TIKVAH-ETHIOPIA
" ክስ መቋረጥን ተከትሎ ከእስር የመፍታት ስራ ተጀምሯል " - አቶ ጌታቸው ረዳ በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራ የልዑካን ቡድን አዲስ አበባ ውስጥ ከፌዴራል መንግስት ጋር እየመከረ ይገኛል። ቡድኑ ከፌዴራል መንግስት ጋር እየተወያየ የሚገኘው በትግራይ መልሶ ማቋቋም እና ሌሎች ወሳኝ በሆኑ ጉዳዮች ላይ ስለመሆኑ ተነግሯል። ከዚህ ባለፈ ልዑኩ በአዲስ አበባ ካሉ የትግራይ…
የአንድ ሳምንቱ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ልዑክ የአዲስ አበባ ቆይታ ምን ይመስል ነበረ ?
በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ የተመራው ልዑካን ቡድን ከፌዴራል እና ከክልል አመራሮች ጋር ያደረገውን ምክክር አጠናቆ ዛሬ መቐለ ገብቷል።
ልዑካን ቡድኑ ለአንድ ሳምንት ያህል የተደረገው ምክክር የተጀመረው የሰላም ሂደት የተሟላ እንዲሆን በማድረግ አንፃር ስኬታማ ነበር ብሏል።
ምክክሩ የነበረው ፦
- የትግራይ ግዛታዊ አንድነትን ወደ ቦታው መመለስ፣
- በጀት እንዲለቀቅ ማድረግ፣
- ትግራይን መልሶ ማቋቋም እና መገንባት
- እስረኞች መፍታት የሚሉት ትኩረት ተሰጥቷቸው ውይይት ከተደረጉባቸው ጉዳዮች መካከል እንደሆኑ ተነግሯል።
ምክክሩን በተመለከተ የልዑካን ቡድኑ አባል ዶ/ር ሃጎስ ጎደፋይ ምን አሉ ?
" በወሳኝ ጉዳዮች ላይ እና በልማት ስራዎች ደጋፊ በሚሆኑበት ላይ በግልፅ እና በቅርበት መወያየት አስፈላጊ ስለነበር በተለይ በበጀት ጥያቄ፣ የግዛት አንድነት፣ እስረኞች መፍታት፣ ሰብዓዊ እርዳታ ሁሉም ጉዳዮች ላይ የፌዴራል መንግስት የድርሻውን እንዲያበረክት በሚያስችል መንገድ ሰፊ ውይይት አድርገናል ፤ በልዩ ሁኔታ በተለይ ከፌዴራል መንግስት ጋር ተነጋግረናል።
የሚኒስቴር መስሪያ ቤቶችም በአካል መጥተው የሚናጋገሩበትን መንገድ የሚጠርግ ነው ፤ መልካም ጅማሮም ታይቷል።
ካሳ፣ የደረሰ ውድመት እንዲሁም ማግኘት ስላለብን በጀት ወዘተ ተነጋግረናል፣ በፓርላማ የተወሰነው የ2015 በጀት እንዲለቀቅልን አሁን ተወስኗል። ሌላው በአስቸኳይ መፈታት ያሉባቸው ጉዳዮች በአፋጣኝ እንዲፈቱ ተነጋግረናል። "
በሌላ በኩል ፤ የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት ትግራይን መልሶ በማቋቋም ሂደት በሁሉም መስክ የበኩሉን እንደሚወጣ ዝግጅት ማጠናቀቁን የክልሉ ፕሬዜዳንት አቶ ሽመልስ አብዲሳ ተናግረዋል።
አቶ ሽመልስ አብዲሳ ከትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ልዑካን ጋር የተወያዩ ሲሆን ውይይቱን ተከትሎ በሰጡት ቃል ተከታዩን ብለዋል ፦
" በትግራይ ባለፉት ዓመታት ከፍተኛ ጉዳት በህዝቡ ላይ ደርሷል፣ ብዙ ጥፋት ነው የተፈፀመው ያንን ከመሰረቱ በሚቀይር መንገድ ጠንክሮ መስራት ያስፈልጋል።
የኦሮሚያ ክልል እዚህ ውስጥ ኃላፊነቱን በመወጣት ግዴታ አለበት፣ የትግራይ ህዝብ ህዝባችን ነው የራሳችን ነው ፤ ለዚህ ህዝባችን የሚያስፈልገውን ልክ ኦሮሚያ ክልል እንደምናደርገው ትኩረት አድርገን እዛ የሚሰሩትን ስራዎች መስራት መቀየር ያስፍልጋል።
ዘር በማቅረብ፣ ቴክኖሎጂ በማቅረብ፣ ችግኝ በማቅረብ፣ የተለያዩ ፕሮጀክቶችን በማገዝ ልክ እንደ አንድ ሀላፊነት ወስደን የክልላችን መንግስት ትኩረት አድርጎ በትግራይ ያሉ ስራዎች ላይ እንሳተፋለን ከኛ የሚጠበቀውን ሁሉ እናደርጋለን። "
Credit : TIGRAI TV
@tikvahethiopia
በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ የተመራው ልዑካን ቡድን ከፌዴራል እና ከክልል አመራሮች ጋር ያደረገውን ምክክር አጠናቆ ዛሬ መቐለ ገብቷል።
ልዑካን ቡድኑ ለአንድ ሳምንት ያህል የተደረገው ምክክር የተጀመረው የሰላም ሂደት የተሟላ እንዲሆን በማድረግ አንፃር ስኬታማ ነበር ብሏል።
ምክክሩ የነበረው ፦
- የትግራይ ግዛታዊ አንድነትን ወደ ቦታው መመለስ፣
- በጀት እንዲለቀቅ ማድረግ፣
- ትግራይን መልሶ ማቋቋም እና መገንባት
- እስረኞች መፍታት የሚሉት ትኩረት ተሰጥቷቸው ውይይት ከተደረጉባቸው ጉዳዮች መካከል እንደሆኑ ተነግሯል።
ምክክሩን በተመለከተ የልዑካን ቡድኑ አባል ዶ/ር ሃጎስ ጎደፋይ ምን አሉ ?
" በወሳኝ ጉዳዮች ላይ እና በልማት ስራዎች ደጋፊ በሚሆኑበት ላይ በግልፅ እና በቅርበት መወያየት አስፈላጊ ስለነበር በተለይ በበጀት ጥያቄ፣ የግዛት አንድነት፣ እስረኞች መፍታት፣ ሰብዓዊ እርዳታ ሁሉም ጉዳዮች ላይ የፌዴራል መንግስት የድርሻውን እንዲያበረክት በሚያስችል መንገድ ሰፊ ውይይት አድርገናል ፤ በልዩ ሁኔታ በተለይ ከፌዴራል መንግስት ጋር ተነጋግረናል።
የሚኒስቴር መስሪያ ቤቶችም በአካል መጥተው የሚናጋገሩበትን መንገድ የሚጠርግ ነው ፤ መልካም ጅማሮም ታይቷል።
ካሳ፣ የደረሰ ውድመት እንዲሁም ማግኘት ስላለብን በጀት ወዘተ ተነጋግረናል፣ በፓርላማ የተወሰነው የ2015 በጀት እንዲለቀቅልን አሁን ተወስኗል። ሌላው በአስቸኳይ መፈታት ያሉባቸው ጉዳዮች በአፋጣኝ እንዲፈቱ ተነጋግረናል። "
በሌላ በኩል ፤ የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት ትግራይን መልሶ በማቋቋም ሂደት በሁሉም መስክ የበኩሉን እንደሚወጣ ዝግጅት ማጠናቀቁን የክልሉ ፕሬዜዳንት አቶ ሽመልስ አብዲሳ ተናግረዋል።
አቶ ሽመልስ አብዲሳ ከትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ልዑካን ጋር የተወያዩ ሲሆን ውይይቱን ተከትሎ በሰጡት ቃል ተከታዩን ብለዋል ፦
" በትግራይ ባለፉት ዓመታት ከፍተኛ ጉዳት በህዝቡ ላይ ደርሷል፣ ብዙ ጥፋት ነው የተፈፀመው ያንን ከመሰረቱ በሚቀይር መንገድ ጠንክሮ መስራት ያስፈልጋል።
የኦሮሚያ ክልል እዚህ ውስጥ ኃላፊነቱን በመወጣት ግዴታ አለበት፣ የትግራይ ህዝብ ህዝባችን ነው የራሳችን ነው ፤ ለዚህ ህዝባችን የሚያስፈልገውን ልክ ኦሮሚያ ክልል እንደምናደርገው ትኩረት አድርገን እዛ የሚሰሩትን ስራዎች መስራት መቀየር ያስፍልጋል።
ዘር በማቅረብ፣ ቴክኖሎጂ በማቅረብ፣ ችግኝ በማቅረብ፣ የተለያዩ ፕሮጀክቶችን በማገዝ ልክ እንደ አንድ ሀላፊነት ወስደን የክልላችን መንግስት ትኩረት አድርጎ በትግራይ ያሉ ስራዎች ላይ እንሳተፋለን ከኛ የሚጠበቀውን ሁሉ እናደርጋለን። "
Credit : TIGRAI TV
@tikvahethiopia
#ETHIOPIA
ኢትዮጵያውያን ደማቅ አሻራቸውን ያሳረፉትበት የታላቁ ህዳሴ ግድብ የመሰረት ድንጋዩ ከተጣለ ዛሬ 12 ዓመት ደፍኗል።
ዛሬ ላይ ኃይል ማመንጨት የጀመረው ግድቡ ስራው ሙሉ በሙሉ ወደማለቁ እየተቃረበ ይገኛል።
ይህ ግድብ ኢትዮጵያውያን ብዙ ዋጋ የከፈሉበት፣ አሁንም እየከፈሉበት የሚገኝ የሀገር እና የህዝብ ኩራት ሀብት ነው።
@tikvahethiopia
ኢትዮጵያውያን ደማቅ አሻራቸውን ያሳረፉትበት የታላቁ ህዳሴ ግድብ የመሰረት ድንጋዩ ከተጣለ ዛሬ 12 ዓመት ደፍኗል።
ዛሬ ላይ ኃይል ማመንጨት የጀመረው ግድቡ ስራው ሙሉ በሙሉ ወደማለቁ እየተቃረበ ይገኛል።
ይህ ግድብ ኢትዮጵያውያን ብዙ ዋጋ የከፈሉበት፣ አሁንም እየከፈሉበት የሚገኝ የሀገር እና የህዝብ ኩራት ሀብት ነው።
@tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#ማስታወሻ
"... የዚህ ታላቅ ፕሮጀክት ጥቅም በኢትዮጵያ ብቻ የተወሰነ አይደለም፤ሁሉንም ጎረቤቶቻችን በተለይም የታችኛው ተፋሰስ ሀገሮች የሆኑትን ሱዳን እና ግብፅን በእጅጉ የሚጠቅም ነው።
ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ ወንዙ ተሸክሞት ይሄድ የነበረው ደለል ስለሚቀር በግብፅ እና በሱዳን ያሉ ግድቦች በተለይም በደለል እየተሞላ የሚሰጠው ጥቅም በከፍተኛ መጠን የቀነሰው የሱዳን የሮሰሪስ ግድብ ከዚህ አደጋ ነፃ ይሆናል።
.
.
ጥቅሙ ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ለጎረቤት ሀገሮች በተለይ ለሱዳን እና ግብፅ ጭምር በመሆኑ ፍትህ የሰፈነበት ሁኔታ ቢኖር የግድቡን ወጪ 3ቱም ሀገራት ሊሸፍኑት በተገባ ነበር።
እያንዳንዱ ሀገር ከግድቡ በሚያገኘው ጥቅም ልክ ወጪውን ይሸፍን ቢባል ሱዳን የወጪውን 30%፣ግብፅ የወጪውን 20% መሸፈን በተገባቸው ነበር።
ይሁንና በአባይ ወንዝ አጠቃቀም ዙሪያ እንዲህ አይነቱ ገንቢና ፍትሃዊ አሰራር ሊሰፍን አልቻለም፤በመሆኑም ወጪው በሙሉ ኢትዮጵያ ለመሸፈን ተገዳለች።
ይባስ ብሎ ግድቡን ለመስራት ብድር እና እርዳታ እንዳናገኝ የተለያዩ ኃይሎች ባደረጉት ከፍተኛ ርብርብ ምክንያት የፕሮጀክቱን ወጪ ለመሸፈን የሚተባበረን ሀገር ወይም ተቋም ማግኘት አልቻልንም።
ስለሆነም ወጪውን ብቻችንን ከመሸፈን አልፈን ከራሳችን ቁጠባ ለመሸፈን የምንገደድበት ሁኔታ ተፈጥሯል።
.
.
ያለን አማራጭ አንድም ግድቡን አለመስራት ፥ አለበለዚያ እንደምንም ወጪውን በራሳችን መሸፈን ነው።
ከነዚህ ሁለት ከባድ አማራጮች መካከል የኢትዮጵያ ህዝብ ምርጫ የቱ እንደሚሆን ግልፅ ነው።
በተለመደው ወኔው ምንም ያህል ድሃ ብንሆንም ድህነታችንን ለማስወገድ ማንኛውም መስዋዕነት ለመክፈል ዝግጁ ነን፤ ስለዚህ ፕሮጀክቱ መሰራት አለበት እንደሚል ለአፍታም ያህል አልጠራጠርም። "
የቀድሞ የኢትዮጵያ ጠ/ሚኒስትር አቶ #መለስ_ዜናዊ - መጋቢት 24 ቀን 2003 ዓ.ም ከተናገሩት የተወሰደ።
@tikvahethiopia
"... የዚህ ታላቅ ፕሮጀክት ጥቅም በኢትዮጵያ ብቻ የተወሰነ አይደለም፤ሁሉንም ጎረቤቶቻችን በተለይም የታችኛው ተፋሰስ ሀገሮች የሆኑትን ሱዳን እና ግብፅን በእጅጉ የሚጠቅም ነው።
ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ ወንዙ ተሸክሞት ይሄድ የነበረው ደለል ስለሚቀር በግብፅ እና በሱዳን ያሉ ግድቦች በተለይም በደለል እየተሞላ የሚሰጠው ጥቅም በከፍተኛ መጠን የቀነሰው የሱዳን የሮሰሪስ ግድብ ከዚህ አደጋ ነፃ ይሆናል።
.
.
ጥቅሙ ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ለጎረቤት ሀገሮች በተለይ ለሱዳን እና ግብፅ ጭምር በመሆኑ ፍትህ የሰፈነበት ሁኔታ ቢኖር የግድቡን ወጪ 3ቱም ሀገራት ሊሸፍኑት በተገባ ነበር።
እያንዳንዱ ሀገር ከግድቡ በሚያገኘው ጥቅም ልክ ወጪውን ይሸፍን ቢባል ሱዳን የወጪውን 30%፣ግብፅ የወጪውን 20% መሸፈን በተገባቸው ነበር።
ይሁንና በአባይ ወንዝ አጠቃቀም ዙሪያ እንዲህ አይነቱ ገንቢና ፍትሃዊ አሰራር ሊሰፍን አልቻለም፤በመሆኑም ወጪው በሙሉ ኢትዮጵያ ለመሸፈን ተገዳለች።
ይባስ ብሎ ግድቡን ለመስራት ብድር እና እርዳታ እንዳናገኝ የተለያዩ ኃይሎች ባደረጉት ከፍተኛ ርብርብ ምክንያት የፕሮጀክቱን ወጪ ለመሸፈን የሚተባበረን ሀገር ወይም ተቋም ማግኘት አልቻልንም።
ስለሆነም ወጪውን ብቻችንን ከመሸፈን አልፈን ከራሳችን ቁጠባ ለመሸፈን የምንገደድበት ሁኔታ ተፈጥሯል።
.
.
ያለን አማራጭ አንድም ግድቡን አለመስራት ፥ አለበለዚያ እንደምንም ወጪውን በራሳችን መሸፈን ነው።
ከነዚህ ሁለት ከባድ አማራጮች መካከል የኢትዮጵያ ህዝብ ምርጫ የቱ እንደሚሆን ግልፅ ነው።
በተለመደው ወኔው ምንም ያህል ድሃ ብንሆንም ድህነታችንን ለማስወገድ ማንኛውም መስዋዕነት ለመክፈል ዝግጁ ነን፤ ስለዚህ ፕሮጀክቱ መሰራት አለበት እንደሚል ለአፍታም ያህል አልጠራጠርም። "
የቀድሞ የኢትዮጵያ ጠ/ሚኒስትር አቶ #መለስ_ዜናዊ - መጋቢት 24 ቀን 2003 ዓ.ም ከተናገሩት የተወሰደ።
@tikvahethiopia
#የWFP_ማጠንቀቂያ
የተመድ ዓለም ምግብ ፕሮግራም ለረሃብ የተጋለጡ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎችን ለመመገብ በቢሊዮኖች የሚቆጠር የገንዘብ ድጋፍ ማግኘት ካልተቻለ በሚቀጥሉት ከ12 እስከ 18 ወራት ውስጥ ዓለም፥ የጅምላ ስደትን፣ መረጋጋት የጎደላቸውን ሀገራት እና በረኀብ የተጠቁ ሕፃናትንና አዋቂዎችን ማየት እንደሚጀምር አስጠንቅቋል።
የድርጅቱ ዋና ኃላፊ ዴቪድ ቤስሊ ባለፈው ዐርብ ቃለ ምልልስ ሰጥተው ነበር።
ቤስሊ ምን አሉ ?
- ለረሃብ የተጋለጡ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎችን ለመመገብ #በቢሊዮኖች የሚቆጠር የገንዘብ ድጋፍ ማግኘት ካልተቻለ በሚቀጥሉት ከ12 እስከ 18 ወራት ውስጥ ዓለም፥ የጅምላ ስደትን፣ መረጋጋት የጎደላቸውን ሀገራት እና በረሃብ የተጠቁ ሕፃናትንና አዋቂዎችን ማየት ይጀምራል።
- ባለፈው ዓመት፣ ከአሜሪካና ከጀርመን የተገኘውን ተጨማሪ ድጋፍ ይደነቃል ፤ ቻይና፣ የባሕረ ሠላጤው ሀገራት፣ ቢሊየነር ባዕለ ጸጋዎች እና ሌሎችም ሀገራት፣ ከምንጊዜውም በላይ አሁን ድጋፋቸውን ሊያፋጥኑ ይገባል።
- በ49 ሀገራት ውስጥ አስቸኳይ የሆነ #የምግብ ርዳታ የሚያስፈልጋቸውን 350 ሚሊዮን ሰዎች ለመርዳት 23 ቢሊየን ዶላር ሲሆን ይህ ገንዘብ ላያገኝ ይችላል ፤ ይህ ደግሞ በከፍተኛ ኹኔታ አስጨንቆኛል።
- አሜሪካ የምትሰጠውን የገንዘብ ርዳታ ከ3.5 ቢሊዮን ዶላር ወደ 7.4 ቢሊዮን አሳድጋለች፤ በተመሳሳይ ጀርመንም ከ350 ሚሊየን ዶላር ወደ 1.7 ቢሊዮን ከፍ አድርጋለች ፤ በዓለም ሁለተኛ ትልቁ የሆነውን ኢኮኖሚ የያዘችው ቻይና ባለፈው ዓመት ለተቋሙ የሰጠችው ገንዘብ 11 ሚሊየን ዶላር ብቻ በመሆኑ ድጋፏን ልታሳድግ ይገባል።
- #የነዳጅ_ዋጋ በከፍተኛ ሁኔታ ከመጨመሩ ጋራ ተያይዞ የባሕረ ሠላጤው ሀገራት የበለጠ እገዛ ሊያደርጉ ይችላሉ። በተለይ ከምሥራቅ አፍሪካ፣ ከሰሐራ እና ከሌሎች የመካከለኛው ምሥራቅ ሀገራት ጋራ ግንኙነት ያላቸው የሙስሊም ሀገራት የተሻለ አስተዋፅኦ ማድረግ ይችላሉ።
- ቅድሚያ ሊሰጣቸው የሚገባቸው በአፍሪካ የሳሕል ክልል የሚገኙ ሀገራትና ምሥራቅ ሶማሊያ ፣ ሰሜናዊ ኬንያ ፣ ደቡብ ሱዳን ፣ #ኢትዮጵያ 🇪🇹 ይገኙባቸዋል።
- የዓለም መሪዎች፣ ከፍተኛ የሆነ አለመረጋጋትን ሊያስከትሉ የሚችሉ የሰብአዊ ርዳታ ክፍተቶች ለአሉባቸው ሀገራት ቅድሚያ ሊሰጡ ይገባል።
ዴቪድ ቤስሊ በዓለም ትልቁ ሰብአዊ ርዳታ ሰጪ በሆነው ተቋም የነበራቸውን ሥልጣን በመጪው ሳምንት ለአሜሪካ አምባሳደር ሲንዲ ማኬይን ያስረክባሉ።
#VOA
@tikvahethiopia
የተመድ ዓለም ምግብ ፕሮግራም ለረሃብ የተጋለጡ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎችን ለመመገብ በቢሊዮኖች የሚቆጠር የገንዘብ ድጋፍ ማግኘት ካልተቻለ በሚቀጥሉት ከ12 እስከ 18 ወራት ውስጥ ዓለም፥ የጅምላ ስደትን፣ መረጋጋት የጎደላቸውን ሀገራት እና በረኀብ የተጠቁ ሕፃናትንና አዋቂዎችን ማየት እንደሚጀምር አስጠንቅቋል።
የድርጅቱ ዋና ኃላፊ ዴቪድ ቤስሊ ባለፈው ዐርብ ቃለ ምልልስ ሰጥተው ነበር።
ቤስሊ ምን አሉ ?
- ለረሃብ የተጋለጡ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎችን ለመመገብ #በቢሊዮኖች የሚቆጠር የገንዘብ ድጋፍ ማግኘት ካልተቻለ በሚቀጥሉት ከ12 እስከ 18 ወራት ውስጥ ዓለም፥ የጅምላ ስደትን፣ መረጋጋት የጎደላቸውን ሀገራት እና በረሃብ የተጠቁ ሕፃናትንና አዋቂዎችን ማየት ይጀምራል።
- ባለፈው ዓመት፣ ከአሜሪካና ከጀርመን የተገኘውን ተጨማሪ ድጋፍ ይደነቃል ፤ ቻይና፣ የባሕረ ሠላጤው ሀገራት፣ ቢሊየነር ባዕለ ጸጋዎች እና ሌሎችም ሀገራት፣ ከምንጊዜውም በላይ አሁን ድጋፋቸውን ሊያፋጥኑ ይገባል።
- በ49 ሀገራት ውስጥ አስቸኳይ የሆነ #የምግብ ርዳታ የሚያስፈልጋቸውን 350 ሚሊዮን ሰዎች ለመርዳት 23 ቢሊየን ዶላር ሲሆን ይህ ገንዘብ ላያገኝ ይችላል ፤ ይህ ደግሞ በከፍተኛ ኹኔታ አስጨንቆኛል።
- አሜሪካ የምትሰጠውን የገንዘብ ርዳታ ከ3.5 ቢሊዮን ዶላር ወደ 7.4 ቢሊዮን አሳድጋለች፤ በተመሳሳይ ጀርመንም ከ350 ሚሊየን ዶላር ወደ 1.7 ቢሊዮን ከፍ አድርጋለች ፤ በዓለም ሁለተኛ ትልቁ የሆነውን ኢኮኖሚ የያዘችው ቻይና ባለፈው ዓመት ለተቋሙ የሰጠችው ገንዘብ 11 ሚሊየን ዶላር ብቻ በመሆኑ ድጋፏን ልታሳድግ ይገባል።
- #የነዳጅ_ዋጋ በከፍተኛ ሁኔታ ከመጨመሩ ጋራ ተያይዞ የባሕረ ሠላጤው ሀገራት የበለጠ እገዛ ሊያደርጉ ይችላሉ። በተለይ ከምሥራቅ አፍሪካ፣ ከሰሐራ እና ከሌሎች የመካከለኛው ምሥራቅ ሀገራት ጋራ ግንኙነት ያላቸው የሙስሊም ሀገራት የተሻለ አስተዋፅኦ ማድረግ ይችላሉ።
- ቅድሚያ ሊሰጣቸው የሚገባቸው በአፍሪካ የሳሕል ክልል የሚገኙ ሀገራትና ምሥራቅ ሶማሊያ ፣ ሰሜናዊ ኬንያ ፣ ደቡብ ሱዳን ፣ #ኢትዮጵያ 🇪🇹 ይገኙባቸዋል።
- የዓለም መሪዎች፣ ከፍተኛ የሆነ አለመረጋጋትን ሊያስከትሉ የሚችሉ የሰብአዊ ርዳታ ክፍተቶች ለአሉባቸው ሀገራት ቅድሚያ ሊሰጡ ይገባል።
ዴቪድ ቤስሊ በዓለም ትልቁ ሰብአዊ ርዳታ ሰጪ በሆነው ተቋም የነበራቸውን ሥልጣን በመጪው ሳምንት ለአሜሪካ አምባሳደር ሲንዲ ማኬይን ያስረክባሉ።
#VOA
@tikvahethiopia
#ExodusPhysiotherapy
በኤክሶደስ የፊዚዮቴራፒ ስፔሻሊቲ ክሊኒክ የምንሰጣቸው የህክምና አገልግሎቶች ፦ ለአንገት ፣ ለትክሻ ፣ ለወገብ ህመም ፣ ከዲስክ መንሸራተት ጋር በተያያዘ ለሚመጣ ችግር ፣ ለማዞር ወይንም ሚዛን የመጠበቅ ችግር ፣ ለፊት መጣመም፣ ከስትሮክ በኋላ ለሚመጣ ግማሽ የሰውነት ክፍል መዛል ፣ ለስፖርታዊ ጉዳቶች፣ ከህፃናት የእድገት ውስንነት ጋር በተያያዘ ለሚከሰቱ የእንቅስቃሴ ችግሮች ፣ በአጠቃላይ ከነርቭ ፣ ከጡንቻ ፣ ከመገጣጠሚያ ጋር በተገናኘ ለሚከሰቱ ችግሮች መፍትሄ ያግኙ ይዳኑ !
የስራ ሰዓት ዘወትር ከሰኞ እስከ ቅዳሜ #ከጠዋቱ 2:30 እስከ #ምሽት 1:00 ሰዓት
አድራሻችን ፦ 22 ከመክሊት ህንፃ ፊት ለፊት ባሮ ህንፃ ላይ እንገኛለን፤ ስልክ 0979099909/ 0911039377
በቴሌግራም ቻናላችን ጠቃሚ መረጃ ያግኙ
https://t.iss.one/ExodPhysioClinic
በኤክሶደስ የፊዚዮቴራፒ ስፔሻሊቲ ክሊኒክ የምንሰጣቸው የህክምና አገልግሎቶች ፦ ለአንገት ፣ ለትክሻ ፣ ለወገብ ህመም ፣ ከዲስክ መንሸራተት ጋር በተያያዘ ለሚመጣ ችግር ፣ ለማዞር ወይንም ሚዛን የመጠበቅ ችግር ፣ ለፊት መጣመም፣ ከስትሮክ በኋላ ለሚመጣ ግማሽ የሰውነት ክፍል መዛል ፣ ለስፖርታዊ ጉዳቶች፣ ከህፃናት የእድገት ውስንነት ጋር በተያያዘ ለሚከሰቱ የእንቅስቃሴ ችግሮች ፣ በአጠቃላይ ከነርቭ ፣ ከጡንቻ ፣ ከመገጣጠሚያ ጋር በተገናኘ ለሚከሰቱ ችግሮች መፍትሄ ያግኙ ይዳኑ !
የስራ ሰዓት ዘወትር ከሰኞ እስከ ቅዳሜ #ከጠዋቱ 2:30 እስከ #ምሽት 1:00 ሰዓት
አድራሻችን ፦ 22 ከመክሊት ህንፃ ፊት ለፊት ባሮ ህንፃ ላይ እንገኛለን፤ ስልክ 0979099909/ 0911039377
በቴሌግራም ቻናላችን ጠቃሚ መረጃ ያግኙ
https://t.iss.one/ExodPhysioClinic
ዓለም አቀፍ የነዳጅ ዋጋ ላይ ጭማሪ ታይቷል ፤ ለምን ?
ባለተጠበቀ ሁኔታ የዓለማችን ከፍተኛ የነዳጅ አምራች አገራት #የነዳጅ_ምርትን_ለመቀነስ ከተስማሙ በኋላ የነዳጅ ዋጋ ጭማሪ አሳይቷል።
በዚህም የብሬንት አንድ በርሜል ድፍድፍ ነዳጅ በ5 የአሜሪካ ዶላር ወይም በ7 በመቶ ጨማሪ አሳይቶ ከ85 ዶላር በላይ እየተሸጠ ይገኛል።
የነዳጅ ዋጋ ጭማሪው የመጣው ፦ሳዑዲ አረቢያ፣ ኢራቅ እና ሌሎች በርካታ የባህረ ሰላጤው አገራት በቀን የአንድ ሚሊዮን በርሜል ነዳጅ ምርት ቅነሳ እናደርጋለን ካሉ በኋላ ነው።
የምርት ቅነሳውን ያደረጉት ኦፔክ+ የሚባሉት ነዳጅ አምራች አገራት ሲሆኑ ለዓለም ገበያ ከሚቀርበው የነዳጅ መጠን 40 በመቶውን ይሸፍናሉ።
ሳዑዲ አረቢያ የቀን ምርቷን በ500 ሺህ በርሜል የምትቀንስ ሲሆን ኢራቅ ደግሞ በ211 ሺህ በርሜል የዕለት ምርቷን ትቀንሳለች። የተባበሩት አረብ ኤሜሬቶች፣ ኩዌት፣ አልጄሪያ እና ኦማን ሌሎች የምርት ቅነሳ የሚያደርጉ አገራት ናቸው።
ነዳጅ አምራች አገራቱ የምርት ቅነሳ ማድረጋቸውን ካሳወቁ በኋላ የአሜሪካ ብሔራዊ ደኅንነት ም/ቤት “ የገበያ መረጋጋት በሌለበት በዚህ ወቅት የምርት ቅነሳ ማድረጉ የሚመከር አይደለም - ይህን ግልጽ አድርገናል ” ሲል አሳውቋል።
የሳዑዲ የኢነርጂ ሚኒስቴር ፤ የነዳጅ ምርት ላይ ቅናሽ ማድረግ ያስፈለገው " የነዳጅ ገበያ መረጋጋት ለመፍጥር የተወሰደ የቅድመ ጥናቃቄ እርምጃ ነው " ብሏል።
ናታን ፓይፐር የተባሉ የዘርፉ ተንታኝ በበኩላቸው ነዳጅ አምራቾች ምርታቸውን የቀነሱት በዓለም ምጣኔ ሃብት መቀዛዝ ምክንያት የነዳጅ ዋጋ በበርሜል #ከ80_ዶላር_በታች_እንዳይወርድ በማሰብ ነው ብለዋል።
መረጃው የቢቢሲ ነው።
@tikvahethiopia
ባለተጠበቀ ሁኔታ የዓለማችን ከፍተኛ የነዳጅ አምራች አገራት #የነዳጅ_ምርትን_ለመቀነስ ከተስማሙ በኋላ የነዳጅ ዋጋ ጭማሪ አሳይቷል።
በዚህም የብሬንት አንድ በርሜል ድፍድፍ ነዳጅ በ5 የአሜሪካ ዶላር ወይም በ7 በመቶ ጨማሪ አሳይቶ ከ85 ዶላር በላይ እየተሸጠ ይገኛል።
የነዳጅ ዋጋ ጭማሪው የመጣው ፦ሳዑዲ አረቢያ፣ ኢራቅ እና ሌሎች በርካታ የባህረ ሰላጤው አገራት በቀን የአንድ ሚሊዮን በርሜል ነዳጅ ምርት ቅነሳ እናደርጋለን ካሉ በኋላ ነው።
የምርት ቅነሳውን ያደረጉት ኦፔክ+ የሚባሉት ነዳጅ አምራች አገራት ሲሆኑ ለዓለም ገበያ ከሚቀርበው የነዳጅ መጠን 40 በመቶውን ይሸፍናሉ።
ሳዑዲ አረቢያ የቀን ምርቷን በ500 ሺህ በርሜል የምትቀንስ ሲሆን ኢራቅ ደግሞ በ211 ሺህ በርሜል የዕለት ምርቷን ትቀንሳለች። የተባበሩት አረብ ኤሜሬቶች፣ ኩዌት፣ አልጄሪያ እና ኦማን ሌሎች የምርት ቅነሳ የሚያደርጉ አገራት ናቸው።
ነዳጅ አምራች አገራቱ የምርት ቅነሳ ማድረጋቸውን ካሳወቁ በኋላ የአሜሪካ ብሔራዊ ደኅንነት ም/ቤት “ የገበያ መረጋጋት በሌለበት በዚህ ወቅት የምርት ቅነሳ ማድረጉ የሚመከር አይደለም - ይህን ግልጽ አድርገናል ” ሲል አሳውቋል።
የሳዑዲ የኢነርጂ ሚኒስቴር ፤ የነዳጅ ምርት ላይ ቅናሽ ማድረግ ያስፈለገው " የነዳጅ ገበያ መረጋጋት ለመፍጥር የተወሰደ የቅድመ ጥናቃቄ እርምጃ ነው " ብሏል።
ናታን ፓይፐር የተባሉ የዘርፉ ተንታኝ በበኩላቸው ነዳጅ አምራቾች ምርታቸውን የቀነሱት በዓለም ምጣኔ ሃብት መቀዛዝ ምክንያት የነዳጅ ዋጋ በበርሜል #ከ80_ዶላር_በታች_እንዳይወርድ በማሰብ ነው ብለዋል።
መረጃው የቢቢሲ ነው።
@tikvahethiopia
ፎቶ፦ የአርባ ምንጭ ከተማ ፖሊስ በህገወጥ መንገድ የተጫነ 41 በርሜል ቤንዚን በቁጥጥር ስር መዋሉን ገልጿል።
ፖሊስ እንዳለው ፤ መጋቢት 24/ 2015 ዓ/ም ምሽት 1:00 ሰዓት ገደማ ነጭ ሳር ቀበሌ ውስጥ የሰሌዳ ቁጥር ኮድ 3 -35295 አ.አ የሆነ ኤፍኤስአር መኪና 41 በርሜል ቤንዚን በህገወጥ መንገድ ጭኖ በህብረተሰቡ ጥቆማ ሊያዝ ችሏል።
Credit : Arbaminch Communication
@tikvahethiopia
ፖሊስ እንዳለው ፤ መጋቢት 24/ 2015 ዓ/ም ምሽት 1:00 ሰዓት ገደማ ነጭ ሳር ቀበሌ ውስጥ የሰሌዳ ቁጥር ኮድ 3 -35295 አ.አ የሆነ ኤፍኤስአር መኪና 41 በርሜል ቤንዚን በህገወጥ መንገድ ጭኖ በህብረተሰቡ ጥቆማ ሊያዝ ችሏል።
Credit : Arbaminch Communication
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
" ሚዲያ የምናፍንበት ፤ ኢንተርኔት የምንዘጋበት ዘመን ድሮ አልፏል፤ ኬንያ ብዙ ርቀት ተጉዛለች " - ፕሬዝዳንት ዶ/ር ዊሊያም ሩቶ
በኬንያ የኑሮ ውድነት መባባስን እንዲሁም የምርጫ ኮሚሽን በአዲስ መልክ የማዋቀር ሂደትን ተከትሎ በኬንያ ባለፉት ሳምንታት ተቃውሞ መነሳቱ ይታወሳል።
በዚህም የተቃዋሚ ፓርቲው መሪ ራይላ ኦዲንጋ በሳምንት ሁለት ቀን ሰኞ እና ሐሙስ በመላው አገሪቱ የተቃውሞ ሰልፍ እንዲደረግ ጥሪ አስተላልፈው ነበር።
ዛሬ ይካሄዳል ተብሎ የነበረው የተቃውሞ ሰልፍ መራዘሙ ተገልጿል።
ፕሬዚዳንት ዶ/ር ዊሊያም ሩቶ ይደረጋል የተባለው ተቃውሞው እንዲቀርና ለውይይት በር እንዲከፈት ከጠየቁ በኋላ የተቃዋሚ መሪው ኦዲንጋ በሰጡት መግለጫ ፥ " ተቃውሞውን የሰረዝነው የፕሬዝዳንቱን ጥሪ ተከትሎ ‘ለንግግር ቦታ እንስጥ’ በሚል ነው " ብለዋል።
የሀገሪቱ የሚዲያ ማኅበራት ጥምረት ምን አለ ?
ከ17 የሚዲያ ማኅበራት የተወጣጣው የሚዲያ ማኅበራት ጥምረት ቀደም ብሎ ዛሬ ይደረጋል ተብሎ የታቀደውን ተቃውሞ ተከትሎ ሚዲያዎችን የመዝጋትና ኢንተርኔትን የማቋረጥ እቅድ መኖሩን ገልጾ ነበር።
የኬንያ አርታኢዎች ማህበር ፕሬዝዳንት ቸርችል ኦቲኖ ፖሊስ ሰልፉን በሚዘግቡ ጋዜጠኞች ላይ ጥቃት ካደረሰ እና መሳሪያዎቻቸውን ካወደመ በሚመጣው ረቡዕ ሰላማዊ ሰልፍ እንደሚያደርጉ ገልጿል።
አክሎም ሁሉም ተዋናዮች ጋዜጠኞች ላይ የሚያደርሱትን ጥቃት እንዲያቆሙ ጠይቀዋል።
ባለፈው ሐሙስ በነበረ ተቃውሞ ወደ 20 የሚሆኑ ጥቃቶች ሪፖርት መደረጋቸውን ያስታወቀው ጥምረቱ ገለልተኛ ምርመራ እንዲካሄድ ጠይቋል።
በሂደቱ ላይ መግለጫ እንዲሰጥ የ7 ቀን ቀነ ቀጠሮ አስቀምጧል።
ጉዳት የደረሰባቸው የሚዲያ ተቀማትና ጋዜጠኞች የህክምና ወጪያቸው እንዲሸፈን፤ ካሳ እንዲከፈላቸው ጥምረቱ መንግስትን ጠይቋል።
ከዚህም በተጨማሪ ሚዲያዎች ጋዜጠኞችን ከማሰማራታቸው በፊት ግልጽ የደህንነት እና የጥበቃ ፕሮቶኮሎች መኖራቸውን እንዲያረጋግጡ ጠይቋል።
ፕሬዝዳንት ዶ/ር ዊሊያም ሩቶ ትላንት በነበራቸው መግለጫ ከሚዲያ ጋር ተያይዞ ምን አሉ?
የኬንያ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ዊሊያም ሩቶ በምሽቱ መግለጫቸው መንግስታቸው ሚዲያዎችን እንደማይዘጋና #የሚዲያ_ነጻነትን እንደሚያከብር ተናግረዋል።
" ሚዲያ የምናፍንበት ኢንተርኔት የምንዘጋበት ዘመን ድሮ አልፏል፤ ኬንያ ብዙ ርቀት ተጉዛለች። ተግባሩን እንዲፈጽም የሚዲያ ነጻነትን እናከብራለን፤ ምንም በኛ ላይ የተዛባ ምልከታ ቢኖራችሁም የእኛ ፍጹም ድጋፍ አላችሁ። እናንተ ግን እኔ በቆምኩበት ቦታ ብትቆሙ ሚዲያዎችን ትዘጉ ነበር፤ ይህ ግን አይሆንም " ብለዋል።
Credit : The Standard
More 👉 @tikvahethmagazine
በኬንያ የኑሮ ውድነት መባባስን እንዲሁም የምርጫ ኮሚሽን በአዲስ መልክ የማዋቀር ሂደትን ተከትሎ በኬንያ ባለፉት ሳምንታት ተቃውሞ መነሳቱ ይታወሳል።
በዚህም የተቃዋሚ ፓርቲው መሪ ራይላ ኦዲንጋ በሳምንት ሁለት ቀን ሰኞ እና ሐሙስ በመላው አገሪቱ የተቃውሞ ሰልፍ እንዲደረግ ጥሪ አስተላልፈው ነበር።
ዛሬ ይካሄዳል ተብሎ የነበረው የተቃውሞ ሰልፍ መራዘሙ ተገልጿል።
ፕሬዚዳንት ዶ/ር ዊሊያም ሩቶ ይደረጋል የተባለው ተቃውሞው እንዲቀርና ለውይይት በር እንዲከፈት ከጠየቁ በኋላ የተቃዋሚ መሪው ኦዲንጋ በሰጡት መግለጫ ፥ " ተቃውሞውን የሰረዝነው የፕሬዝዳንቱን ጥሪ ተከትሎ ‘ለንግግር ቦታ እንስጥ’ በሚል ነው " ብለዋል።
የሀገሪቱ የሚዲያ ማኅበራት ጥምረት ምን አለ ?
ከ17 የሚዲያ ማኅበራት የተወጣጣው የሚዲያ ማኅበራት ጥምረት ቀደም ብሎ ዛሬ ይደረጋል ተብሎ የታቀደውን ተቃውሞ ተከትሎ ሚዲያዎችን የመዝጋትና ኢንተርኔትን የማቋረጥ እቅድ መኖሩን ገልጾ ነበር።
የኬንያ አርታኢዎች ማህበር ፕሬዝዳንት ቸርችል ኦቲኖ ፖሊስ ሰልፉን በሚዘግቡ ጋዜጠኞች ላይ ጥቃት ካደረሰ እና መሳሪያዎቻቸውን ካወደመ በሚመጣው ረቡዕ ሰላማዊ ሰልፍ እንደሚያደርጉ ገልጿል።
አክሎም ሁሉም ተዋናዮች ጋዜጠኞች ላይ የሚያደርሱትን ጥቃት እንዲያቆሙ ጠይቀዋል።
ባለፈው ሐሙስ በነበረ ተቃውሞ ወደ 20 የሚሆኑ ጥቃቶች ሪፖርት መደረጋቸውን ያስታወቀው ጥምረቱ ገለልተኛ ምርመራ እንዲካሄድ ጠይቋል።
በሂደቱ ላይ መግለጫ እንዲሰጥ የ7 ቀን ቀነ ቀጠሮ አስቀምጧል።
ጉዳት የደረሰባቸው የሚዲያ ተቀማትና ጋዜጠኞች የህክምና ወጪያቸው እንዲሸፈን፤ ካሳ እንዲከፈላቸው ጥምረቱ መንግስትን ጠይቋል።
ከዚህም በተጨማሪ ሚዲያዎች ጋዜጠኞችን ከማሰማራታቸው በፊት ግልጽ የደህንነት እና የጥበቃ ፕሮቶኮሎች መኖራቸውን እንዲያረጋግጡ ጠይቋል።
ፕሬዝዳንት ዶ/ር ዊሊያም ሩቶ ትላንት በነበራቸው መግለጫ ከሚዲያ ጋር ተያይዞ ምን አሉ?
የኬንያ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ዊሊያም ሩቶ በምሽቱ መግለጫቸው መንግስታቸው ሚዲያዎችን እንደማይዘጋና #የሚዲያ_ነጻነትን እንደሚያከብር ተናግረዋል።
" ሚዲያ የምናፍንበት ኢንተርኔት የምንዘጋበት ዘመን ድሮ አልፏል፤ ኬንያ ብዙ ርቀት ተጉዛለች። ተግባሩን እንዲፈጽም የሚዲያ ነጻነትን እናከብራለን፤ ምንም በኛ ላይ የተዛባ ምልከታ ቢኖራችሁም የእኛ ፍጹም ድጋፍ አላችሁ። እናንተ ግን እኔ በቆምኩበት ቦታ ብትቆሙ ሚዲያዎችን ትዘጉ ነበር፤ ይህ ግን አይሆንም " ብለዋል።
Credit : The Standard
More 👉 @tikvahethmagazine
#ድሬ
የድሬዳዋ ፖሊስ ፤ በአሽከርካሪነት ተመድቦ ከሚሰራበት ድርጅት እንዲያሽከረክር የተሠጠውን መኪና ሰርቆ በ290 ሺህ ብር የሸጠው ተጠርጣሪ ግለሰብን በቁጥጥር ስር ማዋሉን ገለፀ።
ተጠርጣሪው ግለሰብ CCECC በተሰኘ የመንገድ ስራ ድርጅት ተቀጥሮ በማገልገል ላይ ነበር።
የካቲት 29 ቀን 2015 ዓ.ም ከምሽቱ ሶስት ሠዓት ላይ የድርጅቱን የስራ ኃላፊዎች ወደቤታቸው ካስገባቸው በኋላ ያለማንም ፍቃድ ተሸከርካሪውን ከሌሎች ግብረ አበሮቹ ጋር በመሆን ወደ አዲስ አበባ በመውሰድ 4 ሚሊዮን ብር የሚገመተውን ተሸከርካሪ ለአንድ ግለሰብ በ290 (ሁለት መቶ ዘጠና ሺ) ብር ሽጧጣ።
የወንጀል ድርጊቱ ከተፈፀመ ከሁለት ቀን በኋላ ከድርጅቱ መኪና እንደጠፋ ሪፖርት የደረሰው ፖሊስ ከተጠርጣሪው አድራሻ በመነሳት ባደረገው ክትትል ተሽከርካሪውን በሌላ ሰው እጅ በአዳማ ከተማ ሲሽከረከር በቁጥጥር ስር ሊያውለው መቻሉ አሳውቋል።
በአሁኑ ወቅት ተሽከርካሪውን ሰርቆ የሸጠውን አሽከርካሪ እና የገዛውን ግለሰብ ጨምሮ 5 ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር በማዋል ምርመራ እያጣራ መሆኑን ድሬ ፖሊስ ገልጿል።
የድሬ ፖሊስ መንግስታዊም ሆነ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ለንብረታቸው ተገቢውን ክትትል ማድረግ እንዳለባቸው መልእክት አስተለልፏል።
#ድሬፖሊስ
@tikvahethiopia
የድሬዳዋ ፖሊስ ፤ በአሽከርካሪነት ተመድቦ ከሚሰራበት ድርጅት እንዲያሽከረክር የተሠጠውን መኪና ሰርቆ በ290 ሺህ ብር የሸጠው ተጠርጣሪ ግለሰብን በቁጥጥር ስር ማዋሉን ገለፀ።
ተጠርጣሪው ግለሰብ CCECC በተሰኘ የመንገድ ስራ ድርጅት ተቀጥሮ በማገልገል ላይ ነበር።
የካቲት 29 ቀን 2015 ዓ.ም ከምሽቱ ሶስት ሠዓት ላይ የድርጅቱን የስራ ኃላፊዎች ወደቤታቸው ካስገባቸው በኋላ ያለማንም ፍቃድ ተሸከርካሪውን ከሌሎች ግብረ አበሮቹ ጋር በመሆን ወደ አዲስ አበባ በመውሰድ 4 ሚሊዮን ብር የሚገመተውን ተሸከርካሪ ለአንድ ግለሰብ በ290 (ሁለት መቶ ዘጠና ሺ) ብር ሽጧጣ።
የወንጀል ድርጊቱ ከተፈፀመ ከሁለት ቀን በኋላ ከድርጅቱ መኪና እንደጠፋ ሪፖርት የደረሰው ፖሊስ ከተጠርጣሪው አድራሻ በመነሳት ባደረገው ክትትል ተሽከርካሪውን በሌላ ሰው እጅ በአዳማ ከተማ ሲሽከረከር በቁጥጥር ስር ሊያውለው መቻሉ አሳውቋል።
በአሁኑ ወቅት ተሽከርካሪውን ሰርቆ የሸጠውን አሽከርካሪ እና የገዛውን ግለሰብ ጨምሮ 5 ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር በማዋል ምርመራ እያጣራ መሆኑን ድሬ ፖሊስ ገልጿል።
የድሬ ፖሊስ መንግስታዊም ሆነ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ለንብረታቸው ተገቢውን ክትትል ማድረግ እንዳለባቸው መልእክት አስተለልፏል።
#ድሬፖሊስ
@tikvahethiopia