" እኔ የትራፊክ አደጋ አልደረሰብኝም " - አትሌት ኃይሌ ገ/ስላሴ
አንጋፋው አትሌት ኃይሌ ገ/ስላሴ የትራፊክ አደጋ #እንዳልደረሰበት ተናገረ።
አትሌት ኃይሌ " የትራፊክ አደጋ እንደደረሰበት " ሚዲያዎች እየዘገቡ ሲሆን አትሌቱ ለአል ዓይን አማርኛው ክፍል በሰጠው ቃል " መረጃው ሀሰት ነው እኔ ላይ የትራፊክ አደጋ አልደረሰም " ብሏል።
ኃይሌ ፤ " ያለንበት ሁኔታ እጅግ ከባድ ነው፣ ሌላም ነገር ቢሆን እንዲህ ነው የውሸት መረጃ የሚሰራጨው " ብሏል።
ዛሬ ጠዋት " ብስራት ኤፍ ኤም 101.1 " በተሰኘው ሬድዮ ጣቢያ ከሚሰራጨው " አውቶሞቲቭ " የሬድዮ ፕሮግራም ጋር በስልክ ተደውሎልኝ ስለፍጥነት መገደቢያ ወይም ስፒድ ብሬከር ችግር መሆኑን አስተያየት ሰጥቼ ነበር ያለው ኃይሌ ፤ " ይህ ማለት ግን ዛሬ በእኔ ላይ የትራፊክ አደጋ ደርሶብኛል ማለት አይደለም " ሲል ተናግሯል።
አትሌት ኃይሌ ገብረስላሴ ፤ በተሰራጨው ሀሰተኛ ዘገባ ምክንያት ቤተሰቦቼ እና ጓደኞቼ አሳስቧቸው እጅግ ብዙ የስልክ ጥሪዎች እያደረሱኝ ነው ሲል ለአል ዓይን አማርኛ አገልግሎት ክፍል በሰጠው ቃል ተናግሯል።
#አልዓይንኒውስ
@tikvahethiopia
አንጋፋው አትሌት ኃይሌ ገ/ስላሴ የትራፊክ አደጋ #እንዳልደረሰበት ተናገረ።
አትሌት ኃይሌ " የትራፊክ አደጋ እንደደረሰበት " ሚዲያዎች እየዘገቡ ሲሆን አትሌቱ ለአል ዓይን አማርኛው ክፍል በሰጠው ቃል " መረጃው ሀሰት ነው እኔ ላይ የትራፊክ አደጋ አልደረሰም " ብሏል።
ኃይሌ ፤ " ያለንበት ሁኔታ እጅግ ከባድ ነው፣ ሌላም ነገር ቢሆን እንዲህ ነው የውሸት መረጃ የሚሰራጨው " ብሏል።
ዛሬ ጠዋት " ብስራት ኤፍ ኤም 101.1 " በተሰኘው ሬድዮ ጣቢያ ከሚሰራጨው " አውቶሞቲቭ " የሬድዮ ፕሮግራም ጋር በስልክ ተደውሎልኝ ስለፍጥነት መገደቢያ ወይም ስፒድ ብሬከር ችግር መሆኑን አስተያየት ሰጥቼ ነበር ያለው ኃይሌ ፤ " ይህ ማለት ግን ዛሬ በእኔ ላይ የትራፊክ አደጋ ደርሶብኛል ማለት አይደለም " ሲል ተናግሯል።
አትሌት ኃይሌ ገብረስላሴ ፤ በተሰራጨው ሀሰተኛ ዘገባ ምክንያት ቤተሰቦቼ እና ጓደኞቼ አሳስቧቸው እጅግ ብዙ የስልክ ጥሪዎች እያደረሱኝ ነው ሲል ለአል ዓይን አማርኛ አገልግሎት ክፍል በሰጠው ቃል ተናግሯል።
#አልዓይንኒውስ
@tikvahethiopia