TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.7K photos
1.61K videos
216 files
4.36K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
"የማረጋጋት ስራ እየሰራሁ ነው" - መከላከያ

የሀገር መከላከያ ሰራዊት ግጭት ተከስቶ በነበረባቸው በአማራ ክልል የኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር እና በሰሜን ሸዋ ዞኖች መካከል በመግባት የማረጋጋት ስራ እያከናወነ እንደሚገኝ አስታውቋል፡፡

የኢፌዴሪ መከላከያ ሚንስቴር የማረጋጋት ስራውን በመስራት ላይ የሚገኝው የአማራ ክልል መንግስት ባቀረበለት ጥሪ መሰረት እንደሆነ ገልጿል፡፡

አሁን ላይ አካባቢዎቹ #እየተረጋጉ ቢመጡም አልፎ አልፎ በመንገድ ዳርቻዎች ላይ #የተኩስ ልውውጦች አሉ ነው የተባለው፡፡ የተኩስ ልውውጡ የሚሰማው በገጠራማ አካባቢዎች መሆኑ ነው የተነገረው፡፡

አካባቢዎቹ ሰፊ እንደመሆናቸው በብቃት ለመቆጣጠር #ተጨማሪ ሀይል ወደ ስፍራዎቹ #እየገባ መሆኑን ሚንስቴሩ ይፋ አድርጓል፡፡

ተዘግተው ያሉ የደሴ፣ ኮምቦልቻ፣ ደብረ ሲናና እና ደብረ በርሃን መንገዶችን የማስከፈት ስራ #እንደሚከናወንም ተጠቁሟል፡፡

ምንጭ-#ፋና
@tsegabwolde @tikvahethiopia