TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59K photos
1.5K videos
211 files
4.08K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ባሌ_ሮቤ | ባለፉት ሁለት እና ሶስት ቀናት በማህበራዊ ሚዲያ ብዙ ሲባልባት የነበረችው የባሌ ሮቤ ከተማ ወደ ቀደመው ሰላማዊ እንቅስቃሴዋ እየተመለሰች እንደምትገኝ ተገልጿል። የንግድ እና የትራንስፖርት እንቅስቃሴ ወደነበረበት ተመልሷል። በሁሉም ቀበሌዎች ውይይቶች እየተደረጉ ይገኛሉ። የሀገር ሽማግሌዎች እና አባ ገዳዎች ህዝቡ ወደቀደመው ሰላማዊ ኑሮው እንዲመለስ ከፍተኛ ስራ እየሰሩ ናቸው። ከሰሞኑ ግጭት ጋር በተያያዘ 27 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ውለዋል።

Via NIGI
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ባሌ_ሮቤ

በጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ የተመራ ከፍተኛ የልዑካን ቡድን ለሥራ ጉብኝት ባሌ ሮቤ ገብቷል።

በጉብኝቱ ከጠ/ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ በተጨማሪ ፦

➡️ ሰሞኑን ትግራይ ክልል መቐለ የነበሩት የአፍሪካ ሕብረት የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ኦሉሴጉን ኦባሳንጆ፣

➡️ የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ፣

➡️ የዓለም ባንክ የኢትዮጵያ ተወካይ ኡስማን ዲዮን እንዲሁም የፌደራል እና የክልል ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ተሳታፊ ናቸው።

የልዑካን ቡድኑ በባሌ ዞን እየተከናወኑ ያሉ የግብርና ሥራዎችን ተዘዋውሮ ይመለከታል ተብሎ እንደሚጠበቅ ከኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ያገኘነው መረጃ ያሳያል።

@tikvahethiopia