የቤት ፈረሳ ጉዳይ ...
(በቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል - ጆሲ)
" የቲክቫህ ቤተሰቦች እንደምታውቁት ' ሸገር ሲቲ ' በሚል ምክንያት በነበረ የቤት ማፍረስ ዘመቻ ብዙ ሰዎች እንደተፈናቀሉ የሚዘነጋ አይደለም።
ግን ለጥቂት ጊዜ የመቆም አዝማምያ አሳይቶ ነበር፤ አሁን ላይ ግን ከሚባለው በላይ በአስከፊ ሁኔታ ቀጥሏል።
በጣም #በሚያፀይፍ_ሁኔታ በሚባል መልኩ እንደሚታወቀው ወቅቱ የዝናብ ወቅት ነው ህዝቡ በዚ ወቅት እንኳን መፈናቀል አይደለም እንደፈለገ ወጥቶ መግባት እንኳን የማይችልበት ወቅት ነው ታድያ በዚህ ወቅት ይህ ህዝብ የት ይጠለል ?
ህፃናት ልጆች አሉ ፤ አረጋውያን አሉ ፤ ነፍሰ ጡሮች አሉ ታድያ ይሄንን እንኳን ከግምት ውስጥ ያላስገባ የልማት ዘመቻ በየትኛው ወገን ነው ተቀባይነት ሊያገኝ የሚችለው ?
እሱ ይቅር እኔ ባለሁበት አካባቢ እየተደረገ ያለው ነገር እጅግ አፀያፊ ተግባር ከሰው ልጅ ማንነት የማይጠበቅ ፤ ሰብዓዊነት የጎደለው ተግባር ነው።
እባካቹ የሚመለከተው አካል ይህንን ቅሬታችን ይስማን ። "
Via @tikvah_eth_Bot
ፎቶ ፦ ፋይል
@tikvahethiopia
(በቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል - ጆሲ)
" የቲክቫህ ቤተሰቦች እንደምታውቁት ' ሸገር ሲቲ ' በሚል ምክንያት በነበረ የቤት ማፍረስ ዘመቻ ብዙ ሰዎች እንደተፈናቀሉ የሚዘነጋ አይደለም።
ግን ለጥቂት ጊዜ የመቆም አዝማምያ አሳይቶ ነበር፤ አሁን ላይ ግን ከሚባለው በላይ በአስከፊ ሁኔታ ቀጥሏል።
በጣም #በሚያፀይፍ_ሁኔታ በሚባል መልኩ እንደሚታወቀው ወቅቱ የዝናብ ወቅት ነው ህዝቡ በዚ ወቅት እንኳን መፈናቀል አይደለም እንደፈለገ ወጥቶ መግባት እንኳን የማይችልበት ወቅት ነው ታድያ በዚህ ወቅት ይህ ህዝብ የት ይጠለል ?
ህፃናት ልጆች አሉ ፤ አረጋውያን አሉ ፤ ነፍሰ ጡሮች አሉ ታድያ ይሄንን እንኳን ከግምት ውስጥ ያላስገባ የልማት ዘመቻ በየትኛው ወገን ነው ተቀባይነት ሊያገኝ የሚችለው ?
እሱ ይቅር እኔ ባለሁበት አካባቢ እየተደረገ ያለው ነገር እጅግ አፀያፊ ተግባር ከሰው ልጅ ማንነት የማይጠበቅ ፤ ሰብዓዊነት የጎደለው ተግባር ነው።
እባካቹ የሚመለከተው አካል ይህንን ቅሬታችን ይስማን ። "
Via @tikvah_eth_Bot
ፎቶ ፦ ፋይል
@tikvahethiopia