TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.2K photos
1.5K videos
211 files
4.1K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#ኤር_ኤክስፕረስ_አፍሪካ ኤር ኤክስፕረስ አፍሪካ የግል የአውሮፕላን አየር ትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጥ ተቋም ሆኖ በኢትዮጵያ ተመዘገበ። የኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን ፤ ኤር ኤክስፕረስ አፍሪካ የግል የአውሮፕላን አየር ትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጥ ተቋም ሆኖ መመዝገቡን አሳውቋል። ተቋሙ ምዝገባውን በስኬት ያጠናቀቀው አለም አቀፍ አሰራርን ተከትሎ የተቀመጠውንና በኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን…
#ETHIOPIA

በሀገራችን ኢትዮጵያ 13ኛው የግል የአውሮፕላን አየር ትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጥ ተቋም ተመዝግቧል።

13ኛው የግል የአውሮፕላን አየር ትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጥ ተቋም ሆኖ በኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን የተመዘገበው " ጎልድ ስታር አቪዬሽን " ነው።

ተቋሙ ምዝገባውን በስኬት ያጠናቀቀው ዓለም አቀፍ አሰራርን ተከትሎ የተቀመጠውንና በኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን የሚተገበሩትን 5 ደረጃዎችን (five phases) በስኬት አጠናቆ በመገኘቱ ነው።

በውስጣቸው በርካታ ተግባራትን የያዙት አምስት ስታንዳርዶች pre-application, formal application, Document evaluation and Inspection and finally Certification የሚባሉ ሲሆን ጎልድ ስታር ትላንት በባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ዋና ዳይሬክተር የተፈረመበትን ሰርትፊኬት በይፋ ተቀብሏል፡፡

በአሁን ሰዓት በሀገራችን " ጎልድ ስታር አቪዬሽን " ን ጨምሮ በኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን ተመዝግበው አገልግሎት እየሰጡ የሚገኙ የአውሮፕላን አየር ትራንስፖርት ተቋማት 13 ደርሰዋል፡፡

" ጎልድ ስታር አቪዬሽን " የእውቁ ባለሀብት #ወርቁ_አይተነው ድርጅት መሆኑን ከባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ያገኘነው መረጃ ያሳያል።

@tikvahethiopia