምርጫ ዙርያ የተለያዩ ስራዎችን የሚሰሩ አገር በቀል የሲቪል ማህበራትን ያካተተው የኢትዮጵያ የሲቪል ማህበራት ድርጅቶች ህብረት ለምርጫ (CECOE) ከሚያዝያ 2 ቀን እስከ ግንቦት 13 ቀን 2013 ዓ.ም ድረስ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች የመራጮች ምዝገባን ታዝቦ ሪፖርቱን አቅርቧል።

ህብረቱ ስልጠና ሰጥቶ ያሰማራቸው 117 ታዛቢዎች ከላይ በተጠቀሱት ቀናት በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ተዘዋውረው 1,190 የምርጫ ምዝገባ ጣቢያዎች ላይ የታዘቡ ሲሆን ሪፖርቱ በእነዚህ ጣቢያዎች ላይ የተመሰረተ መሆኑን ገልጿል።

ሪፖርቱ ከ45,000 በላይ የመራጮች ምዝገባ ጣቢያዎችን በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች ከመክፈት አንስቶ ወደ 135,000 የሚጠጉ አስፈፃሚዎችን አሰልጥኖ እስከማሰማራት ድረስ ቦርዱ በአጭር ጊዜ ውስጥ የሰራው ስራ በመልካም ጐኑ የሚጠቀስ ነው ብሏል።

''ምንም እንኳን የመራጮች ምዝገባን የማደራጀትና የማካሄድ ተግባርን ውስብስብነት ህብረቱ ቢረዳም በምዝገባ ሂደቱ ወቅት የበርካታ ኢትዮጵያውያንን የመምረጥ መብት ሊያጣብቡ የሚችሉ ችግሮች መከሰታቸውን መካድ ግን አይቻልም'' ሲል ሪፖርቱ ይጠቅሳል።

* ሙሉ ሪፖርቱ ከላይ ተያይዟል።

@tikvahethiopia
Preliminary_Report_by_CECOE_Referendum_rerun_in_the_Wolaita_zone.pdf
649.8 KB
#CECOE : የኢትዮጵያ የሲቪል ማህበራት ድርጀቶች ኅብረት ለምርጫ (ኅብረት ለምርጫ) በወላይታ ዞን የተካሄደውን የድጋሚ ሕዝበ ውሳኔ የመራጮች ምዝገባና የድምጽ አሰጣጥ ሂደትን አስመልክቶ የሰጠው የመጀመሪያ ደረጃ የትዝብት ሪፖርት ልኮልናል።

በዚሁ የመጀመሪያ ደረጀ ሪፖርት ላይ ከድምፅ አሰጣጹ ጋር ተያይዞ አሳሳቢ ኹነቶች ተብለው የተዘረዘሩት ጉዳዮች ያሉ ሲሆን ከእነዚህም ውስጥ ፤ በተከለከሉ ቦታዎች ላይ የተቋቋመ የምርጫ ጣቢያዎች ፣ ያልተፈቀደላቸው ሰዎች በምርጫ ጣቢያዎች መገኘታቸው፣ የመራጮች ምዝገባ እና ድምፅ አሰጣት ሂደት የመቋረጥ ጉዳይ፣ የቁሳቁስ አለመሟላት የመሳሰሉት ይገኙበታል።

ሙሉ ሪፖርቱን ያንብቡ።

@tikvahethiopia