TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
58.9K photos
1.5K videos
211 files
4.07K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#ትምራን ትምራን ከኢትዮጵያ ሴቶች ማህበራት ቅንጅት (NEWA) ጋር በመተባበር ነገ ሀሙስ " የሴቶች የሰላም የእግር ጉዞ " ይካሂዳሉ። በዚህም ወቅት ለመጪው አዲስ አመት የሰላም ምኞቶ የሚተላለፍበት እንዲሁም ግጭቱ እንዲቆምና ሴቶች በሰላም ግንባታ ተግባራት ውስጥ እንዲሳተፋ የሚጠየቅበት መርሀግብር ይኖረናል ተብሏል። የእግር ጉዞው ከጠዋቱ 1 ሰዓት ላይ በካዛንቺ ሴቶች አደባባይ ጀምሮ መስቀል አደባባይ…
ፎቶ ፦ ትምራን ከኢትዮጵያ ሴቶች ማህበራት ቅንጅት (NEWA) ጋር በመተባበር ያዘጋጁት " የሴቶች የሰላም የእግር ጉዞ " ዛሬ ሀሙስ በአዲስ አበባ ተካሂዷል።

የእግር ጉዞ ተሳያፊዎቹ ለመጪው አዲስ አመት የሰላም ምኞታቸውን ያስተላለፉ ሲሆን በሀገራችን ግጭቱ እንዲቆምና ሴቶች በሰላም ግንባታ ተግባራት ውስጥ እንዲሳተፋ ጠይቀዋል።

በዕለቱ ከተላለፉ መልዕክቶች መካከል ፦

🪧 #በቃን መደፈር !
🪧 የሀገር ሰላም የሴቶችም ሰላም እና ደህንነት ነው !
🪧 የሴቶች ሰውነት የጦር ሜዳ አይደለም !
🪧 ጦርነት የሞት፣ የረሃብ፣ የስደት እና የጥፋት መንስኤ እንጂ የልማት መሳሪያ አይደለም !
🪧 በጦርነት የትኛውም አይነት አለመግባባት መፍትሄ አግኝቶ አያውቅም። እኛ የኢትዮጵያ ሴቶች ሰላማዊ የግጭት መፍቻ ዘዴዎችን እንደግፋለን የሚሉት ይገኙበታል።

የፎቶ ባለቤት ፦ የኢትዮጵያ ሴት የሰብዓዊ መብቶች ተሟጋቾች ጥምረት

@tikvahethiopia