TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.2K photos
1.5K videos
211 files
4.1K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
የቤት ፈረሳ ጉዳይ ...

(በቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል - ጆሲ)

" የቲክቫህ ቤተሰቦች እንደምታውቁት ' ሸገር ሲቲ ' በሚል ምክንያት በነበረ የቤት ማፍረስ ዘመቻ ብዙ ሰዎች እንደተፈናቀሉ የሚዘነጋ አይደለም።

ግን ለጥቂት ጊዜ የመቆም አዝማምያ አሳይቶ ነበር፤ አሁን ላይ ግን ከሚባለው በላይ በአስከፊ ሁኔታ ቀጥሏል።

በጣም #በሚያፀይፍ_ሁኔታ በሚባል መልኩ እንደሚታወቀው ወቅቱ የዝናብ ወቅት ነው ህዝቡ በዚ ወቅት እንኳን መፈናቀል አይደለም እንደፈለገ ወጥቶ መግባት እንኳን የማይችልበት ወቅት ነው ታድያ በዚህ ወቅት ይህ ህዝብ የት ይጠለል ?

ህፃናት ልጆች አሉ ፤ አረጋውያን አሉ ፤ ነፍሰ ጡሮች አሉ ታድያ ይሄንን እንኳን ከግምት ውስጥ ያላስገባ የልማት ዘመቻ በየትኛው ወገን ነው ተቀባይነት ሊያገኝ የሚችለው ?

እሱ ይቅር እኔ ባለሁበት አካባቢ እየተደረገ ያለው ነገር እጅግ አፀያፊ ተግባር ከሰው ልጅ ማንነት የማይጠበቅ ፤ ሰብዓዊነት የጎደለው ተግባር ነው።

እባካቹ የሚመለከተው አካል ይህንን ቅሬታችን ይስማን ። "

Via @tikvah_eth_Bot

ፎቶ ፦ ፋይል

@tikvahethiopia