TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update
🔴 “ 44 ሴት ተማሪዎችን ‘ጥቁር ማስክ አድርጋችኋል አናስገባም’ ብለው፣ ኒቃብ የለበስን 7 ሴቶችንም ከልክለውን ውጪ አደርን ” - ሙስሊም ተማሪዎች
🔵 “ የትምህርት ሚኒስቴር የተቋማትን አስተዳደርና መመሪያዎችን ተከትሎ የሚተዳደር ነውና ተቋሙ ያንን ነው እያደረግን ያለነው ” - ዲላ ዩኒቨርሲቲ
የዲላ ዩኒቨርሲቲ ሴት ሙስሊም ተማሪዎች ኒቃብ፣ ጥቁር ማስክ እንዳይለብሱ በመከልከላቸው ከትምህርታቸው እየተስተጓጎሉ በመሆኑ መፍትሄ እንዲሰጣቸው በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል ጠንከር ያለ ስሞታ አቅርበዋል።
የተማሪዎቹ ዝርዝር ስሞታ ምንድን ነው ?
“ ኒቃብና ጥቁር ማስክ እንዳንለብስ ነው የተከለከልነው። ክልከላው የጀመረው ከአንድ ወር በፊት ነበር። በዚህም ማመልከቻ አስገብተን ነበር መልበስ እንዲፈቀድልን። ሆኖም ግን ምላሽ ሳይሰጠን ቆዬ።
ትምህርታችን በስርዓት እንዳንከታተል አስተጓጎሉን። ቅዳሜ፣ አንዲት እህት ማስክ አድርጋ፣ ሂጃብ ለብሳ በምትገባበት ወቅት ኦዲያ ካምፓስ በሁለቱም በሮች እንዳትገባ ከልክለዋታል።
እንዲያውም ወንዶቹ የግቢው ጥበቆች አስፈራርተው ፊቷን አስከፍተዋታል። እንደዛም ሆኖ ማስክ ለብሳ ወደ ግቢ መግባት እንደማትችል ነግረው መልሰዋታል።
ቅዳሜ ከሰዓት ሁለት ኒቃብ የለበሱ ተማሪዎች ግቢ ሊገቡ ሲሉ ተከልክለዋል። ለምን እንደተከለከሉ ሲጠይቁ ‘ ለደህንነት ሲባል ፊታችሁ መሸፈን የለበትም ’ አሏቸው።
ለደኅንነት ሲባል ከሆነ ሴት ሙስሊም ተማሪዎች በሴት ጥበቃ ተፈትሸው፣ አይዲያቸውን አሳይተው እንዲገቡ ሲጠይቋቸው ‘ ያንችን ፊት ማየት ምንም አይሰራልኝም። ፊትሽን ለምታሳይው አሳይ ’ የሚል መልስ ተሰጠን።
ከዚያ በኋላም ሰኞ እለት ደግሞ ኒቃብ፣ ጥቁር ማስክ መልበስ እንደማይቻል በፕሬዜዳንቱ ጭምር ተወሰነ። የተማሪ ተወካዮች ጠርተው ይህን አሳወቋቸው።
ጥበቃዎቹም ውሳኔውን በመጥቀስ ‘አናስገባም’ አሉን። ማክሰኞ እለት ማታ 44 ሴት ተማሪዎችን ‘ጥቁር ማስክ አድርጋችኋል አናስገባም’ ብለው፣ ኒቃብ የለበስን 7 ሴቶችንም ከልክለውን ውጪ አደርን።
ረቡዕ ጠዋትም ከለር ማስክ አድርገው የገቡትን በፌደራል ጭምር አስፈራርተው ፊታቸውን እንዲገልጡ አድርገው፣ ሂጃብም ማውለቅ እንዳለባቸው አሳሰቧቸው።
ከሰኞ ጀምሮ ክላስም እየተከታተልን አይደለም፣ ኤግዛም አልፎናል፣ አሳይመንትም እያለፈን ነው። ማውለቅ ስለማንችል ከግቢ ውጪ ነን። በቃ ከተማሪነት ውጪ ባለ ህይወት ነን። እንደ ሴትነታችን ትልቅ የመብት ጥሰት ነው የተፈጸመብን።
ከምሽቱ 3 ሰዓት እንዳንገባ ሲከለክሉን የት እንድናድር፣ ምን እንድንለብስ፣ ምን እንደምንምገብ ያሰቡትን አናውቅም። ስለዚህ እንደንገባ ቢፈቅዱም እንዲህ ያደርጉበት ምክንያትን ሊጠየቁ ይገባል ” ሲሉ ተናግረዋል።
ለቅሬታው ምላሽ የጠየቅናቸው ስማቸው እንዲነገር ያልፈቀዱ የዩኒቨርሲቲው አካል፣ ስለጉዳዩ በዩኒቨርሲቲው ፌስ ቡክ ገጽ የወጣውን መረጃ እንድንጠቀም ጠቁመዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ተማሪዎቹ ነቃብ፣ ማስክና ሂጃብ ለብሰው እንዳይገቡ ተከልክለው ከግቢ ውጪ በመሆናቸው ትምህርት እያለፋቸው እንደሆነ ገልጸዋል፤ መከልከሉ ልክ ነው ? የሚል ጥያቄ አቅርቧል።
በምላሻቸው፣ “ እንዲህ አይነት ነገር የለም። የተሳሳተ መረጃ ነው። ማንም ተማሪ እዚህ ግቢ በተፈቀደለት ሰዓት ይገባል፤ ይወጣል ” ሲሉ መልሰዋል።
“ የተቋሙንም ሆነ የትምህርት ሚኒስቴር የተቋማት አስተዳደር መመሪያዎችን ተከትሎ የሚተዳደር ነውና ተቋሙ ያንን ነው እያደረግን ያለነው ” ብለዋል።
ተማሪዎቹ በተጨባጭ ከግቢ ውጪ እንደሆኑ፣ ክላስ እያለፋቸው እንደሆነ በድጋሚ የገለጽንላቸው እኝሁ አካል፣ በድጋሚም “ የለም ” የሚል ማስተባበያ ነው የሰጡት።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ፣ የጌዴኦ ዞን እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤትን ተማሪዎች ደረሰብን የሚሉት ክልከላ ምንድነው ? ዩኒቨርሲቲው “ ሀሰተኛ መረጃ ነው ” ብሏልና እናንተ ጉዳዩን አይታችሁት ነበር ? ሲል ማረጋገጫ ጠይቋል።
ምክር ቤቱ ምን መለሰ ?
“ ጉዳዩ ከወር በፊት ደርሶን ነበር። እየቆየ ከፍ እያለ መጥቶ ተማሪዎች ግቢ ለመግባት ሲከለከሉ እኛም ደብዳቤ ፅፈን ነበር ችግሩ እንዲፈታ።
ዩኒቨርሲቲው እርከን ያልጠበቀ ጉዳይ ተደርጎ ታይቶ ነው፤ ተማሪዎቹን እናገኛቸዋለን የሚል ጥሩ ስሜት ነበረው።
የእስልምና አለባበስ ከጥንት ጀምሮ ራሱን የቻለ ሊቃውንቶች ያስቀመጡት ነው። ይሄ የተሻለውና ተመራጭ የሆነው አለባበስ ነው ” ብሏል።
(ጉዳዩን የምንከታተለው ይሆናል)
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
🔴 “ 44 ሴት ተማሪዎችን ‘ጥቁር ማስክ አድርጋችኋል አናስገባም’ ብለው፣ ኒቃብ የለበስን 7 ሴቶችንም ከልክለውን ውጪ አደርን ” - ሙስሊም ተማሪዎች
🔵 “ የትምህርት ሚኒስቴር የተቋማትን አስተዳደርና መመሪያዎችን ተከትሎ የሚተዳደር ነውና ተቋሙ ያንን ነው እያደረግን ያለነው ” - ዲላ ዩኒቨርሲቲ
የዲላ ዩኒቨርሲቲ ሴት ሙስሊም ተማሪዎች ኒቃብ፣ ጥቁር ማስክ እንዳይለብሱ በመከልከላቸው ከትምህርታቸው እየተስተጓጎሉ በመሆኑ መፍትሄ እንዲሰጣቸው በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል ጠንከር ያለ ስሞታ አቅርበዋል።
የተማሪዎቹ ዝርዝር ስሞታ ምንድን ነው ?
“ ኒቃብና ጥቁር ማስክ እንዳንለብስ ነው የተከለከልነው። ክልከላው የጀመረው ከአንድ ወር በፊት ነበር። በዚህም ማመልከቻ አስገብተን ነበር መልበስ እንዲፈቀድልን። ሆኖም ግን ምላሽ ሳይሰጠን ቆዬ።
ትምህርታችን በስርዓት እንዳንከታተል አስተጓጎሉን። ቅዳሜ፣ አንዲት እህት ማስክ አድርጋ፣ ሂጃብ ለብሳ በምትገባበት ወቅት ኦዲያ ካምፓስ በሁለቱም በሮች እንዳትገባ ከልክለዋታል።
እንዲያውም ወንዶቹ የግቢው ጥበቆች አስፈራርተው ፊቷን አስከፍተዋታል። እንደዛም ሆኖ ማስክ ለብሳ ወደ ግቢ መግባት እንደማትችል ነግረው መልሰዋታል።
ቅዳሜ ከሰዓት ሁለት ኒቃብ የለበሱ ተማሪዎች ግቢ ሊገቡ ሲሉ ተከልክለዋል። ለምን እንደተከለከሉ ሲጠይቁ ‘ ለደህንነት ሲባል ፊታችሁ መሸፈን የለበትም ’ አሏቸው።
ለደኅንነት ሲባል ከሆነ ሴት ሙስሊም ተማሪዎች በሴት ጥበቃ ተፈትሸው፣ አይዲያቸውን አሳይተው እንዲገቡ ሲጠይቋቸው ‘ ያንችን ፊት ማየት ምንም አይሰራልኝም። ፊትሽን ለምታሳይው አሳይ ’ የሚል መልስ ተሰጠን።
ከዚያ በኋላም ሰኞ እለት ደግሞ ኒቃብ፣ ጥቁር ማስክ መልበስ እንደማይቻል በፕሬዜዳንቱ ጭምር ተወሰነ። የተማሪ ተወካዮች ጠርተው ይህን አሳወቋቸው።
ጥበቃዎቹም ውሳኔውን በመጥቀስ ‘አናስገባም’ አሉን። ማክሰኞ እለት ማታ 44 ሴት ተማሪዎችን ‘ጥቁር ማስክ አድርጋችኋል አናስገባም’ ብለው፣ ኒቃብ የለበስን 7 ሴቶችንም ከልክለውን ውጪ አደርን።
ረቡዕ ጠዋትም ከለር ማስክ አድርገው የገቡትን በፌደራል ጭምር አስፈራርተው ፊታቸውን እንዲገልጡ አድርገው፣ ሂጃብም ማውለቅ እንዳለባቸው አሳሰቧቸው።
ከሰኞ ጀምሮ ክላስም እየተከታተልን አይደለም፣ ኤግዛም አልፎናል፣ አሳይመንትም እያለፈን ነው። ማውለቅ ስለማንችል ከግቢ ውጪ ነን። በቃ ከተማሪነት ውጪ ባለ ህይወት ነን። እንደ ሴትነታችን ትልቅ የመብት ጥሰት ነው የተፈጸመብን።
ከምሽቱ 3 ሰዓት እንዳንገባ ሲከለክሉን የት እንድናድር፣ ምን እንድንለብስ፣ ምን እንደምንምገብ ያሰቡትን አናውቅም። ስለዚህ እንደንገባ ቢፈቅዱም እንዲህ ያደርጉበት ምክንያትን ሊጠየቁ ይገባል ” ሲሉ ተናግረዋል።
ለቅሬታው ምላሽ የጠየቅናቸው ስማቸው እንዲነገር ያልፈቀዱ የዩኒቨርሲቲው አካል፣ ስለጉዳዩ በዩኒቨርሲቲው ፌስ ቡክ ገጽ የወጣውን መረጃ እንድንጠቀም ጠቁመዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ተማሪዎቹ ነቃብ፣ ማስክና ሂጃብ ለብሰው እንዳይገቡ ተከልክለው ከግቢ ውጪ በመሆናቸው ትምህርት እያለፋቸው እንደሆነ ገልጸዋል፤ መከልከሉ ልክ ነው ? የሚል ጥያቄ አቅርቧል።
በምላሻቸው፣ “ እንዲህ አይነት ነገር የለም። የተሳሳተ መረጃ ነው። ማንም ተማሪ እዚህ ግቢ በተፈቀደለት ሰዓት ይገባል፤ ይወጣል ” ሲሉ መልሰዋል።
“ የተቋሙንም ሆነ የትምህርት ሚኒስቴር የተቋማት አስተዳደር መመሪያዎችን ተከትሎ የሚተዳደር ነውና ተቋሙ ያንን ነው እያደረግን ያለነው ” ብለዋል።
ተማሪዎቹ በተጨባጭ ከግቢ ውጪ እንደሆኑ፣ ክላስ እያለፋቸው እንደሆነ በድጋሚ የገለጽንላቸው እኝሁ አካል፣ በድጋሚም “ የለም ” የሚል ማስተባበያ ነው የሰጡት።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ፣ የጌዴኦ ዞን እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤትን ተማሪዎች ደረሰብን የሚሉት ክልከላ ምንድነው ? ዩኒቨርሲቲው “ ሀሰተኛ መረጃ ነው ” ብሏልና እናንተ ጉዳዩን አይታችሁት ነበር ? ሲል ማረጋገጫ ጠይቋል።
ምክር ቤቱ ምን መለሰ ?
“ ጉዳዩ ከወር በፊት ደርሶን ነበር። እየቆየ ከፍ እያለ መጥቶ ተማሪዎች ግቢ ለመግባት ሲከለከሉ እኛም ደብዳቤ ፅፈን ነበር ችግሩ እንዲፈታ።
ዩኒቨርሲቲው እርከን ያልጠበቀ ጉዳይ ተደርጎ ታይቶ ነው፤ ተማሪዎቹን እናገኛቸዋለን የሚል ጥሩ ስሜት ነበረው።
የእስልምና አለባበስ ከጥንት ጀምሮ ራሱን የቻለ ሊቃውንቶች ያስቀመጡት ነው። ይሄ የተሻለውና ተመራጭ የሆነው አለባበስ ነው ” ብሏል።
(ጉዳዩን የምንከታተለው ይሆናል)
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update 🔴 “ 44 ሴት ተማሪዎችን ‘ጥቁር ማስክ አድርጋችኋል አናስገባም’ ብለው፣ ኒቃብ የለበስን 7 ሴቶችንም ከልክለውን ውጪ አደርን ” - ሙስሊም ተማሪዎች 🔵 “ የትምህርት ሚኒስቴር የተቋማትን አስተዳደርና መመሪያዎችን ተከትሎ የሚተዳደር ነውና ተቋሙ ያንን ነው እያደረግን ያለነው ” - ዲላ ዩኒቨርሲቲ የዲላ ዩኒቨርሲቲ ሴት ሙስሊም ተማሪዎች ኒቃብ፣ ጥቁር ማስክ እንዳይለብሱ በመከልከላቸው ከትምህርታቸው…
#Update
🔴 " ዩኒቨርሲቲያችን እንደ ሁሉም የሀገራችን ዩኒቨርሲቲዎች ሁሉ በሴኩላሪዝምና ብዝሃ ሃይማኖትን ተረድቶና አክብሮ የሚሰራ ተቋም ነዉ " - የዲላ ዩኒቨርሲቲ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ
➡️ " ወደ ዩኒቨርሲቲዉ ቅጥር ግቢ እንዳንገባ ተደርገናል በዚህም ምክንያት በሁለት መስጊዶች ተጠልለን እንገኛለን " - ሙስሊም ተማሪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ
የዲላ ዩኒቨርሲቲ ሴት የእስልምና እምነት ተከታይ / ሙስሊም ተማሪዎች " በሃይማኖታዊ አለባበሳችን ምክንያት ወደ ዩኒቨርሲቲዉ ቅጥር ግቢ እንዳንገባ ተደርገናል በዚህም ምክንያት በሁለት መስጊዶች ተጠልለን እንገኛለን " ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቅሬታቸዉን አድርሰዋል።
ከቅሬታ አቅራቢዎቹ ተማሪዎቹ መካከል የዲላ ዩኒቨርሲቲ ዋና ግቢ እና ሰመራ ካምፓስ ሴት ሙስሊም ተማሪዎች " አትግቡ መባል ከጀመርን አንድ ወር ገደማ ሆኗል " ያሉን ሲሆን " በሙስሊም ተማሪዎች ተወካይ ኮሚቴ አማካኝነት በፅሑፍ ቅሬታ አቅርበን ስንጠባበቅ ከሰኞ ጥር 12/2017 ዓ/ም ጀምሮ ' ንቃብ ማድረግ አትችሉም ' ተብለን ግቢ እንዳንገባ በመከልከላችን በመስጊዶች ዉስጥ ተጠልለን እንገኛለን " ብለዋል።
የዲላ ዩኒቨርሲቲ የሙስሊም ተማሪዎች ተወካይ ኑሬዲን አብደላህ ፤ " ችግሩ ከተማሪዎች ባሻገር አንዲት የዩኒቨርስቲው መምህርትም ጭምር ያካተተ ስለነበር ለዩኒቨርሲቲዉ የበላይ አመራሮች ቅሬታ በፅሑፍ አቅርበን በቂ ምላሽ ስላልተሰጠን ተማሪዎች በዚህ የፈተና ወቅት በመስጊዶች ዉስጥ ተጠልለዉ ይገኛሉ " ብሏል።
የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ዋና ስራ አስኪያጅ ከማል ሀሩን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል ፥ በደቡብ ኢትዮጵያ የእስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት በኩል 150 ተማሪዎች ከእስላማዊ አለባበሱ ጋር በተያያዘ ክልከላ እንደተደረገባቸውና አብዛኞቹ የፈተና ወቅት በመሆኑ ኒቃብ አዉልቀዉ ማስክ እየተጠቀሙ ወደ ግቢ እንደገቡ ገልጸዋል።
ስራ አስኪያጁ ፥ 22 የሚሆኑ ሴት ተማሪዎች አሁንም በመስጊዶች ተጠልለው እንደሚገኙ መረጃዉ በጽሑፍ እንደደረሳቸው ገልፀዉ ጉዳዩን ለትምህርት ሚንስትር በፅሑፍ ማቅረባቸውንና " ባለድርሻ አካላት የቆዩ መመሪያዎችን ዳግም ማየት ይጠበቅባቸዋል " ብለዋል።
" ከሁለት ዓመታት በፊት በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ተመሳሳይ ችግር ተነስቶ እንዲረግብ ተደርጎ የነበረ ሲሆን አሁንም በሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች ችግሩ ላለመነሳቱ ዋስተና የሌለ በመሆኑ እነዚህን አጋጣሚዎች ለሌሎች ፍላጎቶች በሚጠቀሙ አካላት ጉዳዩ ወዳልተፈለገ አቅጣጫ እንዳያመራ ዘላቂ መፍትሔ ሊበጅለት ይገባል " ብለዋል።
ቲክቫህ የዲላ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ኤልያስ አለሙ (ዶ/ር)ን ስለ ጉዳዩ አነጋግሯቸዋል።
ዶክተር ለቲክቫህ በሰጡት ቃል ፥ " የዲላ ዩኒቨርሲቲ እንደ ሁሉም የሀገራችን ዩኒቨርሲቲዎች ሁሉ በሴኩላሪዝምና ብዝሃ ሃይማኖትን ተረድቶና አክብሮ የሚሰራ ተቋም ነዉ " ብለዋል።
" በዩኒቨርሲቲው ሴት ሙስሊም ተማሪዎች ሂጃብ እንዳይለብሱ አልተከለከለም ኒቃብ ደግሞ አስቀድሞም በዩኒቨርሲቲ አይደረግም ነበር " ብለዋል።
ፕሬዝዳንቱ አክለዉም " በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች ዩኒቨርሲቲዉ ' ሙስሊም ሴት ተማሪዎችን ሂጃብ መልበስ ከልክሏል ' በሚል የሚሰራጨዉ መረጃ ትክክል ያልሆነ ሀሰተኛ መረጃ ነው " ሲሉ ገልፀዋል።
በዚህ ምክንያት ወጪ አሉ ስለተባሉ ተማሪዎች እና ስላመለጣቸዉ ፈተናዎች እንዲሁም ስለዩኒቨርስቲው ቀጣይ አቋም ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ለቀረበዉ ጥያቄ የተለየ ዉሳኔ አለመኖሩን ዩኒቨርስቲው አስታዉቋል።
#TikvahEthiopiaFamilyHawassa
@tikvahethiopia
🔴 " ዩኒቨርሲቲያችን እንደ ሁሉም የሀገራችን ዩኒቨርሲቲዎች ሁሉ በሴኩላሪዝምና ብዝሃ ሃይማኖትን ተረድቶና አክብሮ የሚሰራ ተቋም ነዉ " - የዲላ ዩኒቨርሲቲ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ
➡️ " ወደ ዩኒቨርሲቲዉ ቅጥር ግቢ እንዳንገባ ተደርገናል በዚህም ምክንያት በሁለት መስጊዶች ተጠልለን እንገኛለን " - ሙስሊም ተማሪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ
የዲላ ዩኒቨርሲቲ ሴት የእስልምና እምነት ተከታይ / ሙስሊም ተማሪዎች " በሃይማኖታዊ አለባበሳችን ምክንያት ወደ ዩኒቨርሲቲዉ ቅጥር ግቢ እንዳንገባ ተደርገናል በዚህም ምክንያት በሁለት መስጊዶች ተጠልለን እንገኛለን " ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቅሬታቸዉን አድርሰዋል።
ከቅሬታ አቅራቢዎቹ ተማሪዎቹ መካከል የዲላ ዩኒቨርሲቲ ዋና ግቢ እና ሰመራ ካምፓስ ሴት ሙስሊም ተማሪዎች " አትግቡ መባል ከጀመርን አንድ ወር ገደማ ሆኗል " ያሉን ሲሆን " በሙስሊም ተማሪዎች ተወካይ ኮሚቴ አማካኝነት በፅሑፍ ቅሬታ አቅርበን ስንጠባበቅ ከሰኞ ጥር 12/2017 ዓ/ም ጀምሮ ' ንቃብ ማድረግ አትችሉም ' ተብለን ግቢ እንዳንገባ በመከልከላችን በመስጊዶች ዉስጥ ተጠልለን እንገኛለን " ብለዋል።
የዲላ ዩኒቨርሲቲ የሙስሊም ተማሪዎች ተወካይ ኑሬዲን አብደላህ ፤ " ችግሩ ከተማሪዎች ባሻገር አንዲት የዩኒቨርስቲው መምህርትም ጭምር ያካተተ ስለነበር ለዩኒቨርሲቲዉ የበላይ አመራሮች ቅሬታ በፅሑፍ አቅርበን በቂ ምላሽ ስላልተሰጠን ተማሪዎች በዚህ የፈተና ወቅት በመስጊዶች ዉስጥ ተጠልለዉ ይገኛሉ " ብሏል።
የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ዋና ስራ አስኪያጅ ከማል ሀሩን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል ፥ በደቡብ ኢትዮጵያ የእስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት በኩል 150 ተማሪዎች ከእስላማዊ አለባበሱ ጋር በተያያዘ ክልከላ እንደተደረገባቸውና አብዛኞቹ የፈተና ወቅት በመሆኑ ኒቃብ አዉልቀዉ ማስክ እየተጠቀሙ ወደ ግቢ እንደገቡ ገልጸዋል።
ስራ አስኪያጁ ፥ 22 የሚሆኑ ሴት ተማሪዎች አሁንም በመስጊዶች ተጠልለው እንደሚገኙ መረጃዉ በጽሑፍ እንደደረሳቸው ገልፀዉ ጉዳዩን ለትምህርት ሚንስትር በፅሑፍ ማቅረባቸውንና " ባለድርሻ አካላት የቆዩ መመሪያዎችን ዳግም ማየት ይጠበቅባቸዋል " ብለዋል።
" ከሁለት ዓመታት በፊት በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ተመሳሳይ ችግር ተነስቶ እንዲረግብ ተደርጎ የነበረ ሲሆን አሁንም በሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች ችግሩ ላለመነሳቱ ዋስተና የሌለ በመሆኑ እነዚህን አጋጣሚዎች ለሌሎች ፍላጎቶች በሚጠቀሙ አካላት ጉዳዩ ወዳልተፈለገ አቅጣጫ እንዳያመራ ዘላቂ መፍትሔ ሊበጅለት ይገባል " ብለዋል።
ቲክቫህ የዲላ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ኤልያስ አለሙ (ዶ/ር)ን ስለ ጉዳዩ አነጋግሯቸዋል።
ዶክተር ለቲክቫህ በሰጡት ቃል ፥ " የዲላ ዩኒቨርሲቲ እንደ ሁሉም የሀገራችን ዩኒቨርሲቲዎች ሁሉ በሴኩላሪዝምና ብዝሃ ሃይማኖትን ተረድቶና አክብሮ የሚሰራ ተቋም ነዉ " ብለዋል።
" በዩኒቨርሲቲው ሴት ሙስሊም ተማሪዎች ሂጃብ እንዳይለብሱ አልተከለከለም ኒቃብ ደግሞ አስቀድሞም በዩኒቨርሲቲ አይደረግም ነበር " ብለዋል።
ፕሬዝዳንቱ አክለዉም " በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች ዩኒቨርሲቲዉ ' ሙስሊም ሴት ተማሪዎችን ሂጃብ መልበስ ከልክሏል ' በሚል የሚሰራጨዉ መረጃ ትክክል ያልሆነ ሀሰተኛ መረጃ ነው " ሲሉ ገልፀዋል።
በዚህ ምክንያት ወጪ አሉ ስለተባሉ ተማሪዎች እና ስላመለጣቸዉ ፈተናዎች እንዲሁም ስለዩኒቨርስቲው ቀጣይ አቋም ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ለቀረበዉ ጥያቄ የተለየ ዉሳኔ አለመኖሩን ዩኒቨርስቲው አስታዉቋል።
#TikvahEthiopiaFamilyHawassa
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update
" ህዝቡ በመረጣችሁት መንገድ ይታገላችኋል " - በእነ አቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራው ህወሓት
በምክትል ሊቀ-መንበር አቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራ ህወሓት ፤ ትናንት ጥር 15/2017 ዓ.ም " የበላይ ወታደራዊ ኃይል አመራሮች ነን " በሚል የተሰጠውን መግለጫ የሚቃወም መግለጫ አውጥቷል።
በዚህም መግለጫው ፥ በሊቀ-መንበር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራውን ህወሓት" የነሃሴው " ብሎ ሲጠራው ራሱን ደግሞ " ነባር " በማለት ገልጿል።
" የበላይ ወታደራዊ ኃይል አመራሮች ነን " በሚል ያወጡት መግለጫ የ " ነሃሴው ህወሓት ህዝቡን እና ሰራዊቱ ለመበታተነ የሰራው ክፋት ውጤት ነው " በማለት ገልፆታል።
" የነሃሴው ህወሓት ህዝብን እና የኢትዮጵያ ብሄራዊ የምርጫ ቦርድ ያልተቀበለው ጉባኤ በማካሄድ ነባሩን ህወሓት እንዲዳከም ሰርቷል " ሲል በአቶ ጌታቸው የሚመራው ህወሓት ፤ " ወታደራዊ አምባገንነት ታግሎ ዴሞክራሲያዊ እና ህዝባዊ መንግስት የጨበጠ ህዝብ ወደ ኋላ አይመለስም " ብሏል።
" የበላይ ወታደራዊ ኃይል አመራሮች ነን " በሚል ስም የወጣውን መግለጫ " የጦርነት አዋጅ ነው ፤ በህዝብ ላይ አፋኝ አስተዳደር የሚጭን ተቀባይነት የሌለውና የውድቀት ጥሪ " ሲል ገልጾታል።
" ህዝቡ በመረጣችሁት መንገድ ይታገላቹሃል " ያለው በአቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራው ህወሓት " የጦርነት አዋጃችሁ የፕሪቶሪያ ስምምነት አፍርሶ ፤ ትግራይ ለአህጉራዊ ዓለምአቀፋዊ ተነጥሎ እና ውግዘት የሚዳርግ ህዝቡን ለአደጋ የሚያጋልጥ ነው " ሲል አክሏል።
የአነ አቶ ጌታቸው ቡድን መግለጫውን መላ የትግራይ ኃይል አባላት እንዲያወግዙት ጠይቆ " ህዝብን እና መንግስታችሁ በሚስጡዋችሁ አቅጣጫ ብቻ እንድትንቀሳቀሱ ጥሪያችን እናቀርባለን " ሲል አሳስቧል።
ህዝቡ እና ወጣቱ በአደገኛ ሁኔታ ላይ እንደሚገኙም ገልጾ ይህንኑ በመገንዘብ ከመቼውም ጊዜ በላይ ትግሉ በማጠናከር ለመብቱ ለአንድነቱ እና ለህልውናው በመታገል የተደቀነበት አደጋ እንዲመከት ጥሪ አቅርቧል።
ለህዝቡ ፣ ለዳያስፓራ ፣ ለተፎካካሪ ፓርቲዎች እና ሲቪክ ማህበራት " የበላይ ወታደራዊ ኃይል አመራሮች ነን " በሚል ስም የወጣው መግለጫ እንዲያወግዙት ጠይቀዋል።
መግለጫውን ያወጡት አመራሮች ያለፈ ታሪካቸው ከሚያጎድፍ ተግባር በመውጣት አሁን የፈፀሙት ስህተት በአስቸኳይ እንዲያርሙ እና ታሪካቸው እንዲያድሱ ጥሪ አቅርቧል።
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
" ህዝቡ በመረጣችሁት መንገድ ይታገላችኋል " - በእነ አቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራው ህወሓት
በምክትል ሊቀ-መንበር አቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራ ህወሓት ፤ ትናንት ጥር 15/2017 ዓ.ም " የበላይ ወታደራዊ ኃይል አመራሮች ነን " በሚል የተሰጠውን መግለጫ የሚቃወም መግለጫ አውጥቷል።
በዚህም መግለጫው ፥ በሊቀ-መንበር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራውን ህወሓት" የነሃሴው " ብሎ ሲጠራው ራሱን ደግሞ " ነባር " በማለት ገልጿል።
" የበላይ ወታደራዊ ኃይል አመራሮች ነን " በሚል ያወጡት መግለጫ የ " ነሃሴው ህወሓት ህዝቡን እና ሰራዊቱ ለመበታተነ የሰራው ክፋት ውጤት ነው " በማለት ገልፆታል።
" የነሃሴው ህወሓት ህዝብን እና የኢትዮጵያ ብሄራዊ የምርጫ ቦርድ ያልተቀበለው ጉባኤ በማካሄድ ነባሩን ህወሓት እንዲዳከም ሰርቷል " ሲል በአቶ ጌታቸው የሚመራው ህወሓት ፤ " ወታደራዊ አምባገንነት ታግሎ ዴሞክራሲያዊ እና ህዝባዊ መንግስት የጨበጠ ህዝብ ወደ ኋላ አይመለስም " ብሏል።
" የበላይ ወታደራዊ ኃይል አመራሮች ነን " በሚል ስም የወጣውን መግለጫ " የጦርነት አዋጅ ነው ፤ በህዝብ ላይ አፋኝ አስተዳደር የሚጭን ተቀባይነት የሌለውና የውድቀት ጥሪ " ሲል ገልጾታል።
" ህዝቡ በመረጣችሁት መንገድ ይታገላቹሃል " ያለው በአቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራው ህወሓት " የጦርነት አዋጃችሁ የፕሪቶሪያ ስምምነት አፍርሶ ፤ ትግራይ ለአህጉራዊ ዓለምአቀፋዊ ተነጥሎ እና ውግዘት የሚዳርግ ህዝቡን ለአደጋ የሚያጋልጥ ነው " ሲል አክሏል።
የአነ አቶ ጌታቸው ቡድን መግለጫውን መላ የትግራይ ኃይል አባላት እንዲያወግዙት ጠይቆ " ህዝብን እና መንግስታችሁ በሚስጡዋችሁ አቅጣጫ ብቻ እንድትንቀሳቀሱ ጥሪያችን እናቀርባለን " ሲል አሳስቧል።
ህዝቡ እና ወጣቱ በአደገኛ ሁኔታ ላይ እንደሚገኙም ገልጾ ይህንኑ በመገንዘብ ከመቼውም ጊዜ በላይ ትግሉ በማጠናከር ለመብቱ ለአንድነቱ እና ለህልውናው በመታገል የተደቀነበት አደጋ እንዲመከት ጥሪ አቅርቧል።
ለህዝቡ ፣ ለዳያስፓራ ፣ ለተፎካካሪ ፓርቲዎች እና ሲቪክ ማህበራት " የበላይ ወታደራዊ ኃይል አመራሮች ነን " በሚል ስም የወጣው መግለጫ እንዲያወግዙት ጠይቀዋል።
መግለጫውን ያወጡት አመራሮች ያለፈ ታሪካቸው ከሚያጎድፍ ተግባር በመውጣት አሁን የፈፀሙት ስህተት በአስቸኳይ እንዲያርሙ እና ታሪካቸው እንዲያድሱ ጥሪ አቅርቧል።
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update
" ' የበላይ ወታደራዊ ኃይል አመራሮች ነን ' በሚል የተሰጠው መግለጫ የሰራዊቱ እና የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ሃሳብ እና ውሳኔ እንዳልሆነ ለኢትዮጵያ መንግስት እናሳውቃለን " - የትግራይ ክልል ጊዚያዊ አስተዳደር ካቢኔ
የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ካቢኔ " የበላይ ወታደራዊ ኃይል አመራሮች ነን " በሚል የተሰጠው መግለጫ ተፈፃሚነት እንዳይኖረው (null and void እንዲሆን) ወስኗል።
" በሰራዊቱ የኮር አመራር የሚል አደረጃጀት እውቅና የለውም " ሲል የወሰነው ካቢነኔው " የበላይ ወታደራዊ ኃይል አመራሮች ነን " በሚል ጥር 14/2017 ዓ.ም የተሰጠውን መግለጫ ሙሉ በሙሉ ውድቅ አድርጎታል።
ካቢኔው ዛሬ ቅዳሜ ጥር 17/2017 ዓ.ም በሰጠው መግለጫ ፤ "የበላይ ወታደራዊ ኃይል አመራሮች ነን " በሚል የተሰጠው መግለጫ ፦
- ለአንድ ቡድን የወገነ
- መንግስት የሚፈርስ
- ሰራዊት የሚበትን
- የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት የሚያፈርስ እና መሰረታዊ ችግር ያለው በመሆኑ በአስቸኳይ እንዲታረም እና ታች ወርዶ እንዳይተገበር ወስኗል።
" የተሰጠው መግለጫ ከሰራዊት ተልእኮ ያፈነገጠ ፣ ተቋማዊ አሰራር የጣሰ " ነው "ሲል የገለፀው ካቢኔው ፥ " ' አመራር ነኝ ' በሚል በዚህ ሁኔታ ተሰብስቦ ውሳኔ ለማሳለፍ የሚያስችል ስልጣን የለውም " ብሏል።
" ' የበላይ ወታደራዊ ኃይል አመራሮች ነን ' በሚል በተሰጠው መግለጫ መንግስታዊ ማስተካከያ እንዲደረግ አስመልክቶ የቀረበው አቋም የአንዱ ቡድን የስልጣን ጥማት ለማርካት ሲባል የፕሪቶሪያ ውል የሚያፈርስ ሃላፊነት የጎደለው ውሳኔ ነው " አደገኛ ነው ' ሲል ገልጾ በአስቸኳይ የሚታረምበት አቅጣጫ ማስቀመጡን አሳውቋል።
ካቢኔው ባወጣው የውሳኔ መግለጫ ለኢትዮጵያ መንግስት ባስተላለፈው መልእክት " ' የበላይ ወታደራዊ ኃይል አመራሮች ነን ' በሚል በተሰጠው መግለጫ የሰራዊቱ እና የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ሃሳብ እና ውሳኔ አይደለም በመሆኑም ወድቅ አድርጎታል ፤ ሰራዊቱ እና የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር አሁንም ለፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ተገዢ በመሆን ጅምር ሰላሙ እንዲጎለብት የትግራይ ሉአላዊ ግዛት ተከብሮ ተፈናቃዮች ወደ ቄያቸው እንዲመለሱ የጀመረውን ትግል አጠናክሮ ይቀጥላል " ብሏል።
" የትግራይ ህዝብና ጊዚያዊ አስተዳደሩ ፍላጎት ሰላም ነው " ሲል ለአለም አቀፍ ማህበረሰብ መልእክት ያስተላለፈው ካቢኔው ፤ " የፕሪቶሪያ የሰላም ውል በአፈፃፀም ብዙ ችግሮች ቢኖሩትም በስምምነቱ አፈፃፀም የሚነሱ ችግሮች በሰላማዊ እና ፓለቲካዊ ትግል እንዲመለሱ የአለም አቀፍ ማህበረሰብ የተሟላ ድጋፍ እንዲያደርግ " ሲል ጥሪ አስተላልፏል።
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
" ' የበላይ ወታደራዊ ኃይል አመራሮች ነን ' በሚል የተሰጠው መግለጫ የሰራዊቱ እና የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ሃሳብ እና ውሳኔ እንዳልሆነ ለኢትዮጵያ መንግስት እናሳውቃለን " - የትግራይ ክልል ጊዚያዊ አስተዳደር ካቢኔ
የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ካቢኔ " የበላይ ወታደራዊ ኃይል አመራሮች ነን " በሚል የተሰጠው መግለጫ ተፈፃሚነት እንዳይኖረው (null and void እንዲሆን) ወስኗል።
" በሰራዊቱ የኮር አመራር የሚል አደረጃጀት እውቅና የለውም " ሲል የወሰነው ካቢነኔው " የበላይ ወታደራዊ ኃይል አመራሮች ነን " በሚል ጥር 14/2017 ዓ.ም የተሰጠውን መግለጫ ሙሉ በሙሉ ውድቅ አድርጎታል።
ካቢኔው ዛሬ ቅዳሜ ጥር 17/2017 ዓ.ም በሰጠው መግለጫ ፤ "የበላይ ወታደራዊ ኃይል አመራሮች ነን " በሚል የተሰጠው መግለጫ ፦
- ለአንድ ቡድን የወገነ
- መንግስት የሚፈርስ
- ሰራዊት የሚበትን
- የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት የሚያፈርስ እና መሰረታዊ ችግር ያለው በመሆኑ በአስቸኳይ እንዲታረም እና ታች ወርዶ እንዳይተገበር ወስኗል።
" የተሰጠው መግለጫ ከሰራዊት ተልእኮ ያፈነገጠ ፣ ተቋማዊ አሰራር የጣሰ " ነው "ሲል የገለፀው ካቢኔው ፥ " ' አመራር ነኝ ' በሚል በዚህ ሁኔታ ተሰብስቦ ውሳኔ ለማሳለፍ የሚያስችል ስልጣን የለውም " ብሏል።
" ' የበላይ ወታደራዊ ኃይል አመራሮች ነን ' በሚል በተሰጠው መግለጫ መንግስታዊ ማስተካከያ እንዲደረግ አስመልክቶ የቀረበው አቋም የአንዱ ቡድን የስልጣን ጥማት ለማርካት ሲባል የፕሪቶሪያ ውል የሚያፈርስ ሃላፊነት የጎደለው ውሳኔ ነው " አደገኛ ነው ' ሲል ገልጾ በአስቸኳይ የሚታረምበት አቅጣጫ ማስቀመጡን አሳውቋል።
ካቢኔው ባወጣው የውሳኔ መግለጫ ለኢትዮጵያ መንግስት ባስተላለፈው መልእክት " ' የበላይ ወታደራዊ ኃይል አመራሮች ነን ' በሚል በተሰጠው መግለጫ የሰራዊቱ እና የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ሃሳብ እና ውሳኔ አይደለም በመሆኑም ወድቅ አድርጎታል ፤ ሰራዊቱ እና የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር አሁንም ለፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ተገዢ በመሆን ጅምር ሰላሙ እንዲጎለብት የትግራይ ሉአላዊ ግዛት ተከብሮ ተፈናቃዮች ወደ ቄያቸው እንዲመለሱ የጀመረውን ትግል አጠናክሮ ይቀጥላል " ብሏል።
" የትግራይ ህዝብና ጊዚያዊ አስተዳደሩ ፍላጎት ሰላም ነው " ሲል ለአለም አቀፍ ማህበረሰብ መልእክት ያስተላለፈው ካቢኔው ፤ " የፕሪቶሪያ የሰላም ውል በአፈፃፀም ብዙ ችግሮች ቢኖሩትም በስምምነቱ አፈፃፀም የሚነሱ ችግሮች በሰላማዊ እና ፓለቲካዊ ትግል እንዲመለሱ የአለም አቀፍ ማህበረሰብ የተሟላ ድጋፍ እንዲያደርግ " ሲል ጥሪ አስተላልፏል።
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" ወደ ግርግር እና ረብሻ የሚመሩ የተዛቡ ሁከት ቀስቃሽ መልዕክቶች እየተሰራጩ ነው " - የትግራይ የሰላም እና የፀጥታ ቢሮ የህዝቡ ሰላም እና ፀጥታ በሚያውኩ አካላትም ይሁን ግለሰቦችላይ የማያዳግም አርምጃ እንደሚወሰድ የትግራይ የሰላም እና የፀጥታ ቢሮ በጥብቅ አስጠነቀቀ። ቢሮው " የበላይ ወታደራዊ ኃይል አመራሮች " ጥር 14 /2017 ዓ.ም ያወጡትን መግለጫ ተከትሎ " የማያሻማ የመግለጫውን ትርጉም…
#Update
🚨 " ለእሁድ ጥር 18/2017 ዓ.ም የተፈቀደ የተጠራ ሰልፍ የለም " - የትግራይ የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ፅህፈት ቤት
🔵 " እሁድ ጥር 18/2017 ዓ.ም መቐለ ጨምሮ በመላው ትግራይ የሚካሄደው ሰልፍ መግባባት የተደረሰበት እና የተሟላ ጥበቃ የሚደረገበት ነው " - በሊቀ-መንበር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው ህወሓት
🔴 " ህወሓት ለእሁድ ጥር 18/2017 ዓ.ም የጠራውን ሰላማዊ ሰልፍ በቂ ጥበቃ ለመስጠት ስለምንቸገር ቀን እንዲቀይር እናስታውቃለን " - የትግራይ ፓሊስ ኮሚሽን
እሁድ ጥር 18/2017 ዓ.ም ጥር 14/2017 ዓ.ም " የበላይ ወታደራዊ ኃይል አመራሮች ነን " በሚል የተሰጠው ውሳኔ የሚደግፍ እና የሚቃወም ሰልፍ መጠራቱን ተከትሎ ፓሊስ ሰልፉን መሸፈን የሚችል የሰው ሃይል ስለሚያንሰው እንዲቀየር ጠይቀዋል።
ይሁን እንጂ ጥር 17/2017 ዓ.ም ፓሊስ የሰጠው የሰልፍ ክልከላ ማሳሰብያ በመጣስ በትግራይ ደቡባዊ ዞን የተለያዩ ከተሞች " የበላይ ወታደራዊ ኃይል አመራሮች ነን " በሚል የተሰጠው ውሳኔ የሚቃወም ሰላማዊ ሰልፍ ተካሂደዋል።
እሁድ ጥር 18/2017 ዓ.ም በሊቀ-መንበር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው ህወሓት " የበላይ ወታደራዊ ኃይል አመራሮች ነን " በሚል የተሰጠው ውሳኔ የሚደግፍ ሰላማዊ ስልፍ እንዲካሄድ ጥሪ አቅርቧል።
የክልሉ ፓሊስ " በቂ ጥበቃ ስለሌለኝ ሰላማዊ ስልፍ የሚካሄድበት ቀን እንዲቀየር " ቢያሳስብም በሊቀ-መንበር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው ህወሓት ሰልፉ የተሟላ የፀጥታ ጥበቃ ያለውና ተፈፃሚ የሚሆን ሲል የፅሁፍ መግለጫ ሰጥቷል።
" እሁድ ጥር 18/2017 ዓ.ም መንግስት በመቐለ የጠራው ሰብሰባም ይሁን ሰልፍ የለም " ያለው የክልሉ የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ፅህፈት ቤት ፤ " ሰልፍ ይካሄዳል " በማለት ቤት ለቤት እየተዘዋወሩ የሚያደናግሩት አካላት እና ግለሰቦች ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ አስጠንቅቋል።
@tikvahethiopia
🚨 " ለእሁድ ጥር 18/2017 ዓ.ም የተፈቀደ የተጠራ ሰልፍ የለም " - የትግራይ የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ፅህፈት ቤት
🔵 " እሁድ ጥር 18/2017 ዓ.ም መቐለ ጨምሮ በመላው ትግራይ የሚካሄደው ሰልፍ መግባባት የተደረሰበት እና የተሟላ ጥበቃ የሚደረገበት ነው " - በሊቀ-መንበር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው ህወሓት
🔴 " ህወሓት ለእሁድ ጥር 18/2017 ዓ.ም የጠራውን ሰላማዊ ሰልፍ በቂ ጥበቃ ለመስጠት ስለምንቸገር ቀን እንዲቀይር እናስታውቃለን " - የትግራይ ፓሊስ ኮሚሽን
እሁድ ጥር 18/2017 ዓ.ም ጥር 14/2017 ዓ.ም " የበላይ ወታደራዊ ኃይል አመራሮች ነን " በሚል የተሰጠው ውሳኔ የሚደግፍ እና የሚቃወም ሰልፍ መጠራቱን ተከትሎ ፓሊስ ሰልፉን መሸፈን የሚችል የሰው ሃይል ስለሚያንሰው እንዲቀየር ጠይቀዋል።
ይሁን እንጂ ጥር 17/2017 ዓ.ም ፓሊስ የሰጠው የሰልፍ ክልከላ ማሳሰብያ በመጣስ በትግራይ ደቡባዊ ዞን የተለያዩ ከተሞች " የበላይ ወታደራዊ ኃይል አመራሮች ነን " በሚል የተሰጠው ውሳኔ የሚቃወም ሰላማዊ ሰልፍ ተካሂደዋል።
እሁድ ጥር 18/2017 ዓ.ም በሊቀ-መንበር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው ህወሓት " የበላይ ወታደራዊ ኃይል አመራሮች ነን " በሚል የተሰጠው ውሳኔ የሚደግፍ ሰላማዊ ስልፍ እንዲካሄድ ጥሪ አቅርቧል።
የክልሉ ፓሊስ " በቂ ጥበቃ ስለሌለኝ ሰላማዊ ስልፍ የሚካሄድበት ቀን እንዲቀየር " ቢያሳስብም በሊቀ-መንበር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው ህወሓት ሰልፉ የተሟላ የፀጥታ ጥበቃ ያለውና ተፈፃሚ የሚሆን ሲል የፅሁፍ መግለጫ ሰጥቷል።
" እሁድ ጥር 18/2017 ዓ.ም መንግስት በመቐለ የጠራው ሰብሰባም ይሁን ሰልፍ የለም " ያለው የክልሉ የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ፅህፈት ቤት ፤ " ሰልፍ ይካሄዳል " በማለት ቤት ለቤት እየተዘዋወሩ የሚያደናግሩት አካላት እና ግለሰቦች ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ አስጠንቅቋል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
🚨#Alert ከደቂቃዎች በፊት ከፍ ያለ የመሬት መንቀጥቀጥ አዋሽ አካባቢ ተከስቷል። ንዝሩት በአዲስ አበባና ሌሎች ከተሞች ተሰምቷል። ቃላቸውን የላኩልን የቤተሰባች አባላት " ዛሬ በጣም የሚያስፈራ ነበር። ሰሞኑን ድግግሞሹ ቀንሶ ነበር። ዛሬ በድንገት በሚያስፈራ ሁኔታ ነው የተሰማን " ብለዋል። @tikvahethiopia
#Update
ከጥቂት ደቂቃዎች በፊት (4:38 ላይ) ተከስቶ የነበረው የመሬት መንቀጥቀጥ ከአዋሽ 36 ኪሎሜትር ርቀት ላይ እንደሆነ የጀርመኑ የጂኦሳይንስ ሪሰርች ማዕከል ገልጿል።
መንቀጥቀጡ በሬክተር ስኬል 4.9 መመዝገቡን አሳውቋል።
በርካታ ሰዎች የዛሬው ከወትሮው የተለየ ነበር ብለዋል።
የመሬት መንቀጥቀጡ የነበረበት አካባቢ ያሉ ወገኖች " አስፈሪ " ሲሉ ገልጸዋል።
ንዝረቱ የተሰማባቸው አካባቢዎች ደግሞ ከወትሮው የተለየ እንደነበር ታውቋል።
ለአብነት አዲስ አበባ ብዙ ሰዎች ህንጻ ላይ የነበሩ ተሰምቷቸው መደናገጣቸውን ገልጸውልናል። ለተወሰኑ ሰከንዶች የቆየ ቢሆንም የህንጻ ንቅናቄ ስሜት ፣ የመንስታወት መርገፍገፍ እንደተመለከቱ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
አንድ የቤተሰባችን አባል " 4ኛ ፎቅ ላይ በተቀመጥኩበት መስታወቱ ፣ የቤት እቃዎች ሲነቃነቁ፣ እኔም በተቀመጥኩበት በወትሮ በተለየ ንዝረት ሲሰማኝ ነበር " ብሏል።
ሌላ 12ኛ ፎቅ ላይ የነበረ የቤተሰባችን አባል " ያስፈራ ነበር " ሲል ክስተቱን አስረድቷል።
ከዚህ ባለፈ ንዝረቱ ከተሰባቸው ቦታዎች አንዱ የጅሌ ጥሙጋ አካባቢ ሲሆን የወረዳ አስተዳደር ህንፃ ላይ የሚሰሩ የመንግስት ሰራተኞች በድንጋጤ ከህንጻው መውረዳቸውን ከሰራተኞቹ ለመረዳት ተችሏል።
Photo Credit - Omer Al Faruq
@tikvahethiopa
ከጥቂት ደቂቃዎች በፊት (4:38 ላይ) ተከስቶ የነበረው የመሬት መንቀጥቀጥ ከአዋሽ 36 ኪሎሜትር ርቀት ላይ እንደሆነ የጀርመኑ የጂኦሳይንስ ሪሰርች ማዕከል ገልጿል።
መንቀጥቀጡ በሬክተር ስኬል 4.9 መመዝገቡን አሳውቋል።
በርካታ ሰዎች የዛሬው ከወትሮው የተለየ ነበር ብለዋል።
የመሬት መንቀጥቀጡ የነበረበት አካባቢ ያሉ ወገኖች " አስፈሪ " ሲሉ ገልጸዋል።
ንዝረቱ የተሰማባቸው አካባቢዎች ደግሞ ከወትሮው የተለየ እንደነበር ታውቋል።
ለአብነት አዲስ አበባ ብዙ ሰዎች ህንጻ ላይ የነበሩ ተሰምቷቸው መደናገጣቸውን ገልጸውልናል። ለተወሰኑ ሰከንዶች የቆየ ቢሆንም የህንጻ ንቅናቄ ስሜት ፣ የመንስታወት መርገፍገፍ እንደተመለከቱ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
አንድ የቤተሰባችን አባል " 4ኛ ፎቅ ላይ በተቀመጥኩበት መስታወቱ ፣ የቤት እቃዎች ሲነቃነቁ፣ እኔም በተቀመጥኩበት በወትሮ በተለየ ንዝረት ሲሰማኝ ነበር " ብሏል።
ሌላ 12ኛ ፎቅ ላይ የነበረ የቤተሰባችን አባል " ያስፈራ ነበር " ሲል ክስተቱን አስረድቷል።
ከዚህ ባለፈ ንዝረቱ ከተሰባቸው ቦታዎች አንዱ የጅሌ ጥሙጋ አካባቢ ሲሆን የወረዳ አስተዳደር ህንፃ ላይ የሚሰሩ የመንግስት ሰራተኞች በድንጋጤ ከህንጻው መውረዳቸውን ከሰራተኞቹ ለመረዳት ተችሏል።
Photo Credit - Omer Al Faruq
@tikvahethiopa
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update 🔴 " ዩኒቨርሲቲያችን እንደ ሁሉም የሀገራችን ዩኒቨርሲቲዎች ሁሉ በሴኩላሪዝምና ብዝሃ ሃይማኖትን ተረድቶና አክብሮ የሚሰራ ተቋም ነዉ " - የዲላ ዩኒቨርሲቲ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ➡️ " ወደ ዩኒቨርሲቲዉ ቅጥር ግቢ እንዳንገባ ተደርገናል በዚህም ምክንያት በሁለት መስጊዶች ተጠልለን እንገኛለን " - ሙስሊም ተማሪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የዲላ ዩኒቨርሲቲ ሴት የእስልምና እምነት ተከታይ / ሙስሊም…
#Update
“ በቋሚነት ይሁን ለጊዜው የተብራራ ነገር የለም፡፡ አሁን ግን ተማሪዎቹ ገብተው ትምህርታቸውን መማር ጀምረዋል ” - የዞኑ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት
የዲላ ዩኒቨርሲቲ ሴት ሙስሊም ተማሪዎች በአለባሳቸው ሳቢያ ግቢ እንዳይገቡ በመከልከላቸው፣ ከትምህርት፣ ከካፌና ከማደሪያ ውጪ መሆናቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቅሬታ ማቅረባቸው አይዘነጋም፡፡
ተማሪዎቹ በሰጡት ቃል፣ " 44 ሴት ተማሪዎችን ጥቁር ማስክ አድርጋችሁ 'አናስገባም' ብለው፣ ኒቃብ የለበስን 7 ሴቶችንም ከልክለውን ውጪ አደርን " ነበር ያሉት።
ለቅሬታው ምላሽ የጠየቅነው ዩኒቨርሲቲው፣ እንደ ሁሉም የሀገሪቱ ዩኒቨርሲቲዎች ሁሉ በሴኩላሪዝምና ብዝሃ ሃይማኖትን ተረድቶና አክብሮ የሚሰራ ተቋም እንደሆነና ሴት ሙስሊም ተማሪዎች ሂጃብ እንዳይለብሱ እንዳልተከለከለ ኒቃብ ደግሞ አስቀድሞም በዩኒቨርሲቲ እንደማይደረግ ገልጾ ነበር።
ተማሪዎቹ ግቢ እንዲገቡ ተፈቀዳላቸው ?
ወደ ግቢ ገባችሁ ወይስ አሁንም ከግቢ ውጪ ናችሁ ? ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ ጥያቄ ያቀረበላቸው ተማሪዎቹ፣ " ለጊዜው ከስምምንት ተደርሷል " ሲሉ መልሰዋል።
" በተወካዮቻችን በኩል ኒቃብ፣ ማስክና ሂጃብ ለብሰን መግባት እንደምንችል ተነገረንና ትላንት ገብተናል " ብለዋል።
በስምምነቱ መሰረት ለብሰው እንዲገቡ ከመነገራቸው ውጪ ሌላ የተባሉት ነገር እንደሌለ አስረድተው፣ " ለጊዜው ግን ግቢ ገብተናል " ነው ያሉት፡፡
በደብዳቤ ጭምር በመጠየቅ ጉዳያቸውን ሲከታተል የቆየውን የጌድኦ ዞን እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤትንም ግቢ እንደይገቡ ተከልክለው የነበሩ ተማሪዎች ወደ ግቢ ገብተዋል ? ስንል ጠይቀናል፡፡
የዞኑ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ምን አለ ?
" በቋሚነት ይሁን ለጊዜው የተብራራ ነገር የለም፡፡ ግን ተማሪዎቹ ገብተው ትምህርታቸውን መማር ጀምረዋል፡፡
በዘላቂነቱ ላይ እንደ አገር የሚያዝ አቅጣጫ ይኖራል፡፡ ከዚያ ውጪ ግን ይሄ ነው ተብሎ የተገለጸ ነገር የለም፡፡ ሲጀመር ክልከለውን በተመለከተም በፅሑፍ የተገለጸ የለም፡፡ አሁን ሲፈቀድም በተመሳሳይ ነው፡፡
አገራችን የብዙ ሃይማኖቶችና ብሔሮች መገኛ ስለሆነች ስርዓቶችም ሃይማኖቶችን፣ ብሔር ብሔረሰቦችን ያማካሉ ቢሆኑ፤ ለአንዱ እድል ሰጥቶ ሌላኛውን ያላገለሉ፣ ሃይማኖት ባሉ ነገሮች ምክንያት በሌሎች ቦታዎችም ሁሉን ያማከለ ሆነው ቢወጡ የተሻለ ነው፡፡
የጥብቅ ደን/ብዙ እፅዋቶችን አንድ ላይ ነው በማልማት የሚታወቀውና እንደ አገርም ቅርስ የተያዘለት ማህበረሰብ ያለበት ዩኒቨርሲቲም ስለሆነ ነገሮች ሲከናወኑ በዚያ ቢታሰቡ እጅግ መልካም ይሆናል " ብሏል፡፡
የተደረሰውን ስምምነት በተመለከተ ማብራሪያ ለማግኘት የተደረገው ሙከራ የዩኒቨርሲቲው አካላት ስልክ ለማንሳት ፈቃደኞች ባለመሆናቸው ለጊዜው ሃሳባቸውን ማካተት አልተሳካም፡፡
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
“ በቋሚነት ይሁን ለጊዜው የተብራራ ነገር የለም፡፡ አሁን ግን ተማሪዎቹ ገብተው ትምህርታቸውን መማር ጀምረዋል ” - የዞኑ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት
የዲላ ዩኒቨርሲቲ ሴት ሙስሊም ተማሪዎች በአለባሳቸው ሳቢያ ግቢ እንዳይገቡ በመከልከላቸው፣ ከትምህርት፣ ከካፌና ከማደሪያ ውጪ መሆናቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቅሬታ ማቅረባቸው አይዘነጋም፡፡
ተማሪዎቹ በሰጡት ቃል፣ " 44 ሴት ተማሪዎችን ጥቁር ማስክ አድርጋችሁ 'አናስገባም' ብለው፣ ኒቃብ የለበስን 7 ሴቶችንም ከልክለውን ውጪ አደርን " ነበር ያሉት።
ለቅሬታው ምላሽ የጠየቅነው ዩኒቨርሲቲው፣ እንደ ሁሉም የሀገሪቱ ዩኒቨርሲቲዎች ሁሉ በሴኩላሪዝምና ብዝሃ ሃይማኖትን ተረድቶና አክብሮ የሚሰራ ተቋም እንደሆነና ሴት ሙስሊም ተማሪዎች ሂጃብ እንዳይለብሱ እንዳልተከለከለ ኒቃብ ደግሞ አስቀድሞም በዩኒቨርሲቲ እንደማይደረግ ገልጾ ነበር።
ተማሪዎቹ ግቢ እንዲገቡ ተፈቀዳላቸው ?
ወደ ግቢ ገባችሁ ወይስ አሁንም ከግቢ ውጪ ናችሁ ? ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ ጥያቄ ያቀረበላቸው ተማሪዎቹ፣ " ለጊዜው ከስምምንት ተደርሷል " ሲሉ መልሰዋል።
" በተወካዮቻችን በኩል ኒቃብ፣ ማስክና ሂጃብ ለብሰን መግባት እንደምንችል ተነገረንና ትላንት ገብተናል " ብለዋል።
በስምምነቱ መሰረት ለብሰው እንዲገቡ ከመነገራቸው ውጪ ሌላ የተባሉት ነገር እንደሌለ አስረድተው፣ " ለጊዜው ግን ግቢ ገብተናል " ነው ያሉት፡፡
በደብዳቤ ጭምር በመጠየቅ ጉዳያቸውን ሲከታተል የቆየውን የጌድኦ ዞን እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤትንም ግቢ እንደይገቡ ተከልክለው የነበሩ ተማሪዎች ወደ ግቢ ገብተዋል ? ስንል ጠይቀናል፡፡
የዞኑ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ምን አለ ?
" በቋሚነት ይሁን ለጊዜው የተብራራ ነገር የለም፡፡ ግን ተማሪዎቹ ገብተው ትምህርታቸውን መማር ጀምረዋል፡፡
በዘላቂነቱ ላይ እንደ አገር የሚያዝ አቅጣጫ ይኖራል፡፡ ከዚያ ውጪ ግን ይሄ ነው ተብሎ የተገለጸ ነገር የለም፡፡ ሲጀመር ክልከለውን በተመለከተም በፅሑፍ የተገለጸ የለም፡፡ አሁን ሲፈቀድም በተመሳሳይ ነው፡፡
አገራችን የብዙ ሃይማኖቶችና ብሔሮች መገኛ ስለሆነች ስርዓቶችም ሃይማኖቶችን፣ ብሔር ብሔረሰቦችን ያማካሉ ቢሆኑ፤ ለአንዱ እድል ሰጥቶ ሌላኛውን ያላገለሉ፣ ሃይማኖት ባሉ ነገሮች ምክንያት በሌሎች ቦታዎችም ሁሉን ያማከለ ሆነው ቢወጡ የተሻለ ነው፡፡
የጥብቅ ደን/ብዙ እፅዋቶችን አንድ ላይ ነው በማልማት የሚታወቀውና እንደ አገርም ቅርስ የተያዘለት ማህበረሰብ ያለበት ዩኒቨርሲቲም ስለሆነ ነገሮች ሲከናወኑ በዚያ ቢታሰቡ እጅግ መልካም ይሆናል " ብሏል፡፡
የተደረሰውን ስምምነት በተመለከተ ማብራሪያ ለማግኘት የተደረገው ሙከራ የዩኒቨርሲቲው አካላት ስልክ ለማንሳት ፈቃደኞች ባለመሆናቸው ለጊዜው ሃሳባቸውን ማካተት አልተሳካም፡፡
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
አቶ ብርሃኑ አዴሎ ለኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ኮሚሽነርነት ዕጩ ሆነው ቀረቡ። በቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ መለስ ዜናዊ ዘመነ መንግስት የሚኒስትሮች ካቢኔ ሚኒስትር የነበሩት አቶ ብርሃኑ አዴሎ ገብረማርያም ለኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ኮሚሽነርነት ለመሰየም ዛሬ ጥር 22 ቀን 2017 ዓ/ም ፓርላማ ቀርበዋል። ሌሎች አራት ዕጩዎችም መቅረባቸውን ሪፖርተር ጋዜጣ ዘግቧል። አቶ…
#Update
አቶ ብርሃኑ አዴሎ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ዋና ኮሚሽነር ሆነው ተሹመዋል።
ለሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ኮምሽነር በመሆን የተመረጡት አቶ ብርሃኑ በህዝብ ተወካዮሽ ምክር ቤት ፊት ቀርበው ቃለ መሃላ ፈጽመዋል።
አቶ ብርሃኑ የቀድሞው የምክር ቤት አባል የነበሩ ሲሆን የአዕምሯዊ ንብረት ፅህፈት ቤት ዋና ዳይሬክተር፣ በኢህአዴግ ዘመን የካቢኔ ጉዳዮች ሚኒስትር ሆነው አገልግለዋል።
ላለፉት 10 ዓመታት ደግሞ በጥብቅና በህግ ማማከር ስራ ላይ ቆይተዋል።
የኢሰመኮ ዋና ኮሚሽነር የነበሩት ዳንኤል በቀለ (ዶ/ር) የስራ ዘመናቸውን ማጠናቀቃቸውን ተከትሎ ራኬብ መሰለ በተጠባባቂነት ተቋሙን ሲመሩ ነበር።
@tikvahethiopia
አቶ ብርሃኑ አዴሎ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ዋና ኮሚሽነር ሆነው ተሹመዋል።
ለሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ኮምሽነር በመሆን የተመረጡት አቶ ብርሃኑ በህዝብ ተወካዮሽ ምክር ቤት ፊት ቀርበው ቃለ መሃላ ፈጽመዋል።
አቶ ብርሃኑ የቀድሞው የምክር ቤት አባል የነበሩ ሲሆን የአዕምሯዊ ንብረት ፅህፈት ቤት ዋና ዳይሬክተር፣ በኢህአዴግ ዘመን የካቢኔ ጉዳዮች ሚኒስትር ሆነው አገልግለዋል።
ላለፉት 10 ዓመታት ደግሞ በጥብቅና በህግ ማማከር ስራ ላይ ቆይተዋል።
የኢሰመኮ ዋና ኮሚሽነር የነበሩት ዳንኤል በቀለ (ዶ/ር) የስራ ዘመናቸውን ማጠናቀቃቸውን ተከትሎ ራኬብ መሰለ በተጠባባቂነት ተቋሙን ሲመሩ ነበር።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
በመቐለ ኤፍ ኤም 104.4 ምንድነው የተፈጠረው ? " በመቐለ ኤፍ ኤም ሬድዮ ጣቢያ ላይ የአፈና እና የስራ አመራር የማባረር ሙከራ " መደረጉን ጣቢያው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግሯል። ሙከራው በሊቀ-መንበር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው ህወሓት የመቐለ ከንቲባ እንዲሆኑ በተሾመቱ ረዳኢ በርሀ (ዶ/ር) ያስተባበሩት ነው ተብሏል። ዛሬ ጥር 21/2017 ዓ.ም የተካሄደው የአፈናና አመራር የመቀየር…
#Update
🔴" በ104.4 የመቐለ ኤፍኤም ያጋጠመው ችግር በመግባባት እንዲፈታ አድርጊያለሁ ስልጣን መረከብ የሚፈልግ አካል እና ግለሰብ ህግ እና ስርዓት ያክብር " - የመቐለ ከተማ ፓሊስ
➡" ሬድዮ ጣቢያችን ለሁለት የተሰነጠቁ ቡድኖች መጫወቻ እንዲሆን አንፈቅድም " - የመቐለ FM አመራር
ጥሪ 21 / 2017 ዓ.ም ከረፋዱ 4:00 ሰዓት 5 ታጣቂዎች አስከትሎ የመቐለ ኤፍ ኤም ሬድዮ ጣቢያን ለመቆጣጠረ ሙከራ ያደረገው ሬድዮ ጣብያውን እንዲመራ የመቐለ አስተዳደር " ሹሞኛል " የሚል ግለሰብ እንደሆነ የሬድዮ ጣቢያው አመራሮች ተናግረዋል።
ታጣቂዎች አስከትሎ ሬድዮ ጣብያውን ለመረከብ ሲሞክር የተፃፈለት ደብዳቤ በቦታው ለነበሩ አመራሮች ማሳየት ባለመቻሉ ምክንያት ግርግር እንዲነሳ ምክንያት መሆኑ አመራሮቹ ያብራራሉ።
ዘግይቶ በተደረገው ማጣራት የሹመት ደብዳቤ ማቅረብ ያልቻለውና ሬድዮውን ለመምራት መመደቡ የጠቀሰው ግለሰብ በሊቀ-መንበር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) በሚመራው ህወሓት የከተማዋ ከንቲባ እንዲሆኑ በተሾሙት ረዳኢ በርሀ (ዶ/ር) መመደቡ በቃል እንደጠቀሰላቸው አመራሮቹ ገልጸዋል።
ጉዳዩን ወደ መቐለ ፓሊስ በመውሰድ ጊዚያዊ መፍትሄ ማግኘት መቻላቸው ከምስጋና ጭምር አስታውቀዋል።
የጣቢያው አመራሮች " በደብረፅዮን (ዶ/ር) ህወሓት በተሾመ ከንቲባ ሬድዮ ጣብያውን ለማስተዳደር መመደቡን የሚናገረው ግለሰብ የአገሪቱዋ የሚድያ ህግ በሚጥስ አካሄድ ከአንድ ክፍለ ከተማ ያሰባሰባቸው ታጣቂዎች በማስከተል የአፈና ተግባር ለመፈፀም መመኮሩ የህወሓት በሁለት መሰንጠቅ በክልሉ እያደረሰ ያለው ዘርፈ በዙ ችግር አንዱ ማሳያ ነው " ሲሉ አክለዋል።
" ከ15 ዓመት በላይ ያስቆጠረ እና ከ60 በላይ ሰራተኞች ያሉት የመንግስት የኤፍኤም ሬድዮ ለሁለት የተሰነጠቁ ቡድኖች መጫወቻ አይሆንም " ያሉት አመራሮቹ በአገሪቱ የብሮድካስት ህግ የሚተዳደር ሚድያ መሆኑ በመግለፅ ተመሳሳይ አፈና እንዳይፈፀም በግለሰቡ እና በላከው አካል ላይ ክስ እና አገዳ እንዲጣል እንቅስቃሴ መጀመራቸው አስታውቀዋል።
የመቐለ ፓሊስ በፅሁፍ ባወጣው መግለጫ የአፈና ተግባሩን አውግዞ ፤ ችግሩ በመግባባት መፍታቱን እና ወደ ሃላፊነት መምጣት የሚፈልግ አካል እና ግለሰብ ህግ እና ስርዓት አክብሮ መሆን ይገባዋል ብሏል።
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
🔴" በ104.4 የመቐለ ኤፍኤም ያጋጠመው ችግር በመግባባት እንዲፈታ አድርጊያለሁ ስልጣን መረከብ የሚፈልግ አካል እና ግለሰብ ህግ እና ስርዓት ያክብር " - የመቐለ ከተማ ፓሊስ
➡" ሬድዮ ጣቢያችን ለሁለት የተሰነጠቁ ቡድኖች መጫወቻ እንዲሆን አንፈቅድም " - የመቐለ FM አመራር
ጥሪ 21 / 2017 ዓ.ም ከረፋዱ 4:00 ሰዓት 5 ታጣቂዎች አስከትሎ የመቐለ ኤፍ ኤም ሬድዮ ጣቢያን ለመቆጣጠረ ሙከራ ያደረገው ሬድዮ ጣብያውን እንዲመራ የመቐለ አስተዳደር " ሹሞኛል " የሚል ግለሰብ እንደሆነ የሬድዮ ጣቢያው አመራሮች ተናግረዋል።
ታጣቂዎች አስከትሎ ሬድዮ ጣብያውን ለመረከብ ሲሞክር የተፃፈለት ደብዳቤ በቦታው ለነበሩ አመራሮች ማሳየት ባለመቻሉ ምክንያት ግርግር እንዲነሳ ምክንያት መሆኑ አመራሮቹ ያብራራሉ።
ዘግይቶ በተደረገው ማጣራት የሹመት ደብዳቤ ማቅረብ ያልቻለውና ሬድዮውን ለመምራት መመደቡ የጠቀሰው ግለሰብ በሊቀ-መንበር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) በሚመራው ህወሓት የከተማዋ ከንቲባ እንዲሆኑ በተሾሙት ረዳኢ በርሀ (ዶ/ር) መመደቡ በቃል እንደጠቀሰላቸው አመራሮቹ ገልጸዋል።
ጉዳዩን ወደ መቐለ ፓሊስ በመውሰድ ጊዚያዊ መፍትሄ ማግኘት መቻላቸው ከምስጋና ጭምር አስታውቀዋል።
የጣቢያው አመራሮች " በደብረፅዮን (ዶ/ር) ህወሓት በተሾመ ከንቲባ ሬድዮ ጣብያውን ለማስተዳደር መመደቡን የሚናገረው ግለሰብ የአገሪቱዋ የሚድያ ህግ በሚጥስ አካሄድ ከአንድ ክፍለ ከተማ ያሰባሰባቸው ታጣቂዎች በማስከተል የአፈና ተግባር ለመፈፀም መመኮሩ የህወሓት በሁለት መሰንጠቅ በክልሉ እያደረሰ ያለው ዘርፈ በዙ ችግር አንዱ ማሳያ ነው " ሲሉ አክለዋል።
" ከ15 ዓመት በላይ ያስቆጠረ እና ከ60 በላይ ሰራተኞች ያሉት የመንግስት የኤፍኤም ሬድዮ ለሁለት የተሰነጠቁ ቡድኖች መጫወቻ አይሆንም " ያሉት አመራሮቹ በአገሪቱ የብሮድካስት ህግ የሚተዳደር ሚድያ መሆኑ በመግለፅ ተመሳሳይ አፈና እንዳይፈፀም በግለሰቡ እና በላከው አካል ላይ ክስ እና አገዳ እንዲጣል እንቅስቃሴ መጀመራቸው አስታውቀዋል።
የመቐለ ፓሊስ በፅሁፍ ባወጣው መግለጫ የአፈና ተግባሩን አውግዞ ፤ ችግሩ በመግባባት መፍታቱን እና ወደ ሃላፊነት መምጣት የሚፈልግ አካል እና ግለሰብ ህግ እና ስርዓት አክብሮ መሆን ይገባዋል ብሏል።
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update
" ወደ ቀን መርሃግብር ተቀይረን እንድንማር ከመግባባት ላይ ተደርሷል " - ተማሪዎች
ሰሞኑን የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ በአቅም ማሻሻያ (ሪሚዲያል) መረሃግብር በሳምንቱ የመጨረሻ ቀናት በግል ከፍለዉ መማር ለሚፈልጉ አመልካቾች ባወጣው ማስታወቂያ መሠረት " ተመዝግበንና አስፈላጊውን ክፊያ አጠናቀን ትምህርት በመጀመር ሂደት ዉስጥ ባለንበት ዩኒቨርሲቲው ' አናስተምራችሁም ' ብሎናል " ያሉ ተማሪዎች ቅሬታቸዉን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ማቅረባቸው ይታወሳል።
ዩኒቨርሲቲዉ በበኩሉ ጉዳዩን ከትምህርት ሚንስቴር ጋር በመነጋገር ለመፍታት እየተንቀሳቀሰ መሆኑን ገልፆልን ነበር።
ቅሬታ አቅርበዉ የነበሩ ተማሪዎችና ወላጆች በዛሬው ዕለት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ እንዳስታወቁት ዩኒቨርሲቲው የትምህርት መርሃግብሩን ከእረፍት ቀናት ወደ መደበኛ መርሃግብር በማዘዋወር ተማሪዎቹን ለማስተማር መወሰኑን አረጋግጠዋል።
" ዛሬ ተጠርተን ዉል ተፈራርመናል " ያሉት የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የአቅም ማሻሻያ (ሪሚዲያል) አመልካቾች " በዉሉ ላይ የተቀመጡ ጉዳዮች የመረሃግብሩ ከዕረፍት ቀናት (weekend) ወደ መደበኛ መቀየር ፣ አመልካቾች በግል ከፍለዉ የሚማሩ ስለመሆናቸው የሚገልፅ፣ ስለ ክፍያ አፈፃፀምና በዩኒቨርሲቲው እና በተማሪዎቹ መካከል ስለሚኖረዉ መብትና ግዴታ የሚደነግግ ነው " ሲሉ ገልጸዋል።
የተማሪ ወላጆች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል " ከከፍተኛ ጭንቅ ነዉ የገላገላችሁን፣ ምን እንደምናደርግ ጨንቆን ነበር ትምህርት ሚንስቴር እና የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲም ላሳያችሁን በጎ ምላሽ እናመሰግናለን " ብለዋል።
የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ በግል ከፍሎ የአቅም ማሻሻያ (ሪሚዲያል) ለሚወስዱ ተማሪዎች ያዘጋጀዉን ዉል በዚህ መረጃ ላይ ያካተትን ሲሆን የዩኒቨርሲቲዉ አካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዚዳንት ዶ/ር አክበር ጩፎ ስለጉዳዩ ትክክለኛነት ከመግለፅ ባለፈ ተጨማሪ መረጃ ከመስጠት ተቆጥበዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyHW
@tikvahethiopia
" ወደ ቀን መርሃግብር ተቀይረን እንድንማር ከመግባባት ላይ ተደርሷል " - ተማሪዎች
ሰሞኑን የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ በአቅም ማሻሻያ (ሪሚዲያል) መረሃግብር በሳምንቱ የመጨረሻ ቀናት በግል ከፍለዉ መማር ለሚፈልጉ አመልካቾች ባወጣው ማስታወቂያ መሠረት " ተመዝግበንና አስፈላጊውን ክፊያ አጠናቀን ትምህርት በመጀመር ሂደት ዉስጥ ባለንበት ዩኒቨርሲቲው ' አናስተምራችሁም ' ብሎናል " ያሉ ተማሪዎች ቅሬታቸዉን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ማቅረባቸው ይታወሳል።
ዩኒቨርሲቲዉ በበኩሉ ጉዳዩን ከትምህርት ሚንስቴር ጋር በመነጋገር ለመፍታት እየተንቀሳቀሰ መሆኑን ገልፆልን ነበር።
ቅሬታ አቅርበዉ የነበሩ ተማሪዎችና ወላጆች በዛሬው ዕለት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ እንዳስታወቁት ዩኒቨርሲቲው የትምህርት መርሃግብሩን ከእረፍት ቀናት ወደ መደበኛ መርሃግብር በማዘዋወር ተማሪዎቹን ለማስተማር መወሰኑን አረጋግጠዋል።
" ዛሬ ተጠርተን ዉል ተፈራርመናል " ያሉት የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የአቅም ማሻሻያ (ሪሚዲያል) አመልካቾች " በዉሉ ላይ የተቀመጡ ጉዳዮች የመረሃግብሩ ከዕረፍት ቀናት (weekend) ወደ መደበኛ መቀየር ፣ አመልካቾች በግል ከፍለዉ የሚማሩ ስለመሆናቸው የሚገልፅ፣ ስለ ክፍያ አፈፃፀምና በዩኒቨርሲቲው እና በተማሪዎቹ መካከል ስለሚኖረዉ መብትና ግዴታ የሚደነግግ ነው " ሲሉ ገልጸዋል።
የተማሪ ወላጆች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል " ከከፍተኛ ጭንቅ ነዉ የገላገላችሁን፣ ምን እንደምናደርግ ጨንቆን ነበር ትምህርት ሚንስቴር እና የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲም ላሳያችሁን በጎ ምላሽ እናመሰግናለን " ብለዋል።
የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ በግል ከፍሎ የአቅም ማሻሻያ (ሪሚዲያል) ለሚወስዱ ተማሪዎች ያዘጋጀዉን ዉል በዚህ መረጃ ላይ ያካተትን ሲሆን የዩኒቨርሲቲዉ አካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዚዳንት ዶ/ር አክበር ጩፎ ስለጉዳዩ ትክክለኛነት ከመግለፅ ባለፈ ተጨማሪ መረጃ ከመስጠት ተቆጥበዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyHW
@tikvahethiopia