#እንድታውቁት
(የገቢዎች ሚኒስቴር)
ክሊራንስ ለመስጠት ኦዲት #የማያስፈልጋቸው አገልግሎቶች ፦
ከዚህ በታች ለተዘረዘሩት አገልግሎቶች ታክስ ከፋዩን ኦዲት ማድረግ ሳያስፈልግ የታክስ ክሊራንስ የምስክር ወረቀት ሊሰጥ ይችላል:-
- ንግድ ሥራ ፍቃድ ወይም የሙያ ፍቃድ ለማደስ፤
- ጨረታ ለመካፈል ወይም ለመሳተፍ፤
- ለተሽከርካሪዎች ወይም ለኮንስትራክሽን ማሽነሪዎች ዓመታዊ ምዝገባና ምርመራ (ክላውዶ) ለማድረግ፤
- የባንክ ብድር ለማግኘት፤
- የመድን ካሳ ለማግኘትና የተሽከርካሪ ሰሌዳ ለውጥ ለማድረግ፤
- የድርጅት ስም ወይም አድራሻ ለመለወጥ፤
- የንግድ ሥራ ሀብት መቀነስን ሳይጨምር የንግድ ዘርፍ ቅነሳ ለማድረግ፤
- ድርጅቶች እንደገና ተደራጅተው ሲዋሀዱ የተዋሀደውን ድርጅት የታክስ ዕዳ አካቶ የሚዋሃዱ ስለመሆኑ የፀደቀ ሰነድ ለማቅረብ፤
1. የክሊራንስ ጥያቄ በቀረበበት ጊዜ የታክስ ውሳኔ ማስታወቂያ የተሰጠው እና ያልተከፈለ የታክስ ዕዳ ያለበት ታክስ ከፋይ ኦዲት ሳይደረግ የባንክ ብድር እንዲወስድ ክሊራንስ የሚሰጠው ዕዳውን የከፈለ እንደሆነ ወይም ለመክፈል የባንክ ዋስትና ያቀረበ እንደሆነ ብቻ ነው፡፡
2. ታክስ ከፋዩ የታክስ ክሊራንስ ምስክር ወረቀት ሊሰጠው የሚችለው:-
• ታክስ ከፋዩ ዓመታዊ የንግድ ትርፍ ግብር ማስታወቂያ እና መክፈያ የመጨረሻ ቀን ከመድረሱ በፊት የንግድ ሥራ ፍቃድ ለማደስ፣ በጨረታ ለመሳተፍ፣ የባንክ ብድር ለመውሰድ እና የጉዳት ካሳ ለማግኘት የሚቀርብ የታክስ ክራንስ ምስክር ወረቀት ጥያቄ ከሆነ ጥያቄው ከቀረበበት የግብር ዘመን በፊት ታክሱን አስታውቆ ግዴታውን የተወጣ ስለመሆኑ እና
• የታክስ ክራንስ ምስክር ወረቀት የተጠየቀበትን አገልግሎት ዓይነትና የተፈለገበትን ምክንያት የሚያስረዳ ማስረጃ ሲያቀርብ ብቻ ይሆናል፡፡
3. የባንክ ብድር ለማግኘት የታክስ ክሊራንስ ምስክር ወረቀት እንዲሰጠው ለጠየቀ ሰው የታክስ ክሊራንስ ምስክር ወረቀት የሚሰጠው ጥያቄ አቅራቢው የንግድ ሥራ ያልሠራና በግብር ከፋይነት ያልተመዘገበ ከሆነ ከታክስ መስሪያ ቤቱ አነስተኛ ግብር ከፋዮች ቅ/ጽ/ቤት ከመረጃ ቋት ተገቢውን ማጣራት አድርጎ ጠያቂው በንግድ ሥራ አለመሠማራቱን በማረጋገጥ ይሆናል፡፡
4. የንግድ ሥራ ፍቃድ ለመመለስ ጥያቄ ሲያቀርቡ ከታክስ ሚኒስቴሩ የሥራ ክፍሎች እና ከሶስተኛ ወገን በማጣራት የታክስ ክሊራንስ ምስክር ወረቀት የሚሰጥ ይሆናል፡፡
Credit : የገቢዎች ሚኒስቴር
@tikvahethiopia
(የገቢዎች ሚኒስቴር)
ክሊራንስ ለመስጠት ኦዲት #የማያስፈልጋቸው አገልግሎቶች ፦
ከዚህ በታች ለተዘረዘሩት አገልግሎቶች ታክስ ከፋዩን ኦዲት ማድረግ ሳያስፈልግ የታክስ ክሊራንስ የምስክር ወረቀት ሊሰጥ ይችላል:-
- ንግድ ሥራ ፍቃድ ወይም የሙያ ፍቃድ ለማደስ፤
- ጨረታ ለመካፈል ወይም ለመሳተፍ፤
- ለተሽከርካሪዎች ወይም ለኮንስትራክሽን ማሽነሪዎች ዓመታዊ ምዝገባና ምርመራ (ክላውዶ) ለማድረግ፤
- የባንክ ብድር ለማግኘት፤
- የመድን ካሳ ለማግኘትና የተሽከርካሪ ሰሌዳ ለውጥ ለማድረግ፤
- የድርጅት ስም ወይም አድራሻ ለመለወጥ፤
- የንግድ ሥራ ሀብት መቀነስን ሳይጨምር የንግድ ዘርፍ ቅነሳ ለማድረግ፤
- ድርጅቶች እንደገና ተደራጅተው ሲዋሀዱ የተዋሀደውን ድርጅት የታክስ ዕዳ አካቶ የሚዋሃዱ ስለመሆኑ የፀደቀ ሰነድ ለማቅረብ፤
1. የክሊራንስ ጥያቄ በቀረበበት ጊዜ የታክስ ውሳኔ ማስታወቂያ የተሰጠው እና ያልተከፈለ የታክስ ዕዳ ያለበት ታክስ ከፋይ ኦዲት ሳይደረግ የባንክ ብድር እንዲወስድ ክሊራንስ የሚሰጠው ዕዳውን የከፈለ እንደሆነ ወይም ለመክፈል የባንክ ዋስትና ያቀረበ እንደሆነ ብቻ ነው፡፡
2. ታክስ ከፋዩ የታክስ ክሊራንስ ምስክር ወረቀት ሊሰጠው የሚችለው:-
• ታክስ ከፋዩ ዓመታዊ የንግድ ትርፍ ግብር ማስታወቂያ እና መክፈያ የመጨረሻ ቀን ከመድረሱ በፊት የንግድ ሥራ ፍቃድ ለማደስ፣ በጨረታ ለመሳተፍ፣ የባንክ ብድር ለመውሰድ እና የጉዳት ካሳ ለማግኘት የሚቀርብ የታክስ ክራንስ ምስክር ወረቀት ጥያቄ ከሆነ ጥያቄው ከቀረበበት የግብር ዘመን በፊት ታክሱን አስታውቆ ግዴታውን የተወጣ ስለመሆኑ እና
• የታክስ ክራንስ ምስክር ወረቀት የተጠየቀበትን አገልግሎት ዓይነትና የተፈለገበትን ምክንያት የሚያስረዳ ማስረጃ ሲያቀርብ ብቻ ይሆናል፡፡
3. የባንክ ብድር ለማግኘት የታክስ ክሊራንስ ምስክር ወረቀት እንዲሰጠው ለጠየቀ ሰው የታክስ ክሊራንስ ምስክር ወረቀት የሚሰጠው ጥያቄ አቅራቢው የንግድ ሥራ ያልሠራና በግብር ከፋይነት ያልተመዘገበ ከሆነ ከታክስ መስሪያ ቤቱ አነስተኛ ግብር ከፋዮች ቅ/ጽ/ቤት ከመረጃ ቋት ተገቢውን ማጣራት አድርጎ ጠያቂው በንግድ ሥራ አለመሠማራቱን በማረጋገጥ ይሆናል፡፡
4. የንግድ ሥራ ፍቃድ ለመመለስ ጥያቄ ሲያቀርቡ ከታክስ ሚኒስቴሩ የሥራ ክፍሎች እና ከሶስተኛ ወገን በማጣራት የታክስ ክሊራንስ ምስክር ወረቀት የሚሰጥ ይሆናል፡፡
Credit : የገቢዎች ሚኒስቴር
@tikvahethiopia
#AddisAbaba
" የፈተና ህትመት ደህንነቱን በጠበቀ መልኩ #ከፌደራል_ፖሊስ ጋር በመተባበር በቁጥጥር እየተሰራ ነው " - የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ
በአዲስ አበባ ከተማ ለሚሰጠው የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና በቂ ዝግጅቶች መደረጋቸውን የከተማው ትምህርት ቢሮ አሳውቋል።
የፈተና ህትመት ደህንነቱን በጠበቀ መልኩ ከፌደራል ፖሊስ ጋር በመተባበር በቁጥጥር እየተሰራ እንዳለ ተጠቁሟል።
በዘንድሮው ከተማ አቀፍ ፈተና በ8ኛ ክፍል 75100 ተማሪዎች በ766 ት/ቤቶች እንዲሁም በ6ኛ ክፍል 75090 ተማሪዎች በ788 ትምህርት ቤቶች በመደበኛ በማታና በግል ለመፈተን ምዝገባ ማካሔዳቸውን ተነግሯል።
ከተማ አቀፍ ፈተናውን በብቃት ለመስጠት ትምህርት ቢሮው በቂ ዝግጅት ማድረጉን ያሳወቀ ሲሆን የፈተና ጣቢያ ሃላፊዎች ሱፐርቫይዘሮችና ፈታኞችም ፈተናውን በስኬት ለማጠናቀቅ ሀላፊነታቸውን እንዲወጡ ማሳሰቢያ ተሰጥቷል።
በቀጣይ በከተማዋ 53,535 የሚሆኑ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ለሀገር አቀፍ ፈተና እንደሚቀርቡ ከከተማው የትምህርት ቢሮ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
@tikvahethiopia
" የፈተና ህትመት ደህንነቱን በጠበቀ መልኩ #ከፌደራል_ፖሊስ ጋር በመተባበር በቁጥጥር እየተሰራ ነው " - የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ
በአዲስ አበባ ከተማ ለሚሰጠው የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና በቂ ዝግጅቶች መደረጋቸውን የከተማው ትምህርት ቢሮ አሳውቋል።
የፈተና ህትመት ደህንነቱን በጠበቀ መልኩ ከፌደራል ፖሊስ ጋር በመተባበር በቁጥጥር እየተሰራ እንዳለ ተጠቁሟል።
በዘንድሮው ከተማ አቀፍ ፈተና በ8ኛ ክፍል 75100 ተማሪዎች በ766 ት/ቤቶች እንዲሁም በ6ኛ ክፍል 75090 ተማሪዎች በ788 ትምህርት ቤቶች በመደበኛ በማታና በግል ለመፈተን ምዝገባ ማካሔዳቸውን ተነግሯል።
ከተማ አቀፍ ፈተናውን በብቃት ለመስጠት ትምህርት ቢሮው በቂ ዝግጅት ማድረጉን ያሳወቀ ሲሆን የፈተና ጣቢያ ሃላፊዎች ሱፐርቫይዘሮችና ፈታኞችም ፈተናውን በስኬት ለማጠናቀቅ ሀላፊነታቸውን እንዲወጡ ማሳሰቢያ ተሰጥቷል።
በቀጣይ በከተማዋ 53,535 የሚሆኑ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ለሀገር አቀፍ ፈተና እንደሚቀርቡ ከከተማው የትምህርት ቢሮ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
@tikvahethiopia
#Update
የትምህርት ሚኒስቴር በትግራይ ክልል በጦርነቱ ምክንያት ሥራ አቁመው የነበሩ ዩኒቨርሲቲዎች ከአክሱም ዩኒቨርሲቲ በስተቀር ከአንድ ወር በኃላ ነባር ተማሪዎቻቸውን እንደሚቀበሉ ከመስከረም (2016) ጀምሮ ደግሞ #ሙሉ_ለሙሉ ሥራ እንደሚጀምሩ አስታውቋል።
የሚኒስቴሩ የአስተዳደርና ልማት መሪ ሥራ አስፈጻሚ ሰለሞን አብርሀ (ዶ/ር) ለኢፕድ የሰጡት ቃል ፦
" ከአክሱም ዩኒቨርሲቲ በስተቀር ሦስቱ ዩኒቨርሲቲዎች በመጭው ወር ነባር ተማሪዎችን መቀበል ይጀምራሉ።
በመጪው ዓመት በትግራይ ክልል የሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎችን ወደ መደበኛ የመማር ማስተማር ሂደት ለማስገባት ዝግጅት እየተደረገ ነው።
ዩኒቨርሲቲዎቹን ወደ ሥራ ለማስገባት የትምህርት ሚኒስቴር ዩኒቨርሲቲዎቹ ያሉበት ሁኔታ ከዩኒቨርሲቲዎቹ አመራሮች ጋር በመቐለ ተደጋጋሚ ውይይት አድርጓል።
ሥራ ለማስጀመር የሚያስችሉ ሥራዎችን ለመስራት ወደ ተግባር ተገብቷል።
ዩኒቨርሲቲዎቹ የመማር ማስተማር ሂደት ከመጀመራቸው በፊት ፦
- የምግብ ፣
- የመኝታ፣
- የሕክምና አገልግሎቶች ቅድሚያ የሚያሟሉበት ሁኔታ እየተመቻቸ ነው።
ራያ ዩኒቨርሲቲም ይህንን አሟልቶ በትናንትናው ዕለት የተማሪዎች ምዝገባ ጀምሯል።
መቐለና ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲዎች ደግሞ በቀጣይ ወር ትምህርት መጀመር የሚያስችላቸውን ተግባር ጨርሰው ተማሪዎችን መቀበል እንደሚጀምሩ ይጠበቃል።
አክሱም ዩኒቨርሲቲ ከሌሎቹ ዩኒቨርሲቲዎች በበለጠ በጦርነቱ ጉዳት በማስተናገዱ የተወሰነ ጊዜ ሊዘገይ ይችላል።
አራቱ ዩኒቨርሲቲዎች ከጦርነቱ በፊት 45 ሺሕ ተማሪዎችን ሲያስተምሩ ነበር። ከእነዚህ ውስጥም ባለፉት ዓመታት 22 ሺሕ የሚሆኑ ተማሪዎች እንዲወጡ ተደርጎ በጊዜያዊነት ወደ ሌላ ዩኒቨርሲቲ ተመድበው ትምህርታቸውን እንዲከታተሉ ተደርጓል።
እነዚህ ዩኒቨርሲቲዎችም አሁን ላይ ቅበላ የሚያደርጉት ወደ ሌላ ዩኒቨርሲቲ ሳይመደቡ የቆዩ 20 ሺሕ የሚሆኑ ተማሪዎችን ነው።
በመጪው አገር አቀፍ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ወስደው የሚያልፉ ተማሪዎችም የዩኒቨርሲቲዎቹ ዝግጁነት ተጠንቶና ታይቶ ተማሪዎች ሊመደቡባቸው ይችላል።
ከዚህ ቀደም በትግራይ ክልል ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የነበሩና ወደ ሌላ ዩኒቨርሲቲ ሄደው ያጠናቀቁ ተማሪዎች ውጤታቸውን የሚገልጽ የትምህርት ማስረጃ ሳያገኙ መቆየታቸውን ይታወሳል ፤ አሁን ላይ ከነበሩበት ዩኒቨርሲቲ ያገኙት ውጤት ወደ ትግራይ ዩኒቨርሲቲዎች እንዲላክ አቅጣጫ ተቀምጧል።
ዩኒቨርሲቲዎቹም ውጤቱ ሲደርሳቸው የነበራቸውን ውጤት ደምረው ጥቅል ውጤታቸውን የሚገልጽ ጊዜያዊ ዲግሪ ማግኘት ይችላሉ። "
Via EPA
@tikvahethiopia
የትምህርት ሚኒስቴር በትግራይ ክልል በጦርነቱ ምክንያት ሥራ አቁመው የነበሩ ዩኒቨርሲቲዎች ከአክሱም ዩኒቨርሲቲ በስተቀር ከአንድ ወር በኃላ ነባር ተማሪዎቻቸውን እንደሚቀበሉ ከመስከረም (2016) ጀምሮ ደግሞ #ሙሉ_ለሙሉ ሥራ እንደሚጀምሩ አስታውቋል።
የሚኒስቴሩ የአስተዳደርና ልማት መሪ ሥራ አስፈጻሚ ሰለሞን አብርሀ (ዶ/ር) ለኢፕድ የሰጡት ቃል ፦
" ከአክሱም ዩኒቨርሲቲ በስተቀር ሦስቱ ዩኒቨርሲቲዎች በመጭው ወር ነባር ተማሪዎችን መቀበል ይጀምራሉ።
በመጪው ዓመት በትግራይ ክልል የሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎችን ወደ መደበኛ የመማር ማስተማር ሂደት ለማስገባት ዝግጅት እየተደረገ ነው።
ዩኒቨርሲቲዎቹን ወደ ሥራ ለማስገባት የትምህርት ሚኒስቴር ዩኒቨርሲቲዎቹ ያሉበት ሁኔታ ከዩኒቨርሲቲዎቹ አመራሮች ጋር በመቐለ ተደጋጋሚ ውይይት አድርጓል።
ሥራ ለማስጀመር የሚያስችሉ ሥራዎችን ለመስራት ወደ ተግባር ተገብቷል።
ዩኒቨርሲቲዎቹ የመማር ማስተማር ሂደት ከመጀመራቸው በፊት ፦
- የምግብ ፣
- የመኝታ፣
- የሕክምና አገልግሎቶች ቅድሚያ የሚያሟሉበት ሁኔታ እየተመቻቸ ነው።
ራያ ዩኒቨርሲቲም ይህንን አሟልቶ በትናንትናው ዕለት የተማሪዎች ምዝገባ ጀምሯል።
መቐለና ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲዎች ደግሞ በቀጣይ ወር ትምህርት መጀመር የሚያስችላቸውን ተግባር ጨርሰው ተማሪዎችን መቀበል እንደሚጀምሩ ይጠበቃል።
አክሱም ዩኒቨርሲቲ ከሌሎቹ ዩኒቨርሲቲዎች በበለጠ በጦርነቱ ጉዳት በማስተናገዱ የተወሰነ ጊዜ ሊዘገይ ይችላል።
አራቱ ዩኒቨርሲቲዎች ከጦርነቱ በፊት 45 ሺሕ ተማሪዎችን ሲያስተምሩ ነበር። ከእነዚህ ውስጥም ባለፉት ዓመታት 22 ሺሕ የሚሆኑ ተማሪዎች እንዲወጡ ተደርጎ በጊዜያዊነት ወደ ሌላ ዩኒቨርሲቲ ተመድበው ትምህርታቸውን እንዲከታተሉ ተደርጓል።
እነዚህ ዩኒቨርሲቲዎችም አሁን ላይ ቅበላ የሚያደርጉት ወደ ሌላ ዩኒቨርሲቲ ሳይመደቡ የቆዩ 20 ሺሕ የሚሆኑ ተማሪዎችን ነው።
በመጪው አገር አቀፍ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ወስደው የሚያልፉ ተማሪዎችም የዩኒቨርሲቲዎቹ ዝግጁነት ተጠንቶና ታይቶ ተማሪዎች ሊመደቡባቸው ይችላል።
ከዚህ ቀደም በትግራይ ክልል ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የነበሩና ወደ ሌላ ዩኒቨርሲቲ ሄደው ያጠናቀቁ ተማሪዎች ውጤታቸውን የሚገልጽ የትምህርት ማስረጃ ሳያገኙ መቆየታቸውን ይታወሳል ፤ አሁን ላይ ከነበሩበት ዩኒቨርሲቲ ያገኙት ውጤት ወደ ትግራይ ዩኒቨርሲቲዎች እንዲላክ አቅጣጫ ተቀምጧል።
ዩኒቨርሲቲዎቹም ውጤቱ ሲደርሳቸው የነበራቸውን ውጤት ደምረው ጥቅል ውጤታቸውን የሚገልጽ ጊዜያዊ ዲግሪ ማግኘት ይችላሉ። "
Via EPA
@tikvahethiopia
Forwarded from JD
#ብርሃን_ባንክ
ዛሬ በጥቂት የተከማቸ ገንዘብ አድጎ ለቁም ነገር እንዲውል ጠቀም ያለ ወለድ የሚያስገኘው የህጻናት የቁጠባ ሂሳብ አገልግሎታችን ተጠቃሚ ይሁኑ!
አዳዲስ እና ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት ከታች የሚገኙትን ሊንኮች በመጫን የማህበራዊ ድህረ-ገጾቻችንን ይቀላቀሉ !
Facebook: https://www.facebook.com/berhanbanksc
Telegram: https://t.iss.one/berhanbanksc
Instagram: https://www.instagram.com/berhanbanksc/
Twitter: https://twitter.com/berhanbanksc
እንደ ስማችን ብርሃን ነው ስራችን!
ዛሬ በጥቂት የተከማቸ ገንዘብ አድጎ ለቁም ነገር እንዲውል ጠቀም ያለ ወለድ የሚያስገኘው የህጻናት የቁጠባ ሂሳብ አገልግሎታችን ተጠቃሚ ይሁኑ!
አዳዲስ እና ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት ከታች የሚገኙትን ሊንኮች በመጫን የማህበራዊ ድህረ-ገጾቻችንን ይቀላቀሉ !
Facebook: https://www.facebook.com/berhanbanksc
Telegram: https://t.iss.one/berhanbanksc
Instagram: https://www.instagram.com/berhanbanksc/
Twitter: https://twitter.com/berhanbanksc
እንደ ስማችን ብርሃን ነው ስራችን!
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
" ራያ ዩኒቨርሲቲ ነባር ተማሪዎችን ተቀብሎ ምዝገባ ማካሄድ ጀምሯል፣ መቐለ እና ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ተማሪዎችን መቀበል ይጀምራሉ ፤ ኣክሱም ዩኒቨርሲቲ በሁለት ወር ጊዜ ውስጥ ተማሪዎቹን ይቀበላል " - ዶ/ር ሰለሞን አብርሃ (ለቲክቫህ ኢትዮጵያ)
ትምህርት ሚኒስቴር በትግራይ ክልል ያሉ ዩኒቨርሲቲዎች (መቐለ፣ ዓዲግራት፣ ራያ፣ ኣክሱም) ወደ መማር ማስተማር ስራቸው እንደሚመለሱ አሳወቀ።
የትምህርት ሚኒስቴር የአስተዳደርና ልማት መሪ ሥራ አስፈፃሚ ዶክተር ሰለሞን አብርሃ ፤ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በላኩት መልዕክት በክልሉ ያሉ ዩኒቨርሲቲዎች ወደ መማር ማስተማር ስራቸው እንዲመለሱ ለማድረግ ስራዎች ሲሰሩ መቆየታቸውን ገልጸዋል።
በዚህም ራያ ዩኒቨርሲቲ ከትላንት ጀምሮ ነባር ተማሪዎችን በመቀበል ምዝገባ መጀመሩን አሳውቀውናል።
መቐለ እና ዓዲግራት ዩኒቨርሲቱ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ነባር ተማሪዎቻቸውን መቀበል እንደሚጀምሩ የገለፁልን ዶ/ር ሰለሞን፤ የኣክሱም ዩኒቨርሲቲ ደግሞ በሁለት ወር ጊዜ ውስጥ ተማሪዎቹን መቀበል እንደሚጀምር አሳውቀውናል።
የኣክሱም ዩኒቨርሲቲ ከሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች በበለጠ በጦርነት መጎዳቱ የመዘግየቱ ምክንያት መሆኑን አስረድተውናል።
ዩኒቨርሲቲዎቹ ቅበላ የሚያደርጉት ወደ ሌላ ዩኒቨርሲቲ ሳይመደቡ የቆዩ ተማሪዎችን መሆኑን ዶ/ር ሰለሞን ገልጸውልናል።
በመጪው አገር አቀፍ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ወስደው የሚያልፉ ተማሪዎች የዩኒቨርሲቲዎቹ ዝግጁነት ተጠንቶና ታይቶ ተማሪዎች ሊመደቡባቸው ይችላል ብለዋል።
በትግራይ ክልል ያሉ ሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች ከመስከረም 2016 ዓ/ም ጀምሮ #ሙሉ_በሙሉ ወደ ስራ እንደሚገቡ ዶ/ር ሰለሞን አብርሃ በላኩልን መልዕክት አስረድተዋል።
@tikvahethiopia
ትምህርት ሚኒስቴር በትግራይ ክልል ያሉ ዩኒቨርሲቲዎች (መቐለ፣ ዓዲግራት፣ ራያ፣ ኣክሱም) ወደ መማር ማስተማር ስራቸው እንደሚመለሱ አሳወቀ።
የትምህርት ሚኒስቴር የአስተዳደርና ልማት መሪ ሥራ አስፈፃሚ ዶክተር ሰለሞን አብርሃ ፤ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በላኩት መልዕክት በክልሉ ያሉ ዩኒቨርሲቲዎች ወደ መማር ማስተማር ስራቸው እንዲመለሱ ለማድረግ ስራዎች ሲሰሩ መቆየታቸውን ገልጸዋል።
በዚህም ራያ ዩኒቨርሲቲ ከትላንት ጀምሮ ነባር ተማሪዎችን በመቀበል ምዝገባ መጀመሩን አሳውቀውናል።
መቐለ እና ዓዲግራት ዩኒቨርሲቱ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ነባር ተማሪዎቻቸውን መቀበል እንደሚጀምሩ የገለፁልን ዶ/ር ሰለሞን፤ የኣክሱም ዩኒቨርሲቲ ደግሞ በሁለት ወር ጊዜ ውስጥ ተማሪዎቹን መቀበል እንደሚጀምር አሳውቀውናል።
የኣክሱም ዩኒቨርሲቲ ከሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች በበለጠ በጦርነት መጎዳቱ የመዘግየቱ ምክንያት መሆኑን አስረድተውናል።
ዩኒቨርሲቲዎቹ ቅበላ የሚያደርጉት ወደ ሌላ ዩኒቨርሲቲ ሳይመደቡ የቆዩ ተማሪዎችን መሆኑን ዶ/ር ሰለሞን ገልጸውልናል።
በመጪው አገር አቀፍ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ወስደው የሚያልፉ ተማሪዎች የዩኒቨርሲቲዎቹ ዝግጁነት ተጠንቶና ታይቶ ተማሪዎች ሊመደቡባቸው ይችላል ብለዋል።
በትግራይ ክልል ያሉ ሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች ከመስከረም 2016 ዓ/ም ጀምሮ #ሙሉ_በሙሉ ወደ ስራ እንደሚገቡ ዶ/ር ሰለሞን አብርሃ በላኩልን መልዕክት አስረድተዋል።
@tikvahethiopia
Forwarded from Commercial Bank of Ethiopia - Official
ሲቢኢ ጉዞ የቁጠባ ሂሳብ
=================
ደንበኞች በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭ ሀገራት ለሚያደርጉት ጉዞ ወጪ መሸፈኛ ገንዘብ አስቀድመው መቆጠብ እንዲችሉ የተዘጋጀ የቁጠባ ሂሳብ ነው፡፡
ሲቢኢ ጉዞ የቁጠባ ሂሳብ ከብር 1,000 ጀምሮ ይከፈታል፡፡
የቁጠባ ሂሳቡ የተለያዩ ጥቅሞች ያስገኛል፡፡
• ቆጣቢዎች በሀገር ወስጥ ጉዟቸው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክን ዲጂታል የክፍያ አማራጮች ተጠቅመው ለአየር ትኬት፣ ለቱሪስት መዳረሻዎች መግቢያ፣ ለሆቴል አገልግሎት እና ለመሳሰሉት ክፍያ በሚፈፅሙበት ወቅት ተመላሽ ያገኛሉ፤
• ዳያስፖራ ወይም የውጭ ሀገር ዜጎች የሲቢኢ ቱሪስት ካርድን ሲጠቀሙ እስከ 7 በመቶ የሚደርስ ተመላሽ ያገኛሉ ፤
• ለሀይማኖታዊ ጉዳይ ወደ ውጭ ሀገራት የሚጓዙ ደንበኞች ከአየር ትኬት ክፍያቸው እስከ 3 በመቶ የሚደርስ ተመላሽ ያገኛሉ፤
• ሌሎች ተጨማሪ ጥቅሞችንም ያስገኛል፡፡
ሂሳቡን በአቅራቢያዎ በሚገኝ ቅርንጫፍ ይክፈቱ፤ ለበለጠ መረጃ ወደ 951 ይደውሉ!
ይቆጥቡ፤ ይጓዙ!
=================
ደንበኞች በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭ ሀገራት ለሚያደርጉት ጉዞ ወጪ መሸፈኛ ገንዘብ አስቀድመው መቆጠብ እንዲችሉ የተዘጋጀ የቁጠባ ሂሳብ ነው፡፡
ሲቢኢ ጉዞ የቁጠባ ሂሳብ ከብር 1,000 ጀምሮ ይከፈታል፡፡
የቁጠባ ሂሳቡ የተለያዩ ጥቅሞች ያስገኛል፡፡
• ቆጣቢዎች በሀገር ወስጥ ጉዟቸው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክን ዲጂታል የክፍያ አማራጮች ተጠቅመው ለአየር ትኬት፣ ለቱሪስት መዳረሻዎች መግቢያ፣ ለሆቴል አገልግሎት እና ለመሳሰሉት ክፍያ በሚፈፅሙበት ወቅት ተመላሽ ያገኛሉ፤
• ዳያስፖራ ወይም የውጭ ሀገር ዜጎች የሲቢኢ ቱሪስት ካርድን ሲጠቀሙ እስከ 7 በመቶ የሚደርስ ተመላሽ ያገኛሉ ፤
• ለሀይማኖታዊ ጉዳይ ወደ ውጭ ሀገራት የሚጓዙ ደንበኞች ከአየር ትኬት ክፍያቸው እስከ 3 በመቶ የሚደርስ ተመላሽ ያገኛሉ፤
• ሌሎች ተጨማሪ ጥቅሞችንም ያስገኛል፡፡
ሂሳቡን በአቅራቢያዎ በሚገኝ ቅርንጫፍ ይክፈቱ፤ ለበለጠ መረጃ ወደ 951 ይደውሉ!
ይቆጥቡ፤ ይጓዙ!
Forwarded from TIKVAH-ETHIOPIA
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#forfreemarket
አስፈላጊ ምርቶች ፤ ተመጣጣኝ_ዋጋ
ለተጨማሪ ማብራሪያ የቴሌግራም ገፃችን⤵️
https://t.iss.one/forfreemarket
አነስተኛ የልብስ እና ጫማ ማጠቢያ
👉ለጫማ ቢሉ ለልብስ ቦታ የማይዝ
👉 ለፓንት ቦክሰር እና ካልሲ
👉ለ ቲሸርት ሁነኛ ተመራጭ
👉ለዳይፐር
🏢 አድራሻ 👉 ፒያሳ ጣይቱ ሆቴል ጊቢ ውስጥ
📲 0911255787
📲 0983360606
ጥራት መለያችን ነው
OnLineShopping
አስፈላጊ ምርቶች ፤ ተመጣጣኝ_ዋጋ
ለተጨማሪ ማብራሪያ የቴሌግራም ገፃችን⤵️
https://t.iss.one/forfreemarket
አነስተኛ የልብስ እና ጫማ ማጠቢያ
👉ለጫማ ቢሉ ለልብስ ቦታ የማይዝ
👉 ለፓንት ቦክሰር እና ካልሲ
👉ለ ቲሸርት ሁነኛ ተመራጭ
👉ለዳይፐር
🏢 አድራሻ 👉 ፒያሳ ጣይቱ ሆቴል ጊቢ ውስጥ
📲 0911255787
📲 0983360606
ጥራት መለያችን ነው
OnLineShopping
#Oromia
የኦሮሚያ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ቶላ በሪሶ የ8ኛ ክፍል እና የ12ኛ ክፍል ፈተናዎችን አስመልክቶ ማብራሪያ መስጠታቸውን የክልሉ ትምህርት ቢሮ በማህበራዊ ትስስር ገፁ ላይ አሳውቋል።
የ2015 የ8ኛ ክፍል ፈተና እንደ ክልል የሚካሄድ ሲሆን የ12ኛ ክፍል ፈተና በሀገር አቀፍ ደረጃ እንደሚሰጥ ዶ/ር ቶላ በሪሰ ገልጸዋል
የ8ኛ ከፍል ፈተናን በተመለከተ 490,167 ተማሪዎች እንደሚወስዱ (ከዚህም ውስጥ ወንድ 260,807 እና ሴት 229,360 ናቸው) ገልጸው የ8ኛ ክፈል ፈተና የሚሰጥበት ቀን ሰኔ 26 እና 27/2015 መሆኑን አሳውቀዋል።
የ12ኛ ክፈል ብሄራዊ ፈተናን አስመልክቶ በክልሉ 323,149 ተማሪዎች ለፈተናው እንደሚቀመጡ ገልጸው የፈተና ፕሮግራሙን እንደሚከተለው አብራርተዋል።
የፈተናው ፕሮግራም ፦
👉 ለማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች
- ሐምሌ 16 -17 / 2015 ወደ ተመደቡበት ዩኒቨርሲቲ ይገባሉ።
- ሐምሌ 18 የፈተና ኦረንቴሽን ይሰጣል።
- ከሐምሌ ከ19 - 21/2015 ፈተናው ለ 3ት ቀናት ይሰጣል ።
- ሐምሌ 22-23/2015 ተማሪዎች ወደ ቤተሰቦቻቸው ይመለሳሉ።
👉 ለተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ፦
- ሐምሌ 22 -23/2015 ወደ ተመደቡበት ዩኒቨርሲቲ ይገባሉ።
- ሐምሌ 24/2015 የፈተና ኦረንቴሽን ይሰጣል።
- ከሐምሌ 25 -28/2015 ፈተናው ለአራት ቀናት ይሰጣል።
- ሐምሌ 29-30/2015 ተማሪዎች ወደ ቤተሰቦቻቸው ይመለሳሉ።
ለ8ኛ እና የ12ኛ ክፍል ፈተናዎች ስኬት ሁሉም ማህበረሰብ የበኩሉን እንዲወጣ የኦሮሚያ ክልል ት/ቢሮው ሀላፊ ጥሪ አቅርበዋል።
በተጨማሪም ተማሪዎች በፈተና ጥሩ ውጤት ለማስመዝገብ በሁሉም አቅጣጫ አስፈላጊውን ዝግጅት እንዲያደርጉ አሳስበዋል።
ምንጭ ፦ የኦሮሚያ ክልል ትምህርት ቢሮ
More : @tikvahethafaanoromoo
@tikvahethiopia
የኦሮሚያ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ቶላ በሪሶ የ8ኛ ክፍል እና የ12ኛ ክፍል ፈተናዎችን አስመልክቶ ማብራሪያ መስጠታቸውን የክልሉ ትምህርት ቢሮ በማህበራዊ ትስስር ገፁ ላይ አሳውቋል።
የ2015 የ8ኛ ክፍል ፈተና እንደ ክልል የሚካሄድ ሲሆን የ12ኛ ክፍል ፈተና በሀገር አቀፍ ደረጃ እንደሚሰጥ ዶ/ር ቶላ በሪሰ ገልጸዋል
የ8ኛ ከፍል ፈተናን በተመለከተ 490,167 ተማሪዎች እንደሚወስዱ (ከዚህም ውስጥ ወንድ 260,807 እና ሴት 229,360 ናቸው) ገልጸው የ8ኛ ክፈል ፈተና የሚሰጥበት ቀን ሰኔ 26 እና 27/2015 መሆኑን አሳውቀዋል።
የ12ኛ ክፈል ብሄራዊ ፈተናን አስመልክቶ በክልሉ 323,149 ተማሪዎች ለፈተናው እንደሚቀመጡ ገልጸው የፈተና ፕሮግራሙን እንደሚከተለው አብራርተዋል።
የፈተናው ፕሮግራም ፦
👉 ለማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች
- ሐምሌ 16 -17 / 2015 ወደ ተመደቡበት ዩኒቨርሲቲ ይገባሉ።
- ሐምሌ 18 የፈተና ኦረንቴሽን ይሰጣል።
- ከሐምሌ ከ19 - 21/2015 ፈተናው ለ 3ት ቀናት ይሰጣል ።
- ሐምሌ 22-23/2015 ተማሪዎች ወደ ቤተሰቦቻቸው ይመለሳሉ።
👉 ለተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ፦
- ሐምሌ 22 -23/2015 ወደ ተመደቡበት ዩኒቨርሲቲ ይገባሉ።
- ሐምሌ 24/2015 የፈተና ኦረንቴሽን ይሰጣል።
- ከሐምሌ 25 -28/2015 ፈተናው ለአራት ቀናት ይሰጣል።
- ሐምሌ 29-30/2015 ተማሪዎች ወደ ቤተሰቦቻቸው ይመለሳሉ።
ለ8ኛ እና የ12ኛ ክፍል ፈተናዎች ስኬት ሁሉም ማህበረሰብ የበኩሉን እንዲወጣ የኦሮሚያ ክልል ት/ቢሮው ሀላፊ ጥሪ አቅርበዋል።
በተጨማሪም ተማሪዎች በፈተና ጥሩ ውጤት ለማስመዝገብ በሁሉም አቅጣጫ አስፈላጊውን ዝግጅት እንዲያደርጉ አሳስበዋል።
ምንጭ ፦ የኦሮሚያ ክልል ትምህርት ቢሮ
More : @tikvahethafaanoromoo
@tikvahethiopia
#Update
የ2015 ዓ.ም ብሔራዊ የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ ፈተና ለመውሰድ ከ869 ሺህ በላይ ተፈታኞች በኦንላይን መመዝገባቸውን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል፡፡
ለ2ኛ ጊዜ በዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ የሚሰጠውን አገር አቀፍ ፈተና ለመውሰድ 869 ሺህ 765 ተፈታኞች በኦንላይን መመዝገባቸውን በአገልግሎቱ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት መሪ ሥራ አስፈጻሚ ወንደወሰን ኢየሱስወርቅ ለኢፕድ ተናግረዋል፡፡
ከተመዘገቡት ውስጥ 503,812 ተማሪዎች የሶሻል ሳይንስ እና 365,954 የተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኞች መሆናቸውን ኃላፊው ገልጸዋል።
የፈተና አስፈጻሚዎች፣ ሱፐርቫይዘሮች እና የፈተና ጣቢያ ኃላፊዎች ምልመላ ቅድመ ዝግጅት ሥራዎች መከናወናቸውን ጠቁመዋል፡፡
የ2015 ዓ.ም የ12ኛ ከፍል ማጠቃለያ ፈተና ከሐምሌ 19 እስከ 30/2015 ዓ.ም በሁለት ዙር እንደሚሰጥ ይታወቃል፡፡ #ኢፕድ
More : @tikvahuniversity
@tikvahethiopia
የ2015 ዓ.ም ብሔራዊ የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ ፈተና ለመውሰድ ከ869 ሺህ በላይ ተፈታኞች በኦንላይን መመዝገባቸውን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል፡፡
ለ2ኛ ጊዜ በዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ የሚሰጠውን አገር አቀፍ ፈተና ለመውሰድ 869 ሺህ 765 ተፈታኞች በኦንላይን መመዝገባቸውን በአገልግሎቱ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት መሪ ሥራ አስፈጻሚ ወንደወሰን ኢየሱስወርቅ ለኢፕድ ተናግረዋል፡፡
ከተመዘገቡት ውስጥ 503,812 ተማሪዎች የሶሻል ሳይንስ እና 365,954 የተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኞች መሆናቸውን ኃላፊው ገልጸዋል።
የፈተና አስፈጻሚዎች፣ ሱፐርቫይዘሮች እና የፈተና ጣቢያ ኃላፊዎች ምልመላ ቅድመ ዝግጅት ሥራዎች መከናወናቸውን ጠቁመዋል፡፡
የ2015 ዓ.ም የ12ኛ ከፍል ማጠቃለያ ፈተና ከሐምሌ 19 እስከ 30/2015 ዓ.ም በሁለት ዙር እንደሚሰጥ ይታወቃል፡፡ #ኢፕድ
More : @tikvahuniversity
@tikvahethiopia
#ቮልስዋገን
" ህጋዊ ፈቃድ ያለው መሆኑ እስኪረጋገጥ ድረስ በጊዜያዊነት ወደ ሀገር እንዳይገባ ታግዷል " - የትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ሚኒስቴር
ወደ ኢትዮጵያ ከሚገቡ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች መካከል በቻይና ሀገር ተገጣጥሞ ወደ ኢትዮጲያ እየገባ የሚገኘው " ቮልስ ዋገን " የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ህጋዊ የሆነ ፍቃድ የሌለው መሆኑን የጀርመን ኩባንያ በኢንባሲው በኩል ለትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ሚኒስቴር በጻፈው ደብዳቤ አሳውቋል።
ይህ ቻይና ሀገር የሚመረተው የ " ቮልስ ዋገን " የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ከኩባንያው ህጋዊ ፈቃድ ያለው መሆኑ እስኪረጋገጥ ድረስ በጊዜያዊነት ወደ ሀገር ውስጥ እንዳይገባ መታገዱን ሚኒስቴሩ ዛሬ አሳውቋል።
ምንጭ፦ የትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ሚኒስቴር
@tikvahethiopia
" ህጋዊ ፈቃድ ያለው መሆኑ እስኪረጋገጥ ድረስ በጊዜያዊነት ወደ ሀገር እንዳይገባ ታግዷል " - የትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ሚኒስቴር
ወደ ኢትዮጵያ ከሚገቡ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች መካከል በቻይና ሀገር ተገጣጥሞ ወደ ኢትዮጲያ እየገባ የሚገኘው " ቮልስ ዋገን " የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ህጋዊ የሆነ ፍቃድ የሌለው መሆኑን የጀርመን ኩባንያ በኢንባሲው በኩል ለትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ሚኒስቴር በጻፈው ደብዳቤ አሳውቋል።
ይህ ቻይና ሀገር የሚመረተው የ " ቮልስ ዋገን " የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ከኩባንያው ህጋዊ ፈቃድ ያለው መሆኑ እስኪረጋገጥ ድረስ በጊዜያዊነት ወደ ሀገር ውስጥ እንዳይገባ መታገዱን ሚኒስቴሩ ዛሬ አሳውቋል።
ምንጭ፦ የትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ሚኒስቴር
@tikvahethiopia
#አቢሲንያ_ባንክ
የቪዛ ካርድዎን ከአቢሲኒያ ባንክ በ72 ሰዓታት ውስጥ ይረከቡ! ልክ እንደጊዜው አገልግሎታችንም ፍጥነትን ከጥራት ያሟላ ነው!
መተግበሪያውን ለማውረድ ሊንኩን ይጠቀሙ።
https://apollo.bankofabyssinia.com/download-apollo
#Apollodigitalproduct #AbyssiniaDigital #VISA #ATMcard #poweredbybankofabyssinia #የሁሉም_ምርጫ #The_Choice_For_all
የቪዛ ካርድዎን ከአቢሲኒያ ባንክ በ72 ሰዓታት ውስጥ ይረከቡ! ልክ እንደጊዜው አገልግሎታችንም ፍጥነትን ከጥራት ያሟላ ነው!
መተግበሪያውን ለማውረድ ሊንኩን ይጠቀሙ።
https://apollo.bankofabyssinia.com/download-apollo
#Apollodigitalproduct #AbyssiniaDigital #VISA #ATMcard #poweredbybankofabyssinia #የሁሉም_ምርጫ #The_Choice_For_all
TIKVAH-ETHIOPIA
የንብረት ግብር . . . " ግብር ከፋዮች የሚከፍሉት የንብረት ግብር ተከራይን የማይመለከትና ወደ ተከራይ መተላለፍ የሌለበት መሆኑን ማወቅ አለባቸው " - የአዲስ አበባ ፋይናንስ ቢሮ ነዋሪዎች ስለ ንብረት ግብር ምን አሉ ? " የኑሮ ውድነቱ ከብዶ ባለበት ሁኔታ ግብሩ መሻሻሉ የመጨረሻ ጫናው ተከራዮች ላይ እንዳያርፍ ያደርጋል። መንግሥት ገበያውን መቆጣጣር አለበት። ግብርን መክፈል የሥልጣኔ መገለጫ…
የቤት ግብር . . .
" የከፈልኩት ክፍያ አሰራሩን የጣሰ ነው "
የአዲስ አበባ ከተማ ቦሌ ክ/ከተማ ነዋሪ የሆኑት አቶ አስቻለው ጣሰው (በብሔራዊ ቴሌቪዥን ላይ ቀርበው የተናገሩት) ፦
" የምኖረው ቦሌ ክፍለ ከተማ ነው።
በወረዳ 14 የታዘብኩትን መናገር እፈልጋለሁ።
እኔ የሚጠበቅብኝን የ ' Property Tax ' ከፍያለሁ ነገር ግን የከፈልኩት ክፍያ አሰራሩን የጣሰ ነው።
ታክስ የመክፈል የዜግነት ግዴታዬ ነው ፤ መጀመሪያ መመሪያውን አይቼ ነው ልከፍል የሄድኩት።
መመሪያው ሰርኩላር የተደረገው ሚያዚያ 7 /2015 ነው። እዚህ መመሪያ ላይ ሂሳቡ የሚሰራበት ቀመር አለ እሱን እስልቼ ነበር የሄድኩት ነገር ግን እዛ ወረዳ ላይ ያየሁት ነገር ከ1000 እስከ 1500 በላይ ምኑንም ያላመላከተ፣ ከመመሪያውም ጋር ያልተናበበ ክፍያ ሰዎች እንዲከፍሉ ይደረጋል።
ይሄ ከተመን በፊት ያለ ነው።
ለምሳሌ ፦ እኔ ካርታዬን ' ዲጅታል ' አስደርጊያለሁ ፣ ዲጂታል ሳስደርግ የመሃንዲስ 1500 ብር ከፍያለሁ ነገር ግን በዚህ ወቅት እንድከፍል የተደረገው መሃንዲስ ስሙ ተጠርቶ ብቻ 500 ብር የመሃንዲስ፣ ፋይሌ ወጥቶ ክፍያ ለምፈፅምበት 500 ፣ እንደገና ቅጣት ተብሎ 500 ፤ ቅጣት የአፈር እና የጣራ ግብር የሚባለው ከሆነ ኮንዶሚኒየሞች በዚህ ሲስተም ሲስተናገዱ አልነበረምና ኮንዶሚኒየሞች በምን ታይቶ ነው ከየካቲት አንድ ጀምሮ ሲስተሙ ቅጣት 5 % እየሰራ የሚሄደው ?
ከዚህ በፊት ተግባራዊ ያልተደረገባቸው የጋራ መኖሪያ ቤቶች / ኮንዶሚኒየም ላይ እንዴት በመኖሪያ ቤቶች አሰራር እዛ ላይ ተግባራዊ ተደረገ ? ይሄ ቅጣት ሚያዚያ ላይ በወጣ ሰርኩላር እንዴት ከየካቲት ጀምሮ ሰው ይቀጣል ?
እንደገና ለመክፈል የሄደ ሰው ፋይሉን ከፋይል አውጥቶ፣ አምጥቶ ክፍል ላለው ሰው እንዴት ፋይል ለወጣበት አገልግሎት ተብሎ 500 ብር ለምንድነው ?
ቀመር የተሰራበትን ተቀበለ አብዛኛው በዝቶብናል አስተያየት ይደረግልን ቢልም ግን አብዛኛውን ህዝብ የማተራመስ በፕሮግራም ያለመጥራት ነገር አለ።
ለምሳሌ ወደ ገርጂ ብዙ የኮንዶሚኒየም ሳይቶች አሉ ፤ እንደውም ሰው ሃሳብ ሲሰጣቸው ምናለ ሳይቶቹን በፕሮግራም አድርጋቹ ብትጠሩን ለአሰራር ለናተም ያመቻል ህዝቡም እንዳለ ከሰኞ እስከ አርብ ሲተራመስ አይውልም ምናለ ፕሮግራም አውጥታችሁ ብታስተናግዱን ? እያለ ይጠይዋል ህዝቡ።
የኔን ያለአገባብ ክፍያ ያየ ጓደኛዬ ክፍለ ከተማ ሄዶ 500 ብር ብቻ ከፈለ። ተመልከቱ ክ/ከተማውን እና ወረዳዎች በምን ደረጃ ነው የሚናበቡት ? ቦሌ እና ለሚ ኩራ የሚያስከፍሉት ይለያያል 100 ብር ከፍለን ያሉ አሉ። እዛው ወረዳ 14 እና 13 እራሱ ወረዳ 13 100 ብር ሲያስከፍል ወረዳ 14 1000 ብር ያስከፍላል ይህ አገልግሎት ለሚባለው ነው ቅጣቱን ተውትና።
ሁሉም ቦታ የአገልግሎት እያሉ ይቀበላሉ፤ ግን ወጥ አይደለም ። ለምን ጉራማይሌ ሆነ ? አንዱ ጋር መቶ ሌላው ጋር ሌላ በተለይ የመሃንዲሱ ብቻ 500 ፣ የአገልግሎት 500 እኔ ደረሰኝ ይዤ ነው ይሄንን የምናገረው።
አፈፃፀሙ ላይ ሰዎች ቅር እያላቸው ባላመኑበት ሁኔታ ላይ ተገደው የመክፈል ሁኔታ አለ። ከምንገላታ በሚልም ... አንድ ሰው በጣም ፈጠነ ከተባለ 3 ቀን ነው የሚፈጅበት እኔ 3 ቀን ከመ/ቤት አስፈቅጃለሁ ይሄንን ጉዳይ ለመፈፀም።
ልገብር ብሎ የሚሄድ ሰው ሶስት ቀን ከስራው ቀርቶ አስቡት።
እናስተካክላለን ይላሉ ፤ እሺ የከፈሉ ሰዎች ጉዳይ ምን ይደረጋል ? ሌላው የባንክ እዳ ያለባቸውና ካርታው ባንክ የሆናባቸው አሉ አሁን እነዚህ ሰዎች ሙሉ ባለቤት ነን አይሉም የባንክ እዳ እየከፈሉ ነው ይሄስ እንዴት ነው የሚታየው ?
ኮንዶሚኒየም እና የማህበር ቤቶች በጣም ልዩነት አለው ፤ የማህበር ቤቶች ሲሰሩበት ኖረዋል የአፈር እና የጣራ ግብር እየተባለ አሁን የዛ Update የሆነ ነው እየተባለ ነው ፤ እንዲህ በሆነበት ሁኔታ የኮንዶሚኒየም በዛ ህግ መገዛት አለበት ወይ ? እሺ በህጉ ይገዛ ከዚህ በፊት ባልከፈለበት ሁኔታ ቅጣት የሚባለው ለምን ጨመረ ?
ህዝቡ በአሰራሩና በፕሮግራም አልባነቱ እያመረረ እየተንገላታ ነው። ለመክፈልም ሄዶ መንገላታት በጣም አለ።
ወጥ የሆነው አሰራር ከክፍለ ከተማ እስከ ወረዳ የለም ፤ በራሳቸው በክ/ከተሞች መካከል ተመሳሳይ አከፋፈል የለም ፤ ከአንድ ቢሮ የሚወጣ ከሆነ አሰራሩ ወጥ ሊሆን ይገባል። "
በአዲስ አበባ አስተዳደር የመሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ አማካሪ ዶ/ር ፈቀደ ተረፈ ፦
" አንዳንድ ቦታዎች ላይ የአገልግሎት ክፍያ ተብሎ የተነሳውና መሃንዲስ እንዲሁም የፋይል ተብሎ የተቀመጠው በአሰራር ውስጥ የለም። ይሄ መከፈል የለበትም ይሄ በአሰራር ውስጥ ስለሌለ መከፈል የለበትም።
ከህብረተሰቡ የሚነሱትን ቅሬታዎች እያስተካከልን እንሄዳለን። "
@tikvahethiopia @tikvah_eth_BOT
" የከፈልኩት ክፍያ አሰራሩን የጣሰ ነው "
የአዲስ አበባ ከተማ ቦሌ ክ/ከተማ ነዋሪ የሆኑት አቶ አስቻለው ጣሰው (በብሔራዊ ቴሌቪዥን ላይ ቀርበው የተናገሩት) ፦
" የምኖረው ቦሌ ክፍለ ከተማ ነው።
በወረዳ 14 የታዘብኩትን መናገር እፈልጋለሁ።
እኔ የሚጠበቅብኝን የ ' Property Tax ' ከፍያለሁ ነገር ግን የከፈልኩት ክፍያ አሰራሩን የጣሰ ነው።
ታክስ የመክፈል የዜግነት ግዴታዬ ነው ፤ መጀመሪያ መመሪያውን አይቼ ነው ልከፍል የሄድኩት።
መመሪያው ሰርኩላር የተደረገው ሚያዚያ 7 /2015 ነው። እዚህ መመሪያ ላይ ሂሳቡ የሚሰራበት ቀመር አለ እሱን እስልቼ ነበር የሄድኩት ነገር ግን እዛ ወረዳ ላይ ያየሁት ነገር ከ1000 እስከ 1500 በላይ ምኑንም ያላመላከተ፣ ከመመሪያውም ጋር ያልተናበበ ክፍያ ሰዎች እንዲከፍሉ ይደረጋል።
ይሄ ከተመን በፊት ያለ ነው።
ለምሳሌ ፦ እኔ ካርታዬን ' ዲጅታል ' አስደርጊያለሁ ፣ ዲጂታል ሳስደርግ የመሃንዲስ 1500 ብር ከፍያለሁ ነገር ግን በዚህ ወቅት እንድከፍል የተደረገው መሃንዲስ ስሙ ተጠርቶ ብቻ 500 ብር የመሃንዲስ፣ ፋይሌ ወጥቶ ክፍያ ለምፈፅምበት 500 ፣ እንደገና ቅጣት ተብሎ 500 ፤ ቅጣት የአፈር እና የጣራ ግብር የሚባለው ከሆነ ኮንዶሚኒየሞች በዚህ ሲስተም ሲስተናገዱ አልነበረምና ኮንዶሚኒየሞች በምን ታይቶ ነው ከየካቲት አንድ ጀምሮ ሲስተሙ ቅጣት 5 % እየሰራ የሚሄደው ?
ከዚህ በፊት ተግባራዊ ያልተደረገባቸው የጋራ መኖሪያ ቤቶች / ኮንዶሚኒየም ላይ እንዴት በመኖሪያ ቤቶች አሰራር እዛ ላይ ተግባራዊ ተደረገ ? ይሄ ቅጣት ሚያዚያ ላይ በወጣ ሰርኩላር እንዴት ከየካቲት ጀምሮ ሰው ይቀጣል ?
እንደገና ለመክፈል የሄደ ሰው ፋይሉን ከፋይል አውጥቶ፣ አምጥቶ ክፍል ላለው ሰው እንዴት ፋይል ለወጣበት አገልግሎት ተብሎ 500 ብር ለምንድነው ?
ቀመር የተሰራበትን ተቀበለ አብዛኛው በዝቶብናል አስተያየት ይደረግልን ቢልም ግን አብዛኛውን ህዝብ የማተራመስ በፕሮግራም ያለመጥራት ነገር አለ።
ለምሳሌ ወደ ገርጂ ብዙ የኮንዶሚኒየም ሳይቶች አሉ ፤ እንደውም ሰው ሃሳብ ሲሰጣቸው ምናለ ሳይቶቹን በፕሮግራም አድርጋቹ ብትጠሩን ለአሰራር ለናተም ያመቻል ህዝቡም እንዳለ ከሰኞ እስከ አርብ ሲተራመስ አይውልም ምናለ ፕሮግራም አውጥታችሁ ብታስተናግዱን ? እያለ ይጠይዋል ህዝቡ።
የኔን ያለአገባብ ክፍያ ያየ ጓደኛዬ ክፍለ ከተማ ሄዶ 500 ብር ብቻ ከፈለ። ተመልከቱ ክ/ከተማውን እና ወረዳዎች በምን ደረጃ ነው የሚናበቡት ? ቦሌ እና ለሚ ኩራ የሚያስከፍሉት ይለያያል 100 ብር ከፍለን ያሉ አሉ። እዛው ወረዳ 14 እና 13 እራሱ ወረዳ 13 100 ብር ሲያስከፍል ወረዳ 14 1000 ብር ያስከፍላል ይህ አገልግሎት ለሚባለው ነው ቅጣቱን ተውትና።
ሁሉም ቦታ የአገልግሎት እያሉ ይቀበላሉ፤ ግን ወጥ አይደለም ። ለምን ጉራማይሌ ሆነ ? አንዱ ጋር መቶ ሌላው ጋር ሌላ በተለይ የመሃንዲሱ ብቻ 500 ፣ የአገልግሎት 500 እኔ ደረሰኝ ይዤ ነው ይሄንን የምናገረው።
አፈፃፀሙ ላይ ሰዎች ቅር እያላቸው ባላመኑበት ሁኔታ ላይ ተገደው የመክፈል ሁኔታ አለ። ከምንገላታ በሚልም ... አንድ ሰው በጣም ፈጠነ ከተባለ 3 ቀን ነው የሚፈጅበት እኔ 3 ቀን ከመ/ቤት አስፈቅጃለሁ ይሄንን ጉዳይ ለመፈፀም።
ልገብር ብሎ የሚሄድ ሰው ሶስት ቀን ከስራው ቀርቶ አስቡት።
እናስተካክላለን ይላሉ ፤ እሺ የከፈሉ ሰዎች ጉዳይ ምን ይደረጋል ? ሌላው የባንክ እዳ ያለባቸውና ካርታው ባንክ የሆናባቸው አሉ አሁን እነዚህ ሰዎች ሙሉ ባለቤት ነን አይሉም የባንክ እዳ እየከፈሉ ነው ይሄስ እንዴት ነው የሚታየው ?
ኮንዶሚኒየም እና የማህበር ቤቶች በጣም ልዩነት አለው ፤ የማህበር ቤቶች ሲሰሩበት ኖረዋል የአፈር እና የጣራ ግብር እየተባለ አሁን የዛ Update የሆነ ነው እየተባለ ነው ፤ እንዲህ በሆነበት ሁኔታ የኮንዶሚኒየም በዛ ህግ መገዛት አለበት ወይ ? እሺ በህጉ ይገዛ ከዚህ በፊት ባልከፈለበት ሁኔታ ቅጣት የሚባለው ለምን ጨመረ ?
ህዝቡ በአሰራሩና በፕሮግራም አልባነቱ እያመረረ እየተንገላታ ነው። ለመክፈልም ሄዶ መንገላታት በጣም አለ።
ወጥ የሆነው አሰራር ከክፍለ ከተማ እስከ ወረዳ የለም ፤ በራሳቸው በክ/ከተሞች መካከል ተመሳሳይ አከፋፈል የለም ፤ ከአንድ ቢሮ የሚወጣ ከሆነ አሰራሩ ወጥ ሊሆን ይገባል። "
በአዲስ አበባ አስተዳደር የመሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ አማካሪ ዶ/ር ፈቀደ ተረፈ ፦
" አንዳንድ ቦታዎች ላይ የአገልግሎት ክፍያ ተብሎ የተነሳውና መሃንዲስ እንዲሁም የፋይል ተብሎ የተቀመጠው በአሰራር ውስጥ የለም። ይሄ መከፈል የለበትም ይሄ በአሰራር ውስጥ ስለሌለ መከፈል የለበትም።
ከህብረተሰቡ የሚነሱትን ቅሬታዎች እያስተካከልን እንሄዳለን። "
@tikvahethiopia @tikvah_eth_BOT
የጣሪያና ግድግዳ ግብር . . .
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የኮሚኒኬሽን ቢሮ ፤ የጣሪያና ግድግዳ ግብርን በተመለከተ ዛሬ ለግንዛቤ በሚል አንድ መረጃ አሰራጭቷል።
በዚሁ መረጀው ፤ " መንግስት በሚያለማው መሰረተ ልማት እና የህግ ማሻሻያ ምክንያት በመሬት እና መሬት ነክ ንብረቶች እሴታቸው (Value) ይጨምራል " ያለ ሲሆን " መሬትና መሬት ነክ ንብረቶች እሴታቸው በመጨመሩ ምክኒያት የአከባቢ መንግስታት የሚሰበስቡት ገቢ የቤት ግብር ወይንም የጣራና ግድግዳ ግብር በመባል ይታወቃል " ሲል አስረድቷል።
የጣሪያና ግድግዳ ግብር የሚሰበሰበው ፦
- ከጣሪያና ግድግዳ ግብር የሚሰበሰበው ገቢ መሰረቱ የተረጋጋና አስተማማኝ የገቢ ምንጭ በመሆኑ፣
- የማይለዋወጥና የማይሰወር የግብር አይነት በመሆኑ፣
- ለቁጥጥር አመቺና ከታክስ ለመሸሽ የማይመች የግብር መሰረት በመሆኑ፣
- ለከተሞች የመሰረተ ልማት እድገት የጀርባ አጥንት እንዲሁም ለከተሞች መሰረታዊ የመሰረተ ልማት ችግሮችን ፍላጎት የሚያሟላ በመሆኑ
- ከፋዮች በከፈሉት ልክ የመሰረተ ልማት ተጠቃሚ እንዲሆኑ የሚያደርግ በመሆኑ ነው ብሏል።
ቢሮው ፤ የጣራና ግድግዳ ግብር በአገራችን በህግ በተደገፈ በዘመናዊ መልኩ መተግበር የጀመረው በ1937 ዓ.ም ነው ብሏል።
በመጀመሪያው በከተማ ውስጥ የንብረት ግብር ይጣል የነበረው በማናቸውም የማይንቀሳቀስ ንብረት በመሬትና በህንፃዎች ላይ ነበር ሲል አስታውሷል።
ሁለተኛው በከተማ መሬት ኪራይና በከተማ ቤት ግብር አዋጅ ቁጥር 80/1968 መሆኑን ገልጾ በአዋጁ አንቀጽ 6 መሰረት የጣሪያ ግድግዳ ግብር ዓመታዊ የቤት ኪራይ ግምት መሰረት በማድረግ እንደሚሰበሰብ አመልክቷል።
ሶስተኛው " የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ህገመንግስት አንቀጽ 49 መሰረት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የስልጣን ይዘት እና ወሰን ለመደንገግ በወጣው የፌደራል ቻርተር አዋጅ 361/1995 መሰረት በከተማው ውስጥ የከተማ ቦታ ኪራይ እና የቤት ግብር ይወስናል ይሰበስባል ይላል " ሲል አስረድቷል።
እንደ ኮሚኒኬሽን ቢሮው መረጃ በከተማ አስተዳደሩ ውስጥ ይኖራሉ ተብሎ የሚገመተው 1,020,528 መኖሪያ ቤቶች ሲሆኑ ከዚህ ውስጥ የግል ቤቶች 891,628 ቤቶች እንደሆኑ ይገመታል። ከነዚህ መካከል ግብር እየከፈሉ ያሉት 182,842 ባለይዞታዎች እንደሆኑ የተገለፀ ሲሆን የከፋዮች ቁጥር ማነስ ብቻ ሳይሆን የሚሰበሰበውም ገቢ በጣም አነስተኛ ነው ተብሏል።
" የክፍያ ጫናውን ለማቅለል ሲባል የዚህ ዓመት ክፍያ ያልከፈሉ የቤት ግብር ከፋዮች በጥናት በተለየው የአንድ ሜትር ካሬ የቤት ስፋት ወርሀዊ ኪራይ ግምት ወይም ዓመታዊ የኪራይ ግምት መጠንን ለመኖሪያ ቤት በ50% እና ለመሥሪያ ቤት ደግሞ በ75% ላይ ብቻ ግብሩን በማስላት እንዲከፍሉ ይደረጋል " ሲል የከተማው ኮሚኒኬሽን አስረድቷል።
@tikvahethiopia
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የኮሚኒኬሽን ቢሮ ፤ የጣሪያና ግድግዳ ግብርን በተመለከተ ዛሬ ለግንዛቤ በሚል አንድ መረጃ አሰራጭቷል።
በዚሁ መረጀው ፤ " መንግስት በሚያለማው መሰረተ ልማት እና የህግ ማሻሻያ ምክንያት በመሬት እና መሬት ነክ ንብረቶች እሴታቸው (Value) ይጨምራል " ያለ ሲሆን " መሬትና መሬት ነክ ንብረቶች እሴታቸው በመጨመሩ ምክኒያት የአከባቢ መንግስታት የሚሰበስቡት ገቢ የቤት ግብር ወይንም የጣራና ግድግዳ ግብር በመባል ይታወቃል " ሲል አስረድቷል።
የጣሪያና ግድግዳ ግብር የሚሰበሰበው ፦
- ከጣሪያና ግድግዳ ግብር የሚሰበሰበው ገቢ መሰረቱ የተረጋጋና አስተማማኝ የገቢ ምንጭ በመሆኑ፣
- የማይለዋወጥና የማይሰወር የግብር አይነት በመሆኑ፣
- ለቁጥጥር አመቺና ከታክስ ለመሸሽ የማይመች የግብር መሰረት በመሆኑ፣
- ለከተሞች የመሰረተ ልማት እድገት የጀርባ አጥንት እንዲሁም ለከተሞች መሰረታዊ የመሰረተ ልማት ችግሮችን ፍላጎት የሚያሟላ በመሆኑ
- ከፋዮች በከፈሉት ልክ የመሰረተ ልማት ተጠቃሚ እንዲሆኑ የሚያደርግ በመሆኑ ነው ብሏል።
ቢሮው ፤ የጣራና ግድግዳ ግብር በአገራችን በህግ በተደገፈ በዘመናዊ መልኩ መተግበር የጀመረው በ1937 ዓ.ም ነው ብሏል።
በመጀመሪያው በከተማ ውስጥ የንብረት ግብር ይጣል የነበረው በማናቸውም የማይንቀሳቀስ ንብረት በመሬትና በህንፃዎች ላይ ነበር ሲል አስታውሷል።
ሁለተኛው በከተማ መሬት ኪራይና በከተማ ቤት ግብር አዋጅ ቁጥር 80/1968 መሆኑን ገልጾ በአዋጁ አንቀጽ 6 መሰረት የጣሪያ ግድግዳ ግብር ዓመታዊ የቤት ኪራይ ግምት መሰረት በማድረግ እንደሚሰበሰብ አመልክቷል።
ሶስተኛው " የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ህገመንግስት አንቀጽ 49 መሰረት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የስልጣን ይዘት እና ወሰን ለመደንገግ በወጣው የፌደራል ቻርተር አዋጅ 361/1995 መሰረት በከተማው ውስጥ የከተማ ቦታ ኪራይ እና የቤት ግብር ይወስናል ይሰበስባል ይላል " ሲል አስረድቷል።
እንደ ኮሚኒኬሽን ቢሮው መረጃ በከተማ አስተዳደሩ ውስጥ ይኖራሉ ተብሎ የሚገመተው 1,020,528 መኖሪያ ቤቶች ሲሆኑ ከዚህ ውስጥ የግል ቤቶች 891,628 ቤቶች እንደሆኑ ይገመታል። ከነዚህ መካከል ግብር እየከፈሉ ያሉት 182,842 ባለይዞታዎች እንደሆኑ የተገለፀ ሲሆን የከፋዮች ቁጥር ማነስ ብቻ ሳይሆን የሚሰበሰበውም ገቢ በጣም አነስተኛ ነው ተብሏል።
" የክፍያ ጫናውን ለማቅለል ሲባል የዚህ ዓመት ክፍያ ያልከፈሉ የቤት ግብር ከፋዮች በጥናት በተለየው የአንድ ሜትር ካሬ የቤት ስፋት ወርሀዊ ኪራይ ግምት ወይም ዓመታዊ የኪራይ ግምት መጠንን ለመኖሪያ ቤት በ50% እና ለመሥሪያ ቤት ደግሞ በ75% ላይ ብቻ ግብሩን በማስላት እንዲከፍሉ ይደረጋል " ሲል የከተማው ኮሚኒኬሽን አስረድቷል።
@tikvahethiopia