#Update በአዲስ አበባ #ለውጭ_ሀገራት የስራ ስምሪት ስልጠና የሚሰጡ ተቋማት በሙሉ አቅማቸው አገልግሎት እየሰጡ እንዳልሆነ ተገለፀ። ፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት በአዲስ አበባ ከተዘጋጁት የስልጠና ማእከላት ውስጥ የጄኔራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ እና የንፋስ ስልክ ቴክኒክና ሞያ ኮሌጅ ማዕከላትን ተመልክቷል። እነዚህ ማዕከላት ለመኖሪያ ቤት አገልግሎት ስራ ለሚሄዱ ዜጎች ስልጠና ለመስጠት የሚያስችላቸውን ዝግጅቶች ማድረጋቸውን ነው መታዘብ የተቻለው። ማዕከላቱ ዘመናዊ የቤት ውስጥ መገልገያ መሳሪያዎችን፣ የጽዳት እቃዎችን፣ የማብሰያና ሌሎች የቤት ውስጥ ቁሳቆሶችን ለማሟላት ሞክረዋል።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
@tsegabwolde @tikvahethiopia
Dine with PM ABIY AHEMED FOR SHEGER...
ጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ #ለሀገር ውስጥና #ለውጭ ሀገር ባለሃብቶች በቤተ-መንግስት የእራት ግብዣ ያደርጋሉ። መግቢያ 5 ሚሊዮን ብር ሲሆን ገቢው አዲስ አባባ #ለማስዋብ ይወላል።
Via ELU
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ #ለሀገር ውስጥና #ለውጭ ሀገር ባለሃብቶች በቤተ-መንግስት የእራት ግብዣ ያደርጋሉ። መግቢያ 5 ሚሊዮን ብር ሲሆን ገቢው አዲስ አባባ #ለማስዋብ ይወላል።
Via ELU
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ETHIOPIA
ዛሬ የሚኒስትሮች ም/ቤት ባካሄደው 13ኛ መደበኛ ስብሰባ የባንክ ዘርፍን #ለውጭ_ኢንቨስተሮች ክፍት ለማድረግ በቀረበ ረቂቅ ፖሊሲ ላይ ተወያይቶ በሥራ ላይ እንዲውል ወስኗል።
የባንክ ዘርፍን ለውጭ ኢንቨስተሮች ክፍት ማድረግ የዘርፉን አገልግሎቶች በእውቀት እና በቴክኖሎጂ ለመደገፍ፣ የአገራችን ኢኮኖሚ ከዓለም አቀፍ ገበያ ጋር ያለውን ትስስር ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር፣ የፋይናንስ ዘርፉን ተወዳዳሪነት፣ ውጤታማነትና ቀልጣፋነት በመጨመር በቂ የፋይናንስ አቅርቦት እንዲኖር የሚያስችል ረቂቅ ፖሊሲ በዛሬው ዕለት ለሚኒስትሮች ምክር ቤት ቀርቧል፡፡
ምክር ቤቱ በፖሊሲው ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ ግብዓቶችን በማከል በሥራ ላይ እንዲውል ተወስኗል።
@tikvahethiopia
ዛሬ የሚኒስትሮች ም/ቤት ባካሄደው 13ኛ መደበኛ ስብሰባ የባንክ ዘርፍን #ለውጭ_ኢንቨስተሮች ክፍት ለማድረግ በቀረበ ረቂቅ ፖሊሲ ላይ ተወያይቶ በሥራ ላይ እንዲውል ወስኗል።
የባንክ ዘርፍን ለውጭ ኢንቨስተሮች ክፍት ማድረግ የዘርፉን አገልግሎቶች በእውቀት እና በቴክኖሎጂ ለመደገፍ፣ የአገራችን ኢኮኖሚ ከዓለም አቀፍ ገበያ ጋር ያለውን ትስስር ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር፣ የፋይናንስ ዘርፉን ተወዳዳሪነት፣ ውጤታማነትና ቀልጣፋነት በመጨመር በቂ የፋይናንስ አቅርቦት እንዲኖር የሚያስችል ረቂቅ ፖሊሲ በዛሬው ዕለት ለሚኒስትሮች ምክር ቤት ቀርቧል፡፡
ምክር ቤቱ በፖሊሲው ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ ግብዓቶችን በማከል በሥራ ላይ እንዲውል ተወስኗል።
@tikvahethiopia
#ኢንሹራንስ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በኢንሹራንስ ዘርፍ ላይ ቁጥጥርና ክትትል እንዲያደርግ በሕግ የተሰጠውን ሰልጣን በማሻሻል፣ የኢንሹራንስ ዘርፉ ከብሔራዊ ባንክ ውጪ ራሱን በቻለ ገለልተኛ ባለሥልጣን ቁጥጥር እንዲደረግበት ለማድረግ እንቅስቃሴ መጀመሩን ሪፖርተር አስነብቧል።
በዚህም መሠረት የኢንሹራንስ ዘርፉን የሚቆጣጠርና የሚከታተል ገለልተኛ ተቋም ለማቋቋም አማካሪ ተቀጥሮ ሥራ መጀመሩን ለማወቅ ተችሏል።
ይህ ሥራ ተጠናቆ ተቋሙ ከተመሠረተ በኋላም የኢንሹራንስ ዘርፍ #ለውጭ ኩባንያዎች ውድድር ክፍት እንደሚሆን ታውቋል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ሰሞኑን እንዳስታወቀው የኢንሹራንስ ሪጉላቶሪ ኤጀንሲ ራሱን የቻለ ገለልተኛ ኤጀንሲ እንዲኖረው በመንግሥት በተሰጠው አቅጣጫ መሠረት ኤጀንሲውን ለማቋቋም የሚያስችሉ ሥራዎች ተጀምረዋል፡፡
ብሔራዊ ባንክ " የውጭ ባንኮች በኢትዮጵያ የባንክ ኢንዱስትሪ ውስጥ እንዲገቡ እንደተፈቀደው ሁሉ ለኢንሹራንስ ዘርፉም ሊከፍት ይገባል " በሚል የሚቀርበው ተደጋጋሚ ጥያቄ አግባብ ቢሆን መጀመርያ ሊሠሩ የሚገባቸው ሥራዎች ስላሉ ይህ ከተጠናቀቀ በኋላ ቀጣዩ ዕርምጃ በዘርፉ የውጭ ኩባንያዎችን መጋበዝ ይሆናል ብሏል።
የኢንሹራንስ ተቆጣጣሪ ኤጀንሲው ሳይቋቋም የውጭ ኢንሹራንስ ኩባንያዎች ወደ ኢትዮጵያ እንዲገቡ የማይፈቀድ መሆኑን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ መጠቆሙን ሪፖርተር ዘግቧል።
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በኢንሹራንስ ዘርፍ ላይ ቁጥጥርና ክትትል እንዲያደርግ በሕግ የተሰጠውን ሰልጣን በማሻሻል፣ የኢንሹራንስ ዘርፉ ከብሔራዊ ባንክ ውጪ ራሱን በቻለ ገለልተኛ ባለሥልጣን ቁጥጥር እንዲደረግበት ለማድረግ እንቅስቃሴ መጀመሩን ሪፖርተር አስነብቧል።
በዚህም መሠረት የኢንሹራንስ ዘርፉን የሚቆጣጠርና የሚከታተል ገለልተኛ ተቋም ለማቋቋም አማካሪ ተቀጥሮ ሥራ መጀመሩን ለማወቅ ተችሏል።
ይህ ሥራ ተጠናቆ ተቋሙ ከተመሠረተ በኋላም የኢንሹራንስ ዘርፍ #ለውጭ ኩባንያዎች ውድድር ክፍት እንደሚሆን ታውቋል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ሰሞኑን እንዳስታወቀው የኢንሹራንስ ሪጉላቶሪ ኤጀንሲ ራሱን የቻለ ገለልተኛ ኤጀንሲ እንዲኖረው በመንግሥት በተሰጠው አቅጣጫ መሠረት ኤጀንሲውን ለማቋቋም የሚያስችሉ ሥራዎች ተጀምረዋል፡፡
ብሔራዊ ባንክ " የውጭ ባንኮች በኢትዮጵያ የባንክ ኢንዱስትሪ ውስጥ እንዲገቡ እንደተፈቀደው ሁሉ ለኢንሹራንስ ዘርፉም ሊከፍት ይገባል " በሚል የሚቀርበው ተደጋጋሚ ጥያቄ አግባብ ቢሆን መጀመርያ ሊሠሩ የሚገባቸው ሥራዎች ስላሉ ይህ ከተጠናቀቀ በኋላ ቀጣዩ ዕርምጃ በዘርፉ የውጭ ኩባንያዎችን መጋበዝ ይሆናል ብሏል።
የኢንሹራንስ ተቆጣጣሪ ኤጀንሲው ሳይቋቋም የውጭ ኢንሹራንስ ኩባንያዎች ወደ ኢትዮጵያ እንዲገቡ የማይፈቀድ መሆኑን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ መጠቆሙን ሪፖርተር ዘግቧል።
@tikvahethiopia