TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.2K photos
1.5K videos
211 files
4.1K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#ድርድር የኢትዮጵያ መንግሥት ከሸኔ ወይም እራሱን የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት እያለ ከሚጠራው ታጣቂ ቡድን ጋር የሚደረገው ድርድር ከነገ ወዲያ በታንዛኒያ እንደሚጀመር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ዛሬ ገልጸዋል። ይህንን ያሳወቁት ፥ በሰሜን ኢትዮጵያ የነበረው ግጭት በሰላም ስምምት እንዲቋጭ ቁልፍ ሚና ለነበራቸው አካላት የምስጋና እና የዕውቅና ሥነ ስርዓት በተካሄደበት ወቅት ነው። ጠቅላይ ሚኒስትሩ…
#ድርድር

ጠ/ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ስለ #ድርድር ምንድነው ያሉት ?

" ከኦነግ ሸኔ ጋር የሚደረገው ድርድር ከነገ ወዲያ በታንዛኒያ ይጀመራል።

ይህንን ድርድር የኢትዮጵያ መንግሥት እና ህዝብ አብዝቶ ይፈልገዋል።

በዚህ ድርድር የሚሳተፉ ወገኖች ሁሉ የዛሬዋን ቀን እያሰቡ ፣ ከግጭት፣  ከጦርነት እንደማናተርፍ አውቀው ህግ እና ስርዓት ተከትለን ይቅር ተባብለን ሀገራችንን በጋራ ማነፅ እና መገንባት እንድንችል ፤ የወለጋ ህዝብ አሁን ካለበት ስቃይ እፎይ ማለት እንዲችል ሁሉም ወገን የበኩላቸውን እንዲያደርጉ ከወዲሁ ጥሪዬን አቀርባለሁ። "

ይህንን ድርድር በተመለከተ ከታጠቀው ቡድን (የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት/ መንግሥት ኦነግ ሸኔ ከሚለው ቡድን) በኩል የሚሰጥ መግለጫ ሆነ መረጃ ካለ ተከታትለን እናሳውቃለን።

@tikvahethiopia
" የእኔን ወላጆች ጨምሮ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ተፈናቃዮች አሉን መመለስ መቻል አለባቸው " - አቶ ጌታቸው ረዳ

ዛሬ በአዲስ አበባ ወዳጅነት አደባባይ " ጦርነት ይብቃ፣ ሰላምን እናፅና " በሚል መሪ ቃል የሰሜን ኢትዮጵያውን ጦርነት በሰላም እና በንግግር እንዲቋጭ ላደረጉ አካላት የምስጋና መርሀ ግብር ተካሂዶ ነበር።

በዚህ ስነስርት ላይ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ፣ የአፍሪካ ህብረት ሊቀመንበር ሙሳ ፋኪ መሀመት፣ የአፍሪካ ህብረት የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ኦሊሴንጉን ኦባሳንጆ፣ የቀድሞ የኬንያ ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ፣ አምባሳደር ማይክ ሀመር እና ሌሎችም በርካታ የፌዴራል እና የክልል ከፍተኛ ባለስልጣናት ተገኝተው ነበር።

በዚሁ መድረክ ላይ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ ንግግር አድርገው ነበር።

በንግግራቸው ምን አሉ ?

አቶ ጌታቸው ረዳ ፦

" የትግራይ ህዝብ ጦርነት ሰልችቶታል። ጠብመንጃ የመነቅነቅ አባዜ በፍፁም አይኖረም በዚህ አጋጣሚ ከትግራይ ይዤ የመጣሁት መልዕክት የሰላም እና የፍቅር መልዕክት ብቻ ነው።

አሁንም አራት ዓመት በላይ ትምህርት የሚባል ያላየሁ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ልጆች አሉን ትምህርት ቤት መግባት መቻል አለባቸው።

አሁንም በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ተፈናቃዮች አሉን የኔን ወላጆች ጨምሮ መመለስ መቻል አለባቸው ፣ ስራቸውን መስራት መቻል አለባቸው።

ሁሉንም ነገር ለሰላም በሚሆን መልኩ እናድርገው ፣ ከጎረቤት ወንድም ህዝቦች በተለይም ከአማራ እና ከአፋር ጋር ሊያጋጨን የሚገባ ነገር ሳይኖር ፣ ግጭት ተፈጥሮ በሁላችንም ዘንድ ታሪክ ይቅል ሊለው የማይገባ ብዙ ጥፋት ተፈፅሟል።

ይሄንን ነገር ለአንዴ እና ለመጨረሻ ጊዜ ዘግተን ቋንቋችንን የሰላም እና የመከባበር፣ ልዩነቶቻችንን በመከባበር ፣ በመቻቻል እና በህግ ብቻ ለመፍታት እስከሰራን ድረስ በጋራ ሀገራችንን ከመገንባት አልፈን ፣ በሁለቱም በሶስቱም ጎረቤት እህትማማች፣ ወንድማማች ህዝቦች መካከል ተጥሮ ያለውን መቃቃይ የሚመስል ስሜት አስወግደን ወደ ተሻለ ደረጃ የማናሳድግበት ምክንያት የለም።

... አሁንም ደግሜ ደጋግሜ የምለው የትግራይ ህዝብ ጦርነት ሰልችቶታል ፤ አንገሽግሾታል ይህ ብቻ ሳይሆን ሌሎች አካባቢዎች እንደ ኖርማል የሚወሰዱ ህፃናትን ትምህርት ቤት በሰዓቱ መላክ መመለስ የሚመስሉ ጉዳዮች፣ ማረስ፣ ማለስለስ፣ ማጨድ መዝራት የሚባሉ ነገሮች ይናፍቁታል ፈጥነን ወደዚህ መመለስ መቻል አለብን።

ሁሉንም ለማድረግ የሁሉንም አቅም መጠቀም ያስፈልገናል። ከምንም ነገር በላይ ጠንካራ ሰራተኛ የሆነው የትግራይ ህዝብ ተመልሶ ወደ ስራው ተሰማርቶ የሰላም ችግር ሳይሆን ምን ያክል አተረፍኩ ምን ያክል አመረትኩ በሚል ፉክክር ውስጥ እንዲገባ ለማስቻል የጀመርነውን ጥረት አጠናክረን የምንቀጥል ይሆናል፤ ሁሉም ክልሎች የዚህ እንቅስቃሴ አካል እንደሚሆኑ እምነቴ የፀና ነው ፤ ከፌዴራል መንግሥት ጋር የጀመርናቸው መልካም ግንኙነቶች በአጭር ጊዜ ውስጥ አውንታዊ በሆነ መልኩ ትልቅ ደረጃ ላይ እንደሚደርሱ እምነታችን የፀና ነው። "

@tikvahethiopia
#ExodusPhysiotherapy

በኤክሶደስ የፊዚዮቴራፒ ስፔሻሊቲ ክሊኒክ የምንሰጣቸው የህክምና አገልግሎቶች ፦
- ለአንገት፣ለትክሻ፣ለወገብ ህመም;ከዲስክ መንሸራተት ጋር በተያያዘ ለሚመጣ ችግር፣ ለማዞር ወይንም ሚዛን የመጠበቅ ችግር፣ ለፊት መጣመም፣ ከስትሮክ በኋላ ለሚመጣ ግማሽ የሰውነት ክፍል መዛል፣ ለስፖርታዊ ጉዳቶች ፣ ከህፃናት የእድገት ውስንነት ጋር በተያያዘ ለሚከሰቱ የእንቅስቃሴ ችግሮች ፣ በአጠቃላይ ከነርቭ፣ ከጡንቻ፣ ከመገጣጠሚያ ጋር በተገናኘ ለሚከሰቱ ችግሮች መፍትሄ ያግኙ ይዳኑ !

የስራ ሰዓት ዘወትር ከሰኞ እስከ ቅዳሜ     #ከጠዋቱ 2:30 እስከ #ምሽት 1:00 ሰዓት
አድራሻችን ፦ 22 ከመክሊት ህንፃ ፊት ለፊት ባሮ ህንፃ ላይ እንገኛለን።

ስልክ ፦ 0979099909/ 0911039377
በቴሌግራም ቻናላችን ጠቃሚ መረጃ ያግኙ
https://t.iss.one/ExodPhysioClinic
#AmazonFashion

አማዞን ፋሽን ጥራት ያላቸው ዘመናዊ የቱርክ ሱፎችን በተለያየ አማራጭ ይዞላቹ ቀርቧል። በቡድን ለሚመጡ ተማሪዎች እና ሚዜዎች ጥሩ ቅናሽና ፓኬጅ አዘጋጅተናል።

አድራሻ: ፒያሳ ዶውንታውን ህንፃ ምድር ላይና 2ኛ ፎቅ   

ስልክ ፦ 0919339250 / 0911072936 

https://t.iss.one/joinchat/AAAAAEc8iQJX1Zjgepjq1w
የኢትዮ ቴሌኮም መልዕክት!

ከዛሬ ሚያዝያ 16 ቀን ጀምሮ በአዲስ አበባ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በዲጂታል ክፍያ ሥርዓት ብቻ የሚፈጸም በመሆኑ ለተግባራዊነቱ በአዲስ አበባ ሁሉም የነዳጅ ማደያዎች በቂ ዝግጅት ማድረጋችንን እንገልጻለን።

⛽️ ውድ ደንበኞቻችን ነዳጅ ለመቅዳት ወደ ነዳጅ ማደያ ስትሄዱ በቅድሚያ፡ የቴሌብር ሱፐርአፕን ከ onelink.to/75zfa5 በማውረድ ወይም *127# በመደወል የቴሌብር አካውንት በቀላሉ ክፈቱ፤

⛽️ ከቴሌብር ጋር በተሳሰሩ 20 ባንኮች ከሚገኝ የባንክ አካውንታችሁ፤ በየነዳጅ ማደያዎቹ በተመደቡ የቴሌብር ወኪሎች ወይም የአገልግሎት ማዕከሎቻችን እማካኝነት ገንዘብ ወደ ቴሌብር አካውንትዎ ማስተላለፍ ይችላሉ፤

⛽️ የነዳጅ ማደያ ሠራተኞች ስልክ ቁጥርና የሚከፍሉትን የገንዘብ መጠን ሞልተው ሲጨርሱ በስልክዎ በሚደርስዎ የማረጋገጫ መልዕክት ላይ የገንዘብ መጠኑ ትክክል መሆኑን በማየት የሚስጥር ቁጥር ማስገቢያ ሳጥኑ ውስጥ የሚስጥር ቁጥር (ፒን) በማስገባት ያረጋግጡ፡፡

በመጨረሻም ክፍያው መፈጸሙን የሚያረጋግጥ አጭር መልዕክት የሚደርስዎ ሲሆን ከቴሌብር ሱፐርአፕም ደረሰኝ ማግኘት ይችላሉ፡፡

ለተጨማሪ መረጃ bit.ly/3V3wjPF

(ኢትዮ ቴሌኮም)
TIKVAH-ETHIOPIA
#ድርድር ጠ/ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ስለ #ድርድር ምንድነው ያሉት ? " ከኦነግ ሸኔ ጋር የሚደረገው ድርድር ከነገ ወዲያ በታንዛኒያ ይጀመራል። ይህንን ድርድር የኢትዮጵያ መንግሥት እና ህዝብ አብዝቶ ይፈልገዋል። በዚህ ድርድር የሚሳተፉ ወገኖች ሁሉ የዛሬዋን ቀን እያሰቡ ፣ ከግጭት፣  ከጦርነት እንደማናተርፍ አውቀው ህግ እና ስርዓት ተከትለን ይቅር ተባብለን ሀገራችንን በጋራ ማነፅ እና መገንባት…
#Update

የኢፌዴሪ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ትላንት " ኦነግ ሸኔ " እያሉ ከጠሩት የታጠቀ ቡድን ጋር ነገ ማክሰኞ በታንዛንያ ድርድር እንደሚጀመር ማሳወቃቸው ይታወሳል።

ይህንን የጠቅላይ ሚኒስትሩን ንግግር የታጣቂው ቡድን /የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት / ማረጋገጫ ሰጥቶ ድርድር እንደሚጀመር አሳውቋል።

ታጣቂ ቡድኑ ከፌደራል መንግሥቱ ጋር ልዩነቶችን በንግግር ለመፍታት ከስምምነቱ መደረሱን ባወጣው መግለጫ አረጋግጧል።

" የኢትዮጵያ መንግሥት ለድርድር ያስቀመጥነውን ቅድመ ሁኔታ ተቀብሏል " ያለው ታጣቂው ቡድን " ገለልተኛ ሦስተኛ ወገን ባለበት በድርድሩ ወቅት በዘላቂነት ግልጸኝነት እንዲኖር ተስማምተናል " ብሏል።

በሌላ በኩል የታጣቂ ቡድኑ መንግሥት ድርጅቱን  " ሸኔ " ብሎ ከመጥራት እንዲቆጠብ አሳስቧል።

" የድርጅታችን መጠሪያ፤ የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ነው ፡ ሌላ ስያሜ ስህተት ከመሆኑም በላይ ማንነታችንን እና ዓላማችንን የሚወክል አይሆንም " ሲል ገልጿል።

ካመንግሥት ይህን አይነት የተሳሳተ መረጃ ከማሰራጨት ሊቆጠብ ይገባልም ብሏል።

የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት ከመንግስት ጋር ያለውም ልዩነቶች በንግግር ለመፍታት ቀጠሮ መያዙ " ለፍትሕ፣ እኩልነት እና የራስን እድል በራስ ለመወሰን የለውጥ ምዕራፍ ጅማሮ ነው " ብሏል።

ከዚሁ ከድርድር ጋር በተያያዘ መረጃ ፤ የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት ከፍተኛ አዛዥ አማካሪ ነኝ ያሉት አቶ ጅሬኛ ጉዳታ ለኦሮሚያ ሚዲያ ኔትዎርክ በሰጡት ቃለ ምልልስ በታንዛኒያ የሚደረገው ድርድር ረቡዕ እንደሚጀምር አረጋግጣለሁኝ ብለዋል።

በታንዛኒያ የሚደረገው መድረክ የሂደት ማበጀት መሆኑን ገልጸዋል። በዚህ መድረክ ማነው ሶስተኛው ወገን፣ በምን መልኩ ነው ሂደቱ የሚካሄደው ፣ የደህንነት ማረጋገጫ የሚያደርገው ማነው ? የሚሉና መሰል ጉዳዮች የሚወሰንበት ነው ብለዋል።

አቶ ጅሬኛ ድርድሩን እያማቻቹ ያሉ አካላት የኖርዌይ እና ኬንያ መንግሥታት መሆናቸውን ገልጸው ከአውሮፓም በሂደቱ ውስጥ እየተሳተፉ ያሉ ዲፕሎማቶች መኖራቸውን ጠቁመዋል። አሜሪካ እና የአውሮፓ ህብረትም በሂደቱ የመሳተፍ ፍላጎት እንዳላቸው እኙሁ የሰራዊቱ ከፍተኛ አዛዥ አማካሪ እንደሆኑ የገለፁት አቶ ጅሬኛ አሳውቀዋል።

" ድርድር መደረጉ እና ሰላም እንዲሰፍን የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት ከፍተኛ ፍላጎት አለው " ያሉት አቶ ጅሬኛ ፤ " ሂደቱ ተስፋ ሰጪ ነው " ብለዋል።

@tikvahethiopia
#Gondar

ታሪካዊቷ የጎንደር ከተማ አዲስ ከንቲባ ተሾመላት።

አቶ ባዩህ አቡሃይ በዛሬው ዕለት የጎንደር ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ሆነው ተሹመዋል።

የጎንደር ከተማ ምክር ቤት ዛሬ እያካሄደ በሚገኘው 4ኛ ዙር 10ኛ ዓመት 3ኛ መደበኛ ጉባኤ ነው አቶ ባዩህ አቡሃይ የጎንደር ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አድርጎ የሾመው።

ምንጭ፦ የጎንደር ኮሚኒኬሽን

@tikvahethiopia
#ብሔራዊ_ፈተና

" እስካሁን የመፈተኛ ጊዜ አልተገለጸም " - የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት

የ2015 ት/ት ዘመን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ተፈታኞች የፈተና ምዝገባ እስከ ሚያዝያ 20/2015 ዓ/ም ድረስ ብቻ እንደሚካሄድ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል።

አገልግሎቱ ፥ ማንኛውም የስም፣ የፆታ፣ የተፈጥሮ/የማህበራዊ ዘርፍ እና የፎቶ ማስተካከያ ከፈተና በፊት ስለማይደረግ እያንዳንዱ ተፈታኝና እና መዝጋቢ ትክክለኛነቱን የማጣራትና የማረጋገጥ ኃላፊነት አለበት ብሏል።

ይህ መሆን ያለበትም ምዝገባው በበየነ መረብ በመሆኑ በትምህርት ቤት ደረጃ የተካሄደው የምዝገባ መረጃ በቀጥታ በማንም ሳይነካ ወደ ተቋሙ የመረጃ ቋት የሚገባ በመሆኑ ነው ሲል አስረድቷል።

ከሚያዚያ 20/2015 ዓ/ም በኋላ በግለሰብ ወይም በተቋም በኩል የሚመጡ ተመዝጋቢዎችን #አላስተናግድም ሲል በጥብቅ ያሳሰበው አገልግሎቱ ፥ ፈተናው የሚሰጠው በዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ እንደሚሰጥና የመፈተኛ ጊዜን ምዝገባው ከተጠናቀቀ በኋላ እንደሚገለፅ አሳውቋል።

የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ፥ እስካሁን የመፈተኛ ጊዜ አልተገለጸም ያለ ሲሆን ተፈታኞች ተገቢውን ዝግጅት እንዲያደርጉ አሳስቧል።

@tikvahethiopia
#አቢሲንያ_ባንክ #ዛይራይድ

ዛይራይድ በጋራ ሠርተን በጋራ እንደግ እያለ ባለቤትነቱን የሕዝብ ለማድረግ ለአሽከርካሪዎች እና ለማኅበረሰቡ የጀመረዉን የእክሲዮን ሽያጭ ቀጥሏል!
በዚህም መሰረት የአንድ አክሲዮን ዋጋ 1,000 (አንድ ሺህ) ብር፣ የትንሹ አክሲዮን ግዢ ብዛት ለአሽከርካሪዎች 25 (ሃያ አምስት) አክስዮን ወይም ሃያ አምስት ሺህ (25,000) ብር ሲሆን ከአሽከርካሪዎች ውጪ ላሉት የማህበረሰባችን ክፍል ደግሞ 75 (ሰባ አምስት) አክስዮን ወይም ሰባ አምስት ሺህ (75,000) ብር ነው፡፡

የትልቁ አክስዮን ግዢ መጠን ደግሞ ለሁሉም አክስዮን ገዢዎች 5,000 (አምስት ሺህ) አክስዮን ወይም 5 ሚሊዮን ብር መሆኑን በታላቅ ደስታ እንገልጻለን፡፡

የክፍያ አፈጻጸምን በተመለከተ ደግሞ ለማንኛውም የአክስዮን መጠን ግዢ ክፍያ በቅድሚያ (በአክስዮን ግዢ ወቅት) በአንድ ጊዜ ብቻ የሚፈጸም መሆኑን እያሳወቅን አክስዮኑን Visa እና Mastercard ተጠቅመው መግዛት እንደሚችሉ ስንገልፅ በደስታ ነው።

የአክስዮን ግዢውን በኦንላይን ለመፈፀም ከታች የሚገኘውን የዛይራይድ መስፈንጠሪያ ይጠቀሙ፡፡ www.zayride.com
ሆሴዕ ሪልስቴት ለመቄዶንያ አረጋውያን ማዕከል ድጋፍ አደረገ።

ሆሴዕ ሪልስቴት የካፒታል ሆቴል እና ሰፖ እህት ኩባንያ ግምታዊ ወጪያቸው ከአንድ ሚሊዮን ብር በላይ ግምት ያላቸው የሌሊት ልብሶችና የንጽህና መጠበቂያ ቁሳቁስ ድጋፍ አድርጓል።

ሆሴዕ ሪልስቴት ፥ " በአጭር ጊዜ ውስጥ በሪልስቴት ዘርፍ በመንቀሳቀስ በቅርቡ በአያት 49 አካባቢ በ23 ሺህ ካሬ ሜትር ላይ ለ300 አባወራዎች በ2 ዓመት ከስድስት ወር ጊዜ ውስጥ የሪል እስቴት ቤቶችን ገንብቶ በማስረከብ በርካታ ቤቶችን በአጭር ጊዜ በጥራትና በብቃት ገንብቼ ታሪክ ሰርቻለሁ " ብሏል።

የሆሴዕ ትሬዲንግ ሀውስ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ የማነ ገብረሥላሴ ለመቄዶንያ በጎ አድራጎት ማኅበር የአንድ ሚሊየን ብር ግምት ያላቸው የተለያዩ የጽዳት መገልገያ ቁሳቁሶችን በእርዳታ ለግሰዋል።

ሆሴዕ ሪልስቴት ከሚያከናውኗቸው ስኬታማ ሥራዎች ባሻገር በመቄዶንያ አረጋውያንና ህሙማን ማዕከል በመገኘት ትናንት በሙያና በጉልበታቸው ሀገር ላቆሙ አረጋውያንና ልዩ ልዩ ወገኖቻችን ድጋፍ የሚሆን ፦
- አንሶላ፣
-ፎጣ፣
- ብርድልብስ፣
- ፍራሾችን  እና የተለያዩ የጽዳት መጠበቂያ ቁሳቁሶችን በብር 1 ማሊዮን በመግዛት ለመቄዶንያ አረጋውያን እና የአእምሮ ህሙማን ማዕከል መሥራች ለዶ/ር ቢኒያም በለጠ በሆሴዕ ሪልስቴት ም/ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ምትኩ ልዑል አማካኝነት ተበርክቷል፡፡

የሆሴዕ ትሬዲንግ ሀውስ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር ኩባንያው እስከዛሬ የተለያዩ ሀገራዊ ኃላፊነቱን ሲወጣ መቆየቱን የገለፀ ሲሆን በቀጣይም እንደ መቄዶንያ በጎ አድራጎት ማኅበር ላሉ በጎ ተግባር ላይ ለሚሳተፉ ተቋማት የሚደረገው ድጋፍ ተጠናክሮ ይቀጥለል ብሏል።

ስልክ ፦ 6966 or 0902222225 

@tikvahethiopia