TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.8K photos
1.61K videos
216 files
4.36K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
" ለጅቡቲ ጉምሩክ ደብዳቤ ፅፈናል " - የኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን

በጅቡቲ ጉምሩክ የወደብ ጭነት መዘግየት ችግር የተፈጠረ ሲሆን ችግሩን ለመፍታት ጥረት እየተደረገ መሆኑን የኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን አሳውቋል።

የጂቡቲ ጉምሩክ " ከ20 ሺህ ዶላር በታች የክፍያ ደረሰኝ የያዙ ጭነቶች ወደ ኢትዮጵያ #እንዳያልፉ " በሚል መመሪያ እቃዎች እንዳይንቀሳቀሱ እንዳገደ ተነግሯል።

የኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን የኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክተር አቶ ዘርይሁን አሰፋ በሰጡት ቃል ፤ በሁለቱ ሀገራት መካከል የተፈጠረውን ችግር ለመፍታት ለጅቡቲ ጉምሩክ ደብዳቤ መፃፉን ገልጸዋል።

" ኢትዮጵያ እቃዎችን በጂቡቲ ወደብ በኩል የምታዘዋውር መሆኑን ተከትሎ መሰል ችግሮች ሊያጋጥሙ እንደሚችሉ " ይጠበቃል ያሉት አቶ ዘርይሁን " እቃ አስመጭዎች ለደረሰባቸው ችግር ዘላቂ መፍትሔ ለመስጠት ስራዎች እየተሰሩ ናቸው " ብለዋል።

" በጂቡቲ 2 ማስተባበሪያ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤቶች አሉን " ያሉት ዳይሬክተሩ ችግሩ የሚያሳድረው ተጽእኖ ከፍተኛ በመሆኑ አፋጣኝ መፍትሄ እንደሚሻ አስረድተዋል፡፡ 

ችግሩ ከ3 ሳምንታት በላይ ያስቆጠረ መሆኑን ተከትሎ ጭነቶች ወደብ ላይ በሚቆዩበት ወቅት ከሚከፈለው ገንዘብ መጠን ጋር ተያይዞ ጉዳቱ የከፋ መሆኑን አስረድተዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ፤ ይህ መረጃ #ባለቤትነቱ የአሐዱ ኤፍ ኤም 94.3 ሬድዮ ጣቢያ መሆኑን ያሳውቃል።

@tikvahethiopia
😢345144😡91🙏62🥰33🕊30😭27👏24😱9