TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.8K photos
1.61K videos
216 files
4.37K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#EU #RUSSIA

የአውሮፓ ህብረት አባል ሃገራት በሩስያ የነዳጅ ግብይት ላይ ማዕቀብ ጣሉ።

27ቱ አውሮጳ ህብረት አባል ሃገራት በሩስያ የነዳጅ ግብይት ላይ ማዕቀብ መጣላቸውን ይፋ አድርገዋል።

አባልሃገራቱ በግዙፉ የሩስያ ባንክ ስቤር ባንክንም ከዓለማቀፉ የባንኮች የክፍያ ስረዓት ወይም ስዊፍት ማስወጣታቸውን አስታውቀዋል።

በስምምነቱ መሰረት ወደ አውሮፓ የሚገባው የሩስያ ነዳጅ ሁለት ሶስተኛው እንደሚታቀብ የህብረቱ ፕሬዚደንት ቻርለስ ሚሸል ተናግረዋል።

ማዕቀቡ " የሩስያ የፋይናንስ ምንጭ በከፍተኛ ደረጃ በማንኮታኮት " ሩስያ በዩክሬን ላይ የከፈተችውን ጦርነት ገትታ ከሀገሪቱ ለቃ እንድትወጣ ያስገድዳታል " ሲሉ ፕሬዚደንቱ ተናግረዋል።

የጀርመኑ መራሄ መንግስት ኦላፍ ሾልስም " ስምምነቱ የጋራችን ነው " ብለዋል። ነገር ግን ከሃያ ሰባቱ ሃገራት መካከል ፦
➡️ ሃንጋሪ ፣
➡️ ስሎቫኪያ ፣
➡️ ቼክ ሪፐብሊክ እና ቡልጋሪያ ከሩስያ ነዳጅ ማስገባት #እንደማያቋርጡ አስታውቀዋል።

ይህንኑ በተመለከተ የሃንጋሪው ጠቅላይ ሚኒስትር ቪክቶር ኦርባን የነዳጅ ማዕቀቡ የህብረቱ አጀንዳ መሆን የለበትም ሲሉም ተቃውሟቸውን አሰምተው እንደነበር የጀርመን ድምፅ ሬድዮ ዘግቧል።

@tikvahethiopia
👍3