በወልቂጤ ምን ሆነ ?
ዛሬ ረቡዕ በወልቂጤ ከተማ ውስጥ የጸጥታ ኃይሎች በወሰዱት እርምጃ 2 ሰዎች ሲገደሉ 7 ሰዎች መቁሰላቸው ተሰምቷል።
በከተማው ነዋሪዎችን ካማረረ የመጠጥ ውሃ አቅርቦት ችግር ጋር በተያያዘ ቅሬታቸውን ለማቅረብ በወጡ ሰልፈኞች ላይ የጸጥታ ኃይሎች እርምጃ ወስደዋል።
በዚህ የፀጥታ ኃይሎች እርምጃም 2 ሰዎች ሲገደሉ ቢያንስ 7 ሰዎች መቁሰላቸውን የከተማይቱ ነዋሪዎች እና የጤና ምንጮችን ዋቢ በማድረግ " ኢትዮጵያ ኢንሳይደር " ዘግቧል።
የወልቂጤ ከተማ ፖሊስ ጽህፈት ቤት የሟቾቹን እና የቁስለኞቹን ብዛት ማረጋገጡን ዘገባው አክሏል።
ለሰዎች ህይወት መጥፋት ምክንያት የሆነው ክስተት መነሻ፤ በአዲስ ክ/ ከተማ የመጠጥ ውሃ አቅርቦት ላለፉት 3 ወራት መቋረጡ እንደሆነ የከተማይቱ ነዋሪዎች ተናግረዋል።
ነዋሪዎች የመጠጥ ውሃ ከመኖሪያቸው 14 ኪ/ሜ ርቀት ከሚገኙ አካባቢዎች ሲያጓጉዙ መቆየታቸውን አስታውሰዋል።
በተመሳሳይ ዛሬ ጠዋት ውሃ ለመቅዳት በተለምዶ " ዱባይ ካፌ አደባባይ " ተብሎ ወደሚጠራው አካባቢ ቢጓዙም፤ በስፍራው የውሃ አገልግሎት በመቋረጡ ተቃውሟቸውን ለማሰማት አደባባይ መውጣታቸውን የዓይን እማኞች ገልፀዋል።
ነዋሪዎቹ የጉራጌ ዞን አስተዳደር፣ የወልቂጤ ከንቲባ ጽ/ቤት እና የወልቂጤ ውሃ አገልግሎት ጽ/ቤት ወደሚገኙበት ስፍራ በማምራት ተቃውሟቸውን በሰላማዊ ሰልፍ ሲገልጹ ቆይተዋል።
በአካባቢው ጸጥታ ለማስከበር የተሰማሩት #የደቡብ_ክልል_ልዩ_ኃይል አባላት የተቃውሞ ሰልፉን ለመበተን #የአስለቃሽ_ጭስ በመተኮሳቸው ሰልፈኞቹ ድንጋይ ወደ መወርወር መግባታቸውን የዓይን እማኞቹ ገልጸዋል።
ይህን ተከትሎ የጸጥታ ኃይሎች በከፈቱት ተኩስ 2 ሰዎች ሲገደሉ 9 ሰዎች ቆስለዋል።
(ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)
Photo Credit ፦ ብስራት ዜዶ
@tikvahethiopia
ዛሬ ረቡዕ በወልቂጤ ከተማ ውስጥ የጸጥታ ኃይሎች በወሰዱት እርምጃ 2 ሰዎች ሲገደሉ 7 ሰዎች መቁሰላቸው ተሰምቷል።
በከተማው ነዋሪዎችን ካማረረ የመጠጥ ውሃ አቅርቦት ችግር ጋር በተያያዘ ቅሬታቸውን ለማቅረብ በወጡ ሰልፈኞች ላይ የጸጥታ ኃይሎች እርምጃ ወስደዋል።
በዚህ የፀጥታ ኃይሎች እርምጃም 2 ሰዎች ሲገደሉ ቢያንስ 7 ሰዎች መቁሰላቸውን የከተማይቱ ነዋሪዎች እና የጤና ምንጮችን ዋቢ በማድረግ " ኢትዮጵያ ኢንሳይደር " ዘግቧል።
የወልቂጤ ከተማ ፖሊስ ጽህፈት ቤት የሟቾቹን እና የቁስለኞቹን ብዛት ማረጋገጡን ዘገባው አክሏል።
ለሰዎች ህይወት መጥፋት ምክንያት የሆነው ክስተት መነሻ፤ በአዲስ ክ/ ከተማ የመጠጥ ውሃ አቅርቦት ላለፉት 3 ወራት መቋረጡ እንደሆነ የከተማይቱ ነዋሪዎች ተናግረዋል።
ነዋሪዎች የመጠጥ ውሃ ከመኖሪያቸው 14 ኪ/ሜ ርቀት ከሚገኙ አካባቢዎች ሲያጓጉዙ መቆየታቸውን አስታውሰዋል።
በተመሳሳይ ዛሬ ጠዋት ውሃ ለመቅዳት በተለምዶ " ዱባይ ካፌ አደባባይ " ተብሎ ወደሚጠራው አካባቢ ቢጓዙም፤ በስፍራው የውሃ አገልግሎት በመቋረጡ ተቃውሟቸውን ለማሰማት አደባባይ መውጣታቸውን የዓይን እማኞች ገልፀዋል።
ነዋሪዎቹ የጉራጌ ዞን አስተዳደር፣ የወልቂጤ ከንቲባ ጽ/ቤት እና የወልቂጤ ውሃ አገልግሎት ጽ/ቤት ወደሚገኙበት ስፍራ በማምራት ተቃውሟቸውን በሰላማዊ ሰልፍ ሲገልጹ ቆይተዋል።
በአካባቢው ጸጥታ ለማስከበር የተሰማሩት #የደቡብ_ክልል_ልዩ_ኃይል አባላት የተቃውሞ ሰልፉን ለመበተን #የአስለቃሽ_ጭስ በመተኮሳቸው ሰልፈኞቹ ድንጋይ ወደ መወርወር መግባታቸውን የዓይን እማኞቹ ገልጸዋል።
ይህን ተከትሎ የጸጥታ ኃይሎች በከፈቱት ተኩስ 2 ሰዎች ሲገደሉ 9 ሰዎች ቆስለዋል።
(ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)
Photo Credit ፦ ብስራት ዜዶ
@tikvahethiopia