" አሁንም ቢሆን በርካታ ሥራዎችን የምንሰራው ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር ነው " - ብፁዕ አቡነ አብርሃም ፤
ቤተክርስቲያኗ ከባንክ አገልግሎት ጋር በተያያዙ የሚነገሩባት #አሉባልታዎች ትክክል እንዳልሆኑ ገለፀች።
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ጠቅላይ ሥራ አስኪያጅና የባህርዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ አብርሃም ፤ ከቤተክርስትያኗ የባንክ አገልግሎት ጋር በተያያዘ በርካታ አሉባልታ ይነሳል ብለዋል።
" ቤተክርስቲያን የምትሰራው ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር ነው። " ያሉት ብፁዕነታቸው " ከዓባይ ባንክ ጋር ሥራ የጀመርነው በህጋዊ አሰራር በጨረታ በተደረገ ሂደት አሸናፊ ሆኖ በመገኘቱ ነው። " ብለዋል።
" ከዓባይ ባንክ ይልቅ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና በኦሮሚያ ባንክ ያለን ገንዘብ ይበልጣል። " ያሉት ብፁዕ አቡነ አብርሃም ፤ " ዓባይ ባንክ ያለን ገንዘብ ተንቀሳቃሽና ለሰራተኛው የብድር አገልግሎት በማቅረብ ለሰራተኛው የመኪና፣ የቤትና የልዩልዩ ግዤዎችን ለመፈጸም የሚያስችል አገልግሎት የሚሰጥበት የባንክ አገልግሎት ነው " ሲሉ አስረድተዋል።
በሌላ በኩል፤ ቤተክርስቲያኗ በኦሮሚያ ባንክ የማይንቀሳቀስ ገንዘብ ማስቀመጧን ብፁዕነታቸው ተናግረዋል።
ብፁዕነታቸው " በጣም መጠነኛ ገንዘብ በአዋሽ፣ በሕብረትና በአቢሲኒያ ባንኮች አስቀምጣለች ፤ ከዚህ ውጪ በሌላ ባንክ ወይም በአማራ ባንክ የተቀመጠ ምንም አይነት የማዕከላዊ የቤተክርስቲያን አስተዳደር ገንዘብ የለም። " ሲሉ አሳውቀዋል።
" የተቀመጠ ገንዘብ አለ ከተባለም #በማስረጃ ማቅረብ ይቻላል " ያሉ ሲሆን " አሁንም ቢሆን በርካታ ሥራዎችን የምንሰራው ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር ነው ። " ሲሉ ገልጸዋል።
መረጃው የኢ/ኦ/ተ/ቤ ሕዝብ ግንኙነት ነው።
@tikvahethiopia
ቤተክርስቲያኗ ከባንክ አገልግሎት ጋር በተያያዙ የሚነገሩባት #አሉባልታዎች ትክክል እንዳልሆኑ ገለፀች።
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ጠቅላይ ሥራ አስኪያጅና የባህርዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ አብርሃም ፤ ከቤተክርስትያኗ የባንክ አገልግሎት ጋር በተያያዘ በርካታ አሉባልታ ይነሳል ብለዋል።
" ቤተክርስቲያን የምትሰራው ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር ነው። " ያሉት ብፁዕነታቸው " ከዓባይ ባንክ ጋር ሥራ የጀመርነው በህጋዊ አሰራር በጨረታ በተደረገ ሂደት አሸናፊ ሆኖ በመገኘቱ ነው። " ብለዋል።
" ከዓባይ ባንክ ይልቅ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና በኦሮሚያ ባንክ ያለን ገንዘብ ይበልጣል። " ያሉት ብፁዕ አቡነ አብርሃም ፤ " ዓባይ ባንክ ያለን ገንዘብ ተንቀሳቃሽና ለሰራተኛው የብድር አገልግሎት በማቅረብ ለሰራተኛው የመኪና፣ የቤትና የልዩልዩ ግዤዎችን ለመፈጸም የሚያስችል አገልግሎት የሚሰጥበት የባንክ አገልግሎት ነው " ሲሉ አስረድተዋል።
በሌላ በኩል፤ ቤተክርስቲያኗ በኦሮሚያ ባንክ የማይንቀሳቀስ ገንዘብ ማስቀመጧን ብፁዕነታቸው ተናግረዋል።
ብፁዕነታቸው " በጣም መጠነኛ ገንዘብ በአዋሽ፣ በሕብረትና በአቢሲኒያ ባንኮች አስቀምጣለች ፤ ከዚህ ውጪ በሌላ ባንክ ወይም በአማራ ባንክ የተቀመጠ ምንም አይነት የማዕከላዊ የቤተክርስቲያን አስተዳደር ገንዘብ የለም። " ሲሉ አሳውቀዋል።
" የተቀመጠ ገንዘብ አለ ከተባለም #በማስረጃ ማቅረብ ይቻላል " ያሉ ሲሆን " አሁንም ቢሆን በርካታ ሥራዎችን የምንሰራው ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር ነው ። " ሲሉ ገልጸዋል።
መረጃው የኢ/ኦ/ተ/ቤ ሕዝብ ግንኙነት ነው።
@tikvahethiopia