TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.1K photos
1.5K videos
211 files
4.09K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
" እኔ የትራፊክ አደጋ አልደረሰብኝም " - አትሌት ኃይሌ ገ/ስላሴ

አንጋፋው አትሌት ኃይሌ ገ/ስላሴ የትራፊክ አደጋ #እንዳልደረሰበት ተናገረ።

አትሌት ኃይሌ " የትራፊክ አደጋ እንደደረሰበት " ሚዲያዎች እየዘገቡ ሲሆን አትሌቱ ለአል ዓይን አማርኛው ክፍል በሰጠው ቃል " መረጃው ሀሰት ነው እኔ ላይ የትራፊክ አደጋ አልደረሰም " ብሏል።

ኃይሌ ፤ " ያለንበት ሁኔታ እጅግ ከባድ ነው፣ ሌላም ነገር ቢሆን እንዲህ ነው የውሸት መረጃ የሚሰራጨው " ብሏል።

ዛሬ ጠዋት " ብስራት ኤፍ ኤም 101.1 " በተሰኘው ሬድዮ ጣቢያ ከሚሰራጨው " አውቶሞቲቭ " የሬድዮ ፕሮግራም ጋር በስልክ ተደውሎልኝ ስለፍጥነት መገደቢያ ወይም ስፒድ ብሬከር ችግር መሆኑን አስተያየት ሰጥቼ ነበር ያለው ኃይሌ ፤ " ይህ ማለት ግን ዛሬ በእኔ ላይ የትራፊክ አደጋ ደርሶብኛል ማለት አይደለም " ሲል ተናግሯል።

አትሌት ኃይሌ ገብረስላሴ ፤ በተሰራጨው ሀሰተኛ ዘገባ ምክንያት ቤተሰቦቼ እና ጓደኞቼ አሳስቧቸው እጅግ ብዙ የስልክ ጥሪዎች እያደረሱኝ ነው ሲል ለአል ዓይን አማርኛ አገልግሎት ክፍል በሰጠው ቃል ተናግሯል።

#አልዓይንኒውስ

@tikvahethiopia