TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.8K photos
1.61K videos
216 files
4.37K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
"የመከላከያ ሰራዊቱን #ማገት የሚለው አስቸጋሪ ነው፡፡ #መከላከያን ማንም ሊያግተው አይችልም፡፡ አማርኛው ቢቀየር ጥሩ ነው። ሰራዊቱን #የትግራይ_ህዝብ አያገትም፡፡ ነገር ግን #ስጋት እየፈጠረ መኖር የለመደ አካል አለ፡፡ በጣም ጥቂት ነው፡፡ ህዝቡን ሽፋን አድርጎ ትርምስ ለመፍጠር የሚሞክር ኃይል አለ፡፡ ጥቂቶች ናቸው፡፡ እርግጠኛ ነኝ #ይጋለጣሉ፡፡ የትግራይ ህዝብም #ቢዘገይም ይገባዋል፡፡ እንዲጋለጡና ህዝቡም እንዲያውቃቸው እናደርጋለን፡፡ ይህ እስኪሆን ግን ከህዝቡ ጋር #የሚያጣላ ነገር አናደርግም፡፡ ህዝብ ቅር ከሚለው እኛ ቅር ቢለን ይሻለናል፡፡ በነገራችን ላይ ይህ ነገር ከክልሉ እውቅና ውጭ ነው፡፡ ክልሉ ወስኖ የተደረገ ነገር አይደለም፡፡ የክልሉ ፍላጎትም አይደለም፡፡"-የጦር ኃይሎች ምክትል ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ጀነራል ብርሃኑ ጁላ ዛሬ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የተናገሩት፤

@tsegabwolde @tikvqhethiopia
#የትግራይ_ህዝብ_ፍቅር_ነው!

"ወደ ትግራይ እንዳትሄድ ብለው አስጠንቅቀውኝ ነበር! የመጣነው ከአዳማ፣ ኦሮሚያ ነው። ልጆቻችን ለማስመረቅ ወደ መቐለ እንሄዳለን ብለን ስንናገር #ይቅርባችሁ ተብለናል። እንሄዳለን ብለን ስንወስንም በሉ አፋን ኦሮሞ እንዳትናገሩ ብለው መክረው ስለ ላኩን አሁን ግን የቴሌቪኑ የስርጭት ቋንቋ አማርኛ ቢሆንም ደስታዬ እና መልእክቴን በአፋን ኦሮሞ ነው ማስተላልፈው!" ብለው በኣፋን ኦሮሞ ደስታቸውን መልዕክታቸውን ተናገሩ። (ከትግራይ ህዝብ ጋር 'በ በሬ ወለደ ውሸታቸው ሊለያዩን የሚያስቡ ሰዎች ጤነኛ ናቸውን?) በማለት በአፍ መፍቻ ቋንቋቸው በአፋን ኦሮሞ ሐሳባቸውን ገለፁ።

የትግራይ ቴሌቪዥን ጋዜጠኛም ጎበዝ ነበር እንደ እሳቸው በአፋን ኦሮሞ ጥያቄውን አስከተለ (አንድ ቋንቋ የሚናገር አንድ ሰው ነው:ሁለት የሚናገር ሁለት ሰው ነው ይባል የለ?) ጋዜጠኛው ብዙ ሰው ነበረ፡፡ እንግዳውም ቀጥለው... በአማርኛ ቋንቋ የትግራይ ህዝብ በሄዱበት መስጊድ፣ ምግብ ቤትና መኝታ ቤት በታላቅ ክብር እንዳስተናገዷቸው ገልፀው አመሰገኑ፡፡"

ፍቅር፤ ሰላም፤ አንድነት!
@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ጄኔራል ታደሰ ወረደ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንትነትን ሲረከቡ የፈረሙት " የትግራይ ክልል አካታች ጊዜያዊ አስተዳደር የተልዕኮ አፈጻጸም የቃል ኪዳን ሰነድ " ምን ይላል ? 1. የተፈናቀሉ ዜጎችን ወደ ቀያቸው የመመለስ ሂደት፣ በጅምር ያለው እንዲጠናቀቅ እና በቀሪ አካባቢዎችም #በፍጥነት እንዲተገበር ማድረግ፤ 2. በፕሪቶሪያ ስምምነት መሠረት ትጥቅ የመፍታት እና የቀድሞ ታጣቂዎችን መልሶ…
" የተሰጠኝ ኃላፊነት ከባድ የሆነ ፈተና ነው ፤ ጥሩ ከተሰራ ግን እድል ነው " - ጄነራል ታደሰ ወረደ

አዲሱ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ጄነራል ታደሰ ወረደ አስተዳደራቸው የካቢኔ መዋቅር ማስተካከያ እንደሚያደረግ ገልጸዋል።

ጄነራል ታደሰ የተሰጣቸው ኃላፊነት  ከባድ ፈተና እንደሆነ ተናግረዋል። " የምትመኘው ነገር አይደለም "  ያሉት ፕሬዝዳንቱ " ጥሩ ከተሰራ ግን እድል ነው " ብለዋል።

"ፈተና" ያሏቸውን እንደኖሩባቸውና እንደሚያውቋቸውም ጠቁመዋል።

ባለፉት ጊዜ ያልተሰሩት ስራዎች ከፕሪቶሪያ ስምምነት ጋር የተያያዙ ብቻ እንዳልሆኑ ጠቁመው " በራሳችን በውስጣች የተፈጠሩ ከፍተኛ የፀጥታ ፣ የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚ ቀውሶች አሉ " ብለዋል።

እነዚህን በርካታ ችግሮች ለመቅረፍ ትግራይ ማዕከላዊ ስልጣን አጥታ ነበር አሁን ግን ማዕከሉን በማጠናከር ይሰራል ሲሉ ገልጸዋል።

የሰላም ስራዎች ላይ ፣ የፕሪቶሪያ ስምምነት መተግበር ላይ፣ የህዝቡ ጥያቄን መፍታት ላይ ጠንክረው እንደሚሰሩ የተናገሩት ጄነራል " አሁን  ያለው ውጥረት ረግቦ ሁሉም የፖለቲካ አካሄድ ለውጥ የሚመጣበት ፤ የወጣቶችም የለውጥ ፍላጎት የሚሳካበት ሁኔታ ይፈጠራል " ብለው እንደሚገምቱ ተናግረዋል።

በሳቸው አስተዳደር የካቢኔ ማስተካከያ እንደሚኖርም ይፋ አድርገዋል።

በፕሬዜዳንትነት ጊዜያቸው ዋናው #የትግራይ_ህዝብ ድጋፍ እንደማይለያቸው ፤ የፌዴራሉም መንግሥት እንዲሁም የዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ድጋፍም እንዲሁ እንደማይለያቸው እምነታቸው ገልጸዋል።

" ትልቁ ነገር ደግሞ አቶ ጌታቸው ረዳ የስራ ለውጥ ቢያደርጉም ክልሉን ያውቁታል ያላቸውን እና በቀጣይ የሚኖራቸውን ሚና በደምብ እገነዘባለሁና የእሳቸው ድጋፍም እንደማይለየኛ ተስፋ አደርጋለሁ " ብለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
480🕊180🤔79😡66👏51😭29🙏16💔15😢14😱12🥰6