TIKVAH-ETHIOPIA
#MoE • 12,787 ተማሪዎች ፈተና አንፈተንም ብለው ጥለው ወጥተዋል። • በደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ አንድ ተማሪ ህይወቱ አልፏል። ትምህርት ሚኒስቴር የ12ኛ ክፍል የ2014 ዓ.ም የመጀመሪያ ዙር የማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ፈተና መጠናቀቁን ገልጿል። ሚኒስቴሩ በሰጠው መግለጫ ለፈተና ከተቀመጡ 595 ሺህ ተፈታኞች ውስጥ 586 ሽህ 541 ተፈታኞች ፈተናውን ወስደዋል ብሏል። " ፈተናው በተጀመረበት…
#MoE
የትምህርት ሚኒስቴር ፤ በ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና የመጀመሪያ ዙር የማህበራዊ ሳይንስ ፈተና ከተሳተፈው ሰው ብዛት፣ ከተፈታኙ ብዛትና በዚህ መልኩ ፈተና ሲሰጥ የመጀመርያ ከመሆኑ አንጻር የሚጠበቅ ቢሆንም አጋጥመዋል ያላቸው ቁልፍ ችግሮች ፦
- በቂ ኦሬንቴሽን ባለማግኘት ወይም በማወቅም ጭምር የተከለከሉ ቁሶችን ይዘው የመጡና ይዘው የተገኙ ተፈታኞች መኖራቸው፤
- ነፍሰጡርና መጫት ተፈታኞች በሌላ ዙር እንደሚፈተኑ አስቀድሞ ቢገለፅም በዚህኛው ዙር ለፈተና መምጣታቸው፣
- በፈተና አዳራሽ #በጋራ_ካልሰራን ብለው ከፈተና አስፈጻሚዎች ጋር ግብ ግብ የፈጠሩ ተፈታኞች ማጋጠማቸው፤
- ከተሰጣቸው መመሪያና ከፈታኝ የማይጠበቅ ተግባር ላይ የተሳተፉ የፈተና አስፈፃሚዎች ማጋጠማቸው፤
- በትራንስፖርት እጥረት ምክንያት ዘግይተውና አምሽተው በዩኒቨርስቲዎች የደረሱ መኖራቸው፤
- ተማሪዎች ስልክ እንደሌላቸውና ፈተና ቢወጣ እንኳ እንደማያገኙ እየታወቀ ፈተና እንለጥፋለን የሚሉ " የቴሌግራም ገፆች " ማጋጠማቸውና ፈተና ካለቀ ወይም በመሰጠት ላይ እያለ አንድም ሁለትም ገፅ መለጠፋቸው፤
(የትምህርት ሚኒስቴር ሙሉ መግለጫ ከላይ ተያይዟል)
@tikvahethiopia
የትምህርት ሚኒስቴር ፤ በ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና የመጀመሪያ ዙር የማህበራዊ ሳይንስ ፈተና ከተሳተፈው ሰው ብዛት፣ ከተፈታኙ ብዛትና በዚህ መልኩ ፈተና ሲሰጥ የመጀመርያ ከመሆኑ አንጻር የሚጠበቅ ቢሆንም አጋጥመዋል ያላቸው ቁልፍ ችግሮች ፦
- በቂ ኦሬንቴሽን ባለማግኘት ወይም በማወቅም ጭምር የተከለከሉ ቁሶችን ይዘው የመጡና ይዘው የተገኙ ተፈታኞች መኖራቸው፤
- ነፍሰጡርና መጫት ተፈታኞች በሌላ ዙር እንደሚፈተኑ አስቀድሞ ቢገለፅም በዚህኛው ዙር ለፈተና መምጣታቸው፣
- በፈተና አዳራሽ #በጋራ_ካልሰራን ብለው ከፈተና አስፈጻሚዎች ጋር ግብ ግብ የፈጠሩ ተፈታኞች ማጋጠማቸው፤
- ከተሰጣቸው መመሪያና ከፈታኝ የማይጠበቅ ተግባር ላይ የተሳተፉ የፈተና አስፈፃሚዎች ማጋጠማቸው፤
- በትራንስፖርት እጥረት ምክንያት ዘግይተውና አምሽተው በዩኒቨርስቲዎች የደረሱ መኖራቸው፤
- ተማሪዎች ስልክ እንደሌላቸውና ፈተና ቢወጣ እንኳ እንደማያገኙ እየታወቀ ፈተና እንለጥፋለን የሚሉ " የቴሌግራም ገፆች " ማጋጠማቸውና ፈተና ካለቀ ወይም በመሰጠት ላይ እያለ አንድም ሁለትም ገፅ መለጠፋቸው፤
(የትምህርት ሚኒስቴር ሙሉ መግለጫ ከላይ ተያይዟል)
@tikvahethiopia