ወደ ትግራይ የየብስ ጉዞ ተጀመረ።
" ሰላም ባስ " ከአዲስ አበባ ወደ መቐለ / ከመቐለ ወደ አዲስ አበባ ሲሰጠው የነበረውና በጦርነቱ ምክንያት ተቋርጦ የነበረውን የትራንስፓርት አገልግሎት ጀምሯል።
ከሁለት ዓመታት በኋላ የሰላም ባስ የመንገድ ትራንስፖርት ለመጀመሪያ ጊዜ ከአዲስ አበባ ወደ መቐለ ጉዞ አድርጓል።
ከዚህ በተጨማሪ በዛሬው ዕለት 51 ተጓዞችን በመያዝ ወደ አዲስ አበባ አገልግሎት መስጠት ጀመሩን ለማወቅ ተችሏል።
ድምፂ ወያነ ፤ አገልግሎት መጀመሩን ተከትሎ ትኬት ሲቆርጡ አገኘኃቸው ያላቸው ደንበኞች ፥ ወደ አዲስ አበባ የየብስ ትራንስፖርት በመጀመሩ ደስተኞች መሆናቸውን በመግለፅ ወደ ሌሎች አጎራባች ክልልሎችም ተመሳሳይ አገልግሎት ቢጀመር ሰላሙን ይበልጥ እንደሚያጠናክር ገልፀዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከ " ሰላም ባስ " የትራንስፖርት አገልግሎት ባገኘው መረጃ በየቀኑ ከአዲስ አበባ ወደ መቐለ እና ከመቐለ ወደ አዲስ አበባ ጉዞ የተጀመረ ሲሆን ጉዞው የሚደረገው #በአፋር በኩል ነው።
ፎቶ፦ ሰላም ባስ / ድምፂ ወያነ
@tikvahethiopia
" ሰላም ባስ " ከአዲስ አበባ ወደ መቐለ / ከመቐለ ወደ አዲስ አበባ ሲሰጠው የነበረውና በጦርነቱ ምክንያት ተቋርጦ የነበረውን የትራንስፓርት አገልግሎት ጀምሯል።
ከሁለት ዓመታት በኋላ የሰላም ባስ የመንገድ ትራንስፖርት ለመጀመሪያ ጊዜ ከአዲስ አበባ ወደ መቐለ ጉዞ አድርጓል።
ከዚህ በተጨማሪ በዛሬው ዕለት 51 ተጓዞችን በመያዝ ወደ አዲስ አበባ አገልግሎት መስጠት ጀመሩን ለማወቅ ተችሏል።
ድምፂ ወያነ ፤ አገልግሎት መጀመሩን ተከትሎ ትኬት ሲቆርጡ አገኘኃቸው ያላቸው ደንበኞች ፥ ወደ አዲስ አበባ የየብስ ትራንስፖርት በመጀመሩ ደስተኞች መሆናቸውን በመግለፅ ወደ ሌሎች አጎራባች ክልልሎችም ተመሳሳይ አገልግሎት ቢጀመር ሰላሙን ይበልጥ እንደሚያጠናክር ገልፀዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከ " ሰላም ባስ " የትራንስፖርት አገልግሎት ባገኘው መረጃ በየቀኑ ከአዲስ አበባ ወደ መቐለ እና ከመቐለ ወደ አዲስ አበባ ጉዞ የተጀመረ ሲሆን ጉዞው የሚደረገው #በአፋር በኩል ነው።
ፎቶ፦ ሰላም ባስ / ድምፂ ወያነ
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update የሱዳን ጦር በ72 ሰዓታቱ የተኩስ አቁም ተስማማ። ጦሩ ከዛሬ ጀምሮ ለሶስት ቀን ድረስ ዜጎች የኢድ አልፈጥር በዓልን እንዲያከብሩ፣ እና ለሰብዓዊ ድጋፍ አገልግሎት መሳለጥ ሲባል የተኩስ አቁም ለማድረግ መስማማቱን ዛሬ ማምሻውን አሳውቋል። በጄነራል ቡርሃን የሚመራው የሱዳን ጦር " አማፂያን " ሲል የጠራቸው የRSF ኃይሎች የተኩስ አቁሙን እንዲያከብሩና ይህንን የሚያደናቅፉ ማንኛውም ወታደራዊ…
#SUDAN
የሱዳን ተዋጊ ኃይሎች የተኩስ አቁም ቢያውጁም ውጊያው አሁንም መቀጠሉ ታውቋል ፤ ሀገራት ዜጎቻቸውን ከሱዳን ለማስወጣት ሩጫ ላይ ናቸው።
ትላንት የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ኃይል (RSF) የዒድ አልፈጥር በዓልን ምክንያት በማድረግ የ72 ሰዓታት የተኩስ አቁም ማወጁ፤ የሱዳን ጦርም ምሽት ላይ በተኩስ አቁሙ እንደተስማማ አሳውቀው እንደነበር ይታወሳል።
ነገር ግን ዛሬም በሱዳን የተለያዩ ቦታዎች ውጊያ መኖሩ ተሰምቷል። በካርቱም ካለፉት ቀናት ጋር ሲነፃፀር በተለየ መልኩ የተኩስ ድምፅ ቀንሶ ታይቷል።
በሌላ በኩል ፤ ሀገራት ዜጎቻቸውን ከሱዳን ለማስወጣት ሩጫ ላይ ናቸው። ተዋጊ ኃይሎቹም የውጭ ዜጎች እንዲወጡ ለማመቻቸት ቃል ገብተዋል ተብሏል።
የሱዳን ጦር ፤ የውጭ ዜጎች እና ዲፕሎማቶች ከአሜሪካ ፣ ዩናይትድ ኪንግደም፣ ፈረንሳይ እና ቻይና በጦር አውሮፕላኖች ከካርቱም ኤርፖርት የማስወጣት ስራ በሰዓታት ውስጥ ይጀምራል ብሏል።
ከዚህ ባለፈ በሀገሪቱ የሚገኙ የሳዑዲ አረቢያ ዲፕሎማቶች ከካርቱም ወደ ፖርት ሱዳን ከዚያም ወደ ሳዑዲ አረቢያ እንዲወጡ መደረጉን አስታውቋል። የጆርዳን ዲፕሎማቶችም ዛሬ ወደበኃላ ላይ በተመሳሳይ መንገድ ከአገሪቱ ይወጣሉ ሲል ገልጿል።
በሱዳን የተካሄደ ያለው ውጊያ እጅጉን የከፋው በትልልቅ ከተሞች፣ የዜጎች የመኖሪያ መንደሮች፣ የስራ ቦታዎች ላይ እየተደረገ መሆኑ ሲሆን የሀገሬው ዜጋ እና የሌሎችም ሀገራት ዜጎች ያለ ውሃ ፣ ምግብ ፣ መብራት ቤታቸው ውስጥ ከሳምንት በላይ እንዲቀመጡ አድርጓል።
@tikvahethiopia
የሱዳን ተዋጊ ኃይሎች የተኩስ አቁም ቢያውጁም ውጊያው አሁንም መቀጠሉ ታውቋል ፤ ሀገራት ዜጎቻቸውን ከሱዳን ለማስወጣት ሩጫ ላይ ናቸው።
ትላንት የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ኃይል (RSF) የዒድ አልፈጥር በዓልን ምክንያት በማድረግ የ72 ሰዓታት የተኩስ አቁም ማወጁ፤ የሱዳን ጦርም ምሽት ላይ በተኩስ አቁሙ እንደተስማማ አሳውቀው እንደነበር ይታወሳል።
ነገር ግን ዛሬም በሱዳን የተለያዩ ቦታዎች ውጊያ መኖሩ ተሰምቷል። በካርቱም ካለፉት ቀናት ጋር ሲነፃፀር በተለየ መልኩ የተኩስ ድምፅ ቀንሶ ታይቷል።
በሌላ በኩል ፤ ሀገራት ዜጎቻቸውን ከሱዳን ለማስወጣት ሩጫ ላይ ናቸው። ተዋጊ ኃይሎቹም የውጭ ዜጎች እንዲወጡ ለማመቻቸት ቃል ገብተዋል ተብሏል።
የሱዳን ጦር ፤ የውጭ ዜጎች እና ዲፕሎማቶች ከአሜሪካ ፣ ዩናይትድ ኪንግደም፣ ፈረንሳይ እና ቻይና በጦር አውሮፕላኖች ከካርቱም ኤርፖርት የማስወጣት ስራ በሰዓታት ውስጥ ይጀምራል ብሏል።
ከዚህ ባለፈ በሀገሪቱ የሚገኙ የሳዑዲ አረቢያ ዲፕሎማቶች ከካርቱም ወደ ፖርት ሱዳን ከዚያም ወደ ሳዑዲ አረቢያ እንዲወጡ መደረጉን አስታውቋል። የጆርዳን ዲፕሎማቶችም ዛሬ ወደበኃላ ላይ በተመሳሳይ መንገድ ከአገሪቱ ይወጣሉ ሲል ገልጿል።
በሱዳን የተካሄደ ያለው ውጊያ እጅጉን የከፋው በትልልቅ ከተሞች፣ የዜጎች የመኖሪያ መንደሮች፣ የስራ ቦታዎች ላይ እየተደረገ መሆኑ ሲሆን የሀገሬው ዜጋ እና የሌሎችም ሀገራት ዜጎች ያለ ውሃ ፣ ምግብ ፣ መብራት ቤታቸው ውስጥ ከሳምንት በላይ እንዲቀመጡ አድርጓል።
@tikvahethiopia
#ብርሃን_ባንክ
በሆቴሎች፤ በሱፐርማርኬቶች እና በቅርንጫፎቻችን በሚገኙት የፖስ ማሽኖቻችን የቪዛና ማስተር ካርድዎን ተጠቅመው ግብይትዎን ያቅልሉ፡፡
አዳዲስ እና ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት ከታች የሚገኙትን ሊንኮች በመጫን የማህበራዊ ድህረ-ገጾቻችንን ይቀላቀሉ !
Facebook: https://www.facebook.com/berhanbanksc
Telegram: https://t.iss.one/berhanbanksc
Instagram: https://www.instagram.com/berhanbanksc/
Twitter: https://twitter.com/berhanbanksc
LinkedIn: https://www.linkedin.com/company/76151001
YouTube: https://www.youtube.com/channel/UCvOxWe439dzMSvNnMrjcYVQ
እንደ ስማችን ብርሃን ነው ስራችን!
በሆቴሎች፤ በሱፐርማርኬቶች እና በቅርንጫፎቻችን በሚገኙት የፖስ ማሽኖቻችን የቪዛና ማስተር ካርድዎን ተጠቅመው ግብይትዎን ያቅልሉ፡፡
አዳዲስ እና ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት ከታች የሚገኙትን ሊንኮች በመጫን የማህበራዊ ድህረ-ገጾቻችንን ይቀላቀሉ !
Facebook: https://www.facebook.com/berhanbanksc
Telegram: https://t.iss.one/berhanbanksc
Instagram: https://www.instagram.com/berhanbanksc/
Twitter: https://twitter.com/berhanbanksc
LinkedIn: https://www.linkedin.com/company/76151001
YouTube: https://www.youtube.com/channel/UCvOxWe439dzMSvNnMrjcYVQ
እንደ ስማችን ብርሃን ነው ስራችን!
TIKVAH-ETHIOPIA
#ነሲሓ " ነሲሓ የበጎ አድራጎት እና የልማት ድርጅት " በደብረ ብርሃን የመጠለያ ካምፕ ለሚገኙ ተፈናቃዮች ድጋፍ እያሰባሰበ እንደሚገኝ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አሳውቋል። ድጋፉ " ዘካተል ፊጥራችንን ለወገኖቻችን" በሚል መሪ ቃል የሚሰበሰብ መሆኑን አመልክቷል። የበጎ አደራጎት ድርጅቱ " ሙስሊሞች የምታወጡትን #ዘካተል_ፊጥር በደብረ ብርሃን ለሚገኙ ተፈናቃዮች ድጋፍ ይሆን ዘንድ በሚከተሉት አካውንቶች እያሰባሰበን…
#ደብረብርሃን
ነሲሓ የበጎ አድራጎትና የልማት ድርጅት በደብረ ብርሃን መጠለያ ካምፕ ለሚገኙ ተፈናቃዮች ድጋፍ ማድረጉን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አሳውቋል።
ድርጅቱ ከማኅበረሰቡ ባሰባሰበው ድጋፍ 210 ኩንታል ፉርኖ ዱቄት ከፋብሪካ የገዛ ሲሆን፣ በአጠቃላይ ለ1800 አባወራ ድጋፍ ማድረግ መቻሉን አመልክቷል።
ነሲሓ የበጎ አድራጎትና ልማት ድርጅት ድጋፍ ለሰጡ የማኅበረሰብ ክፍሎች ምስጋናውን አቅርቧል። ድርጅቱ ከቀናት በፊት በደብረ ብርሃን ለሚገኙ ወገኖች ድጋፍ እንዲደረግ ጥሪ ማቅረቡ ይታወቃል።
ከዚህ ቀደም በደብረ ብርሃን መጠለያ ካምፕ በርካታ ወገኖቻችን ተጠልለው እንደሚገኙ መግለፁ ይታወሳል፤ አሁንም ከድጋፍ አድራጊ ድርጅቶች የሚሰራው ስራ ተጠናክሮ መቀጠል ያለበት ቢሆንም የሚመለከተው አካል ግን ዜጎች ወደ ቀደመ ህይወታቸው እንዲመለሱ ማድረግ አለበት።
@tikvahethiopia
ነሲሓ የበጎ አድራጎትና የልማት ድርጅት በደብረ ብርሃን መጠለያ ካምፕ ለሚገኙ ተፈናቃዮች ድጋፍ ማድረጉን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አሳውቋል።
ድርጅቱ ከማኅበረሰቡ ባሰባሰበው ድጋፍ 210 ኩንታል ፉርኖ ዱቄት ከፋብሪካ የገዛ ሲሆን፣ በአጠቃላይ ለ1800 አባወራ ድጋፍ ማድረግ መቻሉን አመልክቷል።
ነሲሓ የበጎ አድራጎትና ልማት ድርጅት ድጋፍ ለሰጡ የማኅበረሰብ ክፍሎች ምስጋናውን አቅርቧል። ድርጅቱ ከቀናት በፊት በደብረ ብርሃን ለሚገኙ ወገኖች ድጋፍ እንዲደረግ ጥሪ ማቅረቡ ይታወቃል።
ከዚህ ቀደም በደብረ ብርሃን መጠለያ ካምፕ በርካታ ወገኖቻችን ተጠልለው እንደሚገኙ መግለፁ ይታወሳል፤ አሁንም ከድጋፍ አድራጊ ድርጅቶች የሚሰራው ስራ ተጠናክሮ መቀጠል ያለበት ቢሆንም የሚመለከተው አካል ግን ዜጎች ወደ ቀደመ ህይወታቸው እንዲመለሱ ማድረግ አለበት።
@tikvahethiopia
#ዘሪሁን_ወዳጆ
አንጋፋው አርቲስት ዘሪሁን ወዳጆ በህመም ምክንያት ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል።
በሙዚቃ ስራዎቹ ለኦሮሞ ህዝብ ትግል ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳበረከተ የሚነገርለት አርቲስት ዘሪሁን በህንድ አገር በሕክምና ላይ እያለ ህይወቱ እንዳለፈ ታውቋል።
የኦሮሚያ ክልል መንግሥት ፤ አርቲስት ዘሪሁን ወዳጆች በህይወት በነበረበት ወቅት ከትውልድ ትውልድ የሚሸጋገሩ ስራዎችን መስራቱንና ለበርካታ አርቲስቶችም ምሳሌ መሆን የቻለ ከህዝብ አእምሮ የማይጠፋ አርቲስት እንደበር ገልጿል።
@tikvahethiopia
አንጋፋው አርቲስት ዘሪሁን ወዳጆ በህመም ምክንያት ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል።
በሙዚቃ ስራዎቹ ለኦሮሞ ህዝብ ትግል ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳበረከተ የሚነገርለት አርቲስት ዘሪሁን በህንድ አገር በሕክምና ላይ እያለ ህይወቱ እንዳለፈ ታውቋል።
የኦሮሚያ ክልል መንግሥት ፤ አርቲስት ዘሪሁን ወዳጆች በህይወት በነበረበት ወቅት ከትውልድ ትውልድ የሚሸጋገሩ ስራዎችን መስራቱንና ለበርካታ አርቲስቶችም ምሳሌ መሆን የቻለ ከህዝብ አእምሮ የማይጠፋ አርቲስት እንደበር ገልጿል።
@tikvahethiopia
#MekelleUniversity
ትግራይ ያሉ ዩኒቨርሲቲዎች ወደ ቀደመው የመማር ማስተማር ስራቸው ለመመለስ ከፍተኛ ርብርብ እያደረጉ ይገኛሉ።
ከነዚህም ውስጥ የኣክሱምና ራያ ዩኒቨርሲቲዎች ወደ ሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች ተመድበው መማር ያልቻሉ ተማሪዎች በአጭር ቀናት ውስጥ በስልክ እየደወሉ እንዲመዘገቡ ጥሪ አቅርበዋል።
ለማስታወሻ ፦ https://t.iss.one/tikvahethiopia/77964
የመቐለ ዩኒቨርሲቲ በተመሳሳይ ለሁሉም በሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች ላልተመደቡ የዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች ጥሪ አቅርቧል።
ዩኒቨርስቲው በጦርነቱ ምክንያት ትምህርት ያቋረጡ የመጀመርያ ዲግሪ ተማሪዎች ቀጥሎ የተቀመጡትን መረጃዎች ከሚያዝያ 16-20/2015 ዓ.ም. ባሉት የስራ ሰዓታት ብቻ ከታች በተቀመጡት ስልክ ቁጥሮች በመጠቀም መረጃዎች እንዲያቀብሉ ጠይቋል።
ተፈላጊ መረጃዎቹ ምንድናቸው ?
👉 ሙሉ ስም
👉 የመታወቅያ ቁጥር
👉 ትምህርት ክፍል
👉 የስንተኛ ኣመት ተማሪ መሆንዎ
እነዚህን መረጃዎች የመላኪያ ስልክ ቁጥሮች ፦
1. EiTM - 0984026089 / 0984026059
2. MIT - 0984026727
3. CHS - 0984023986
4. CVS - 0984024072
5. CLG - 0984023987
6. CSSL - 0984023985
7. CBE - 0984024069
8. IPHC - 0984025512
9. CDAaNR - 0984025593
10. CNCS - 0984025582
11. Other Universities - 0984025589
መቐለ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የፅሁፍ መልእክቱን ሲልኩ #በእንግሊዘኛ እንዲልኩ አሳስቧል።
ዩኒቨርሲቲው በሌሎች የሀገራችን ዩኒቨርሲቲዎች ሲማሩ የነበሩና በጦርነቱ ምክንያት ያቋረጡ የመጀመሪያ ዲግሪ ተማሪዎች ከላት የተጠየቁትን መረጃዎች ፤ከዛ በተጨማሪ ሲማሩበት የነበረውን የዩኒቨርሲቲ ስም በማከል መረጃ እንዲያሳውቁ ጥሪውን አቅርቧል።
በሌላ በኩል ፥ የመቐለ ዩኒቨርሲቲ የድህረ ምረቃ ተማሪዎቹን በቅርብ ጊዜ እንደሚጠራ ገልጿል።
@tikvahethiopia
ትግራይ ያሉ ዩኒቨርሲቲዎች ወደ ቀደመው የመማር ማስተማር ስራቸው ለመመለስ ከፍተኛ ርብርብ እያደረጉ ይገኛሉ።
ከነዚህም ውስጥ የኣክሱምና ራያ ዩኒቨርሲቲዎች ወደ ሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች ተመድበው መማር ያልቻሉ ተማሪዎች በአጭር ቀናት ውስጥ በስልክ እየደወሉ እንዲመዘገቡ ጥሪ አቅርበዋል።
ለማስታወሻ ፦ https://t.iss.one/tikvahethiopia/77964
የመቐለ ዩኒቨርሲቲ በተመሳሳይ ለሁሉም በሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች ላልተመደቡ የዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች ጥሪ አቅርቧል።
ዩኒቨርስቲው በጦርነቱ ምክንያት ትምህርት ያቋረጡ የመጀመርያ ዲግሪ ተማሪዎች ቀጥሎ የተቀመጡትን መረጃዎች ከሚያዝያ 16-20/2015 ዓ.ም. ባሉት የስራ ሰዓታት ብቻ ከታች በተቀመጡት ስልክ ቁጥሮች በመጠቀም መረጃዎች እንዲያቀብሉ ጠይቋል።
ተፈላጊ መረጃዎቹ ምንድናቸው ?
👉 ሙሉ ስም
👉 የመታወቅያ ቁጥር
👉 ትምህርት ክፍል
👉 የስንተኛ ኣመት ተማሪ መሆንዎ
እነዚህን መረጃዎች የመላኪያ ስልክ ቁጥሮች ፦
1. EiTM - 0984026089 / 0984026059
2. MIT - 0984026727
3. CHS - 0984023986
4. CVS - 0984024072
5. CLG - 0984023987
6. CSSL - 0984023985
7. CBE - 0984024069
8. IPHC - 0984025512
9. CDAaNR - 0984025593
10. CNCS - 0984025582
11. Other Universities - 0984025589
መቐለ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የፅሁፍ መልእክቱን ሲልኩ #በእንግሊዘኛ እንዲልኩ አሳስቧል።
ዩኒቨርሲቲው በሌሎች የሀገራችን ዩኒቨርሲቲዎች ሲማሩ የነበሩና በጦርነቱ ምክንያት ያቋረጡ የመጀመሪያ ዲግሪ ተማሪዎች ከላት የተጠየቁትን መረጃዎች ፤ከዛ በተጨማሪ ሲማሩበት የነበረውን የዩኒቨርሲቲ ስም በማከል መረጃ እንዲያሳውቁ ጥሪውን አቅርቧል።
በሌላ በኩል ፥ የመቐለ ዩኒቨርሲቲ የድህረ ምረቃ ተማሪዎቹን በቅርብ ጊዜ እንደሚጠራ ገልጿል።
@tikvahethiopia
የመምህራኑ ጥያቄ ...
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመምህራን ማኅበር በሥሩ ከሚገኙት አባላት መካከል የ29,500 አባላቱ የመኖሪያ ቤት ችግር እንዲፈታለት ከንቲባ አዳነች አቤቤን በደብዳቤ ጠይቋል።
የማኅበሩ ፕሬዚዳንት አቶ ድንቃለም ቶሎሳ ለሪፖርተር ቃለ ምልልስ ሰጥተው ነበር። በዚህ ቃለምልልስ ምን አሉ ?
- ማህበሩ ከሁለት ሳምንት በፊት ለከንቲባዋ በጻፈው ደብዳቤ፣ በአስተዳደሩ ሥር የሚገኙ መምህራን የቤት ጥያቄ እንዲፈታ ጠይቋል፡፡
- የመምህራን ጥያቄ እየበረታ በመምጣቱ ከንቲባዋ ከመምህራን ጋር በ2013 ዓ.ም. በነበራቸው ስብሳሰባ፣ መምህራን በማኅበር ተደራጅተው ቤት እንዲገነቡ እንደሚደረግ ቢገለጽም፣ እስካሁን ምንም ዓይነት ተስፋ ሰጪ ነገር እየታየ አይደለም።
- ለከንቲባዋ በተፃፈው ደብዳቤ ለመምህራን የኑሮ ውድነትን የሚያረግቡ ድጎማዎች እንዲደረጉ፣ ከንቲባዋ በመድረክ ላይ የገቡት ቃል ወደ ታች ወርዶ እንዲፈጸምና በከተማ አስተዳደሩ በተጀመሩ ልማቶች የመምህራን ጥያቄዎች እልባት እንዲያገኙ ተጠይቋል።
- የመምህራን የደመወዝ ጥያቄ የከተማ አስተዳደሩ የችግሩን አሳሳቢነት በመረዳት ከተቻለ በልዩ ትኩረት በከተማው ደረጃ ውሳኔ ሰጥቶበት እንዲፈታ፣ ካልሆነም ደግሞ የሚመለከተው የፌዴራል ተቋም ለጉዳዩ ትኩረት በመስጠት እልባት መስጠት እንዲቻል እንዲደረግ ጥሪ ቀርቧል።
- የኑሮ ውድነት ማረጋጊያ ድጎማ 3,000 ብር የሚሰጥ ቢሆንም፣ ገንዘቡ ከችግሩ ጋር አብሮ የማይሄድ በመሆኑ ቢያንስ በእጥፍ እንዲያድግ መምህራኑ ይፈልጋሉ።
በተጨማሪ ለከንቲባዋ በተፃፈው ደብዳቤ ....
ለመምህራን ሁለተኛ መ/ ቤታቸው የሆነው የመኖሪያ ቤት ጥያቄ፣ ግንቦት 2013 ዓ.ም. መምህራንን ባወያዩበት ወቅት መምህራን በማኅበር ተደራጅተው ቤት እንዲገነቡ እንደሚደረግ የተገለጸ ቢሆንም፣ ነገር ግን እስካሁን በተፈለገው ርቀት ወደ ሥራ አለመገባቱን ያትታል፡፡
በዚህ የተነሳ ባለፉት ወራት ምንም ዓይነት ለውጥ አለመኖሩ መምህራንን ተጠቃሚ ከማድረግ ይልቅ፣ ጉዳዩን በተቃራኒ በጥርጣሬ እንዲያዩት አነሳሽ ምክንያት ከመሆኑም በላይ ተስፋ አስቆራጭነቱ እየሰፋ የመጣ ስለመሆኑ ይገልጻል።
ይህ ጉዳይ መምህራን ቃል የገቡልንን አልተገበሩልንም (አላስተገበሩልንም) የሚል ስሜት ፈጥሮ የመምህራንን ሞራል ያላሸቀ ፣ ቤት ባላቸውና በሌላቸው መምህራን መካከል የፍትሐዊነት ጥያቄ ያስነሳ መሆኑም በደብዳቤው ተመላክቷል፡፡
መምህራን የሚያገኙት የደመወዝ መጠንና በአሁኑ ወቅት ያለው ፦ የቤት ኪራይ ዋጋ፣ በተጨማሪም የኑሮ ውድነት መምህራንን ተረጋግተው እንዳያስተምሩ ጫና እየፈጠረ በመሆኑ ከንቲባዋ ለመምህራኑ በገቡት ቃል መሠረት ለጉዳዩ ልዩ ትኩረት በመስጠት፣ የመምህራን የመኖሪያ ቤት ጥያቄ ምላሽ እንዲያገኝ " አጥብቀን እንጠይቃለን " ብሏል።
በአሁኑ ወቅት ያለውን የኑሮ ውድነት መምህራኑ ከሚያገኙት ደመወዝና የኑሮ መደጎሚያ ጋር ተቋቁሞ መኖር ከባድ መሆኑን የሚያስረዳው ደብዳቤው፣ የከተማ አስተዳደሩ ከዚህ ቀደም ባደረገው የኑሮ መደጎሚያ ላይ ወቅቱን የሚመጥን ማሻሻያ እንዲያደርግ ጠይቋል፡፡
ተጨማሪ ፦ https://telegra.ph/Reporter-04-23
#ሪፖርተር
@tikvahethiopia
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመምህራን ማኅበር በሥሩ ከሚገኙት አባላት መካከል የ29,500 አባላቱ የመኖሪያ ቤት ችግር እንዲፈታለት ከንቲባ አዳነች አቤቤን በደብዳቤ ጠይቋል።
የማኅበሩ ፕሬዚዳንት አቶ ድንቃለም ቶሎሳ ለሪፖርተር ቃለ ምልልስ ሰጥተው ነበር። በዚህ ቃለምልልስ ምን አሉ ?
- ማህበሩ ከሁለት ሳምንት በፊት ለከንቲባዋ በጻፈው ደብዳቤ፣ በአስተዳደሩ ሥር የሚገኙ መምህራን የቤት ጥያቄ እንዲፈታ ጠይቋል፡፡
- የመምህራን ጥያቄ እየበረታ በመምጣቱ ከንቲባዋ ከመምህራን ጋር በ2013 ዓ.ም. በነበራቸው ስብሳሰባ፣ መምህራን በማኅበር ተደራጅተው ቤት እንዲገነቡ እንደሚደረግ ቢገለጽም፣ እስካሁን ምንም ዓይነት ተስፋ ሰጪ ነገር እየታየ አይደለም።
- ለከንቲባዋ በተፃፈው ደብዳቤ ለመምህራን የኑሮ ውድነትን የሚያረግቡ ድጎማዎች እንዲደረጉ፣ ከንቲባዋ በመድረክ ላይ የገቡት ቃል ወደ ታች ወርዶ እንዲፈጸምና በከተማ አስተዳደሩ በተጀመሩ ልማቶች የመምህራን ጥያቄዎች እልባት እንዲያገኙ ተጠይቋል።
- የመምህራን የደመወዝ ጥያቄ የከተማ አስተዳደሩ የችግሩን አሳሳቢነት በመረዳት ከተቻለ በልዩ ትኩረት በከተማው ደረጃ ውሳኔ ሰጥቶበት እንዲፈታ፣ ካልሆነም ደግሞ የሚመለከተው የፌዴራል ተቋም ለጉዳዩ ትኩረት በመስጠት እልባት መስጠት እንዲቻል እንዲደረግ ጥሪ ቀርቧል።
- የኑሮ ውድነት ማረጋጊያ ድጎማ 3,000 ብር የሚሰጥ ቢሆንም፣ ገንዘቡ ከችግሩ ጋር አብሮ የማይሄድ በመሆኑ ቢያንስ በእጥፍ እንዲያድግ መምህራኑ ይፈልጋሉ።
በተጨማሪ ለከንቲባዋ በተፃፈው ደብዳቤ ....
ለመምህራን ሁለተኛ መ/ ቤታቸው የሆነው የመኖሪያ ቤት ጥያቄ፣ ግንቦት 2013 ዓ.ም. መምህራንን ባወያዩበት ወቅት መምህራን በማኅበር ተደራጅተው ቤት እንዲገነቡ እንደሚደረግ የተገለጸ ቢሆንም፣ ነገር ግን እስካሁን በተፈለገው ርቀት ወደ ሥራ አለመገባቱን ያትታል፡፡
በዚህ የተነሳ ባለፉት ወራት ምንም ዓይነት ለውጥ አለመኖሩ መምህራንን ተጠቃሚ ከማድረግ ይልቅ፣ ጉዳዩን በተቃራኒ በጥርጣሬ እንዲያዩት አነሳሽ ምክንያት ከመሆኑም በላይ ተስፋ አስቆራጭነቱ እየሰፋ የመጣ ስለመሆኑ ይገልጻል።
ይህ ጉዳይ መምህራን ቃል የገቡልንን አልተገበሩልንም (አላስተገበሩልንም) የሚል ስሜት ፈጥሮ የመምህራንን ሞራል ያላሸቀ ፣ ቤት ባላቸውና በሌላቸው መምህራን መካከል የፍትሐዊነት ጥያቄ ያስነሳ መሆኑም በደብዳቤው ተመላክቷል፡፡
መምህራን የሚያገኙት የደመወዝ መጠንና በአሁኑ ወቅት ያለው ፦ የቤት ኪራይ ዋጋ፣ በተጨማሪም የኑሮ ውድነት መምህራንን ተረጋግተው እንዳያስተምሩ ጫና እየፈጠረ በመሆኑ ከንቲባዋ ለመምህራኑ በገቡት ቃል መሠረት ለጉዳዩ ልዩ ትኩረት በመስጠት፣ የመምህራን የመኖሪያ ቤት ጥያቄ ምላሽ እንዲያገኝ " አጥብቀን እንጠይቃለን " ብሏል።
በአሁኑ ወቅት ያለውን የኑሮ ውድነት መምህራኑ ከሚያገኙት ደመወዝና የኑሮ መደጎሚያ ጋር ተቋቁሞ መኖር ከባድ መሆኑን የሚያስረዳው ደብዳቤው፣ የከተማ አስተዳደሩ ከዚህ ቀደም ባደረገው የኑሮ መደጎሚያ ላይ ወቅቱን የሚመጥን ማሻሻያ እንዲያደርግ ጠይቋል፡፡
ተጨማሪ ፦ https://telegra.ph/Reporter-04-23
#ሪፖርተር
@tikvahethiopia
#ነዳጅ #አዲስአበባ
በአዲስ አበባ ከነገ ሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት በዲጂታል የክፍያ አማራጮች ብቻ ይደረጋል።
ይህንንም ተከትሎ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከኤግልላየን ሲስተም ቴክኖሎጂ ጋር በመተባበር ያቀረበውን #ነዳጅ የተባለ መተግበርያ በመጠቀም ከ900 በላይ የሚሆኑ ማደያዎች ላይ የነዳጅ ግብይት መፈፀም የሚያስችል አሰራራር አስተዋውቋል።
የነዳጅ መተግበሪያን በመጠቀም እንዴት መገበያየት ይቻላል ?
- በመጀመሪያ የነዳጅ መተግበሪያን ከፕሌይ ስቶር ወይም አፕ ስቶር ያውርዱ፤
- ሙሉ መረጃዎን በማስገባት መተግበሪያው ላይ ይመዝገቡ ወዲያውኑ የነዳጅ መለያ ቁጥር በ አጭር የጽሁፍ መልዕክት ይደርስዎታል።
- በመቀጠል መተግበርያው ላይ የተሽከርካሪዎን የሰሌዳ ቁጥር በማስገባት ተሽከርካሪዎን ይመዝግቡ።
- የነዳጅ መለያ ቁጥርዎን በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሞባይል ባንኪንግ Utility ውስጥ በመግባት Utility payment በመምረጥ በመልእክት የደረሰንን የነዳጅ ID አስገብተን Link ማድረግ ወይንም በአቅራቢያዎት ወደሚገኝ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቅርንጫፍ በመሄድ ከሂሳብ አካውንትዎ ጋር ያስተሳስሩ።
ከዚህ በኋላ ቀጥታ ከሂሳብ አካውንትዎ ግብይት መፈጸም ብቻ !
- ነዳጅ ለመቅዳት ማደያ በሚሄዱበት ወቅት የነዳጅ ቀጂ ባለሙያው የሰሌዳ ቁጥርዎን ፣ የሚቀዱትን የነዳጅ መጠን እና የገንዘብ መጠን በ(ነዳጅ ቀጂው) መተግበሪያ ላይ በማስገባት ግብይቱን ያስጀምራል።
- ወዲያውኑ በሚደርስዎት የአጭር የፅሁፍ መልዕክት የሚቀዱትን የነዳጅ መጠን እና የገንዘብ መጠን ትክክል መሆኑን በማረጋገጥ የሚስጥር ቁጥሩን(OTP) ለነዳጅ ቀጂ ባለሙያው በመንገር ግብይቱን ያጠናቅቁ።
ነዳጅን ለየት የሚያደርገው ፦
አንድ ጊዜ ብቻ ከሂሳብ አካውንትዎ ጋር በማስተሳሰር ቀጥታ ከአካውንትዎ የነዳጅ ግብይት የሚፈጽሙበት መሆኑ!
በአቅራቢያዎ ያሉ ነዳጅ ማደያዎችን እንዲሁም ነዳጅ መኖሩን እና አለመኖሩን አረጋግጠው መሄድ የሚያስችሎትን አማራጭ ይዞ መምጣቱ!
አንዴ በመተግበሪያው ላይ ከተመዘገቡ በኋላ የስማርት ስልክ አለማስፈለጉ!
መተግበሪያውን ለማውረድ ?
ፕላይ ስቶር:https://play.google.com/store/apps/details?id=com.eaglelionsystems.nedaj
አፕስቶር : https://apps.apple.com/us/app/nedaj/id1639807926
አሰራሩ በሀገሪቱ በሚገኙ ሁሉም ማደያዎች ማከናወን ይቻላል።
#ነዳጅ #CBE #ኤግልላየን
በአዲስ አበባ ከነገ ሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት በዲጂታል የክፍያ አማራጮች ብቻ ይደረጋል።
ይህንንም ተከትሎ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከኤግልላየን ሲስተም ቴክኖሎጂ ጋር በመተባበር ያቀረበውን #ነዳጅ የተባለ መተግበርያ በመጠቀም ከ900 በላይ የሚሆኑ ማደያዎች ላይ የነዳጅ ግብይት መፈፀም የሚያስችል አሰራራር አስተዋውቋል።
የነዳጅ መተግበሪያን በመጠቀም እንዴት መገበያየት ይቻላል ?
- በመጀመሪያ የነዳጅ መተግበሪያን ከፕሌይ ስቶር ወይም አፕ ስቶር ያውርዱ፤
- ሙሉ መረጃዎን በማስገባት መተግበሪያው ላይ ይመዝገቡ ወዲያውኑ የነዳጅ መለያ ቁጥር በ አጭር የጽሁፍ መልዕክት ይደርስዎታል።
- በመቀጠል መተግበርያው ላይ የተሽከርካሪዎን የሰሌዳ ቁጥር በማስገባት ተሽከርካሪዎን ይመዝግቡ።
- የነዳጅ መለያ ቁጥርዎን በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሞባይል ባንኪንግ Utility ውስጥ በመግባት Utility payment በመምረጥ በመልእክት የደረሰንን የነዳጅ ID አስገብተን Link ማድረግ ወይንም በአቅራቢያዎት ወደሚገኝ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቅርንጫፍ በመሄድ ከሂሳብ አካውንትዎ ጋር ያስተሳስሩ።
ከዚህ በኋላ ቀጥታ ከሂሳብ አካውንትዎ ግብይት መፈጸም ብቻ !
- ነዳጅ ለመቅዳት ማደያ በሚሄዱበት ወቅት የነዳጅ ቀጂ ባለሙያው የሰሌዳ ቁጥርዎን ፣ የሚቀዱትን የነዳጅ መጠን እና የገንዘብ መጠን በ(ነዳጅ ቀጂው) መተግበሪያ ላይ በማስገባት ግብይቱን ያስጀምራል።
- ወዲያውኑ በሚደርስዎት የአጭር የፅሁፍ መልዕክት የሚቀዱትን የነዳጅ መጠን እና የገንዘብ መጠን ትክክል መሆኑን በማረጋገጥ የሚስጥር ቁጥሩን(OTP) ለነዳጅ ቀጂ ባለሙያው በመንገር ግብይቱን ያጠናቅቁ።
ነዳጅን ለየት የሚያደርገው ፦
አንድ ጊዜ ብቻ ከሂሳብ አካውንትዎ ጋር በማስተሳሰር ቀጥታ ከአካውንትዎ የነዳጅ ግብይት የሚፈጽሙበት መሆኑ!
በአቅራቢያዎ ያሉ ነዳጅ ማደያዎችን እንዲሁም ነዳጅ መኖሩን እና አለመኖሩን አረጋግጠው መሄድ የሚያስችሎትን አማራጭ ይዞ መምጣቱ!
አንዴ በመተግበሪያው ላይ ከተመዘገቡ በኋላ የስማርት ስልክ አለማስፈለጉ!
መተግበሪያውን ለማውረድ ?
ፕላይ ስቶር:https://play.google.com/store/apps/details?id=com.eaglelionsystems.nedaj
አፕስቶር : https://apps.apple.com/us/app/nedaj/id1639807926
አሰራሩ በሀገሪቱ በሚገኙ ሁሉም ማደያዎች ማከናወን ይቻላል።
#ነዳጅ #CBE #ኤግልላየን
#ድርድር
የኢትዮጵያ መንግሥት ከሸኔ ወይም እራሱን የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት እያለ ከሚጠራው ታጣቂ ቡድን ጋር የሚደረገው ድርድር ከነገ ወዲያ በታንዛኒያ እንደሚጀመር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ዛሬ ገልጸዋል።
ይህንን ያሳወቁት ፥ በሰሜን ኢትዮጵያ የነበረው ግጭት በሰላም ስምምት እንዲቋጭ ቁልፍ ሚና ለነበራቸው አካላት የምስጋና እና የዕውቅና ሥነ ስርዓት በተካሄደበት ወቅት ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ፤ የወለጋ ሕዝብ እፎይ እንዲል ሁሉም ወገን የበኩሉን እንዲያደርግ ጥሪ አቅርበዋል።
በሌላ በኩል በቀጣዩ ሣምንት በብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት የተመራ ልዑክ ወደ መቐለ እንደሚያቀና ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሳውቀዋል።
ልዑኩ የሁሉንም ክልሎች ርዕሳነ መስተዳድሮች ያካተተ እንደሚሆን ነው ጠቅላይ ሚኒስትሩ የተናገሩት፡፡
ፎቶ፦ ኤፍቢሲ
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ መንግሥት ከሸኔ ወይም እራሱን የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት እያለ ከሚጠራው ታጣቂ ቡድን ጋር የሚደረገው ድርድር ከነገ ወዲያ በታንዛኒያ እንደሚጀመር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ዛሬ ገልጸዋል።
ይህንን ያሳወቁት ፥ በሰሜን ኢትዮጵያ የነበረው ግጭት በሰላም ስምምት እንዲቋጭ ቁልፍ ሚና ለነበራቸው አካላት የምስጋና እና የዕውቅና ሥነ ስርዓት በተካሄደበት ወቅት ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ፤ የወለጋ ሕዝብ እፎይ እንዲል ሁሉም ወገን የበኩሉን እንዲያደርግ ጥሪ አቅርበዋል።
በሌላ በኩል በቀጣዩ ሣምንት በብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት የተመራ ልዑክ ወደ መቐለ እንደሚያቀና ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሳውቀዋል።
ልዑኩ የሁሉንም ክልሎች ርዕሳነ መስተዳድሮች ያካተተ እንደሚሆን ነው ጠቅላይ ሚኒስትሩ የተናገሩት፡፡
ፎቶ፦ ኤፍቢሲ
@tikvahethiopia