TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.8K photos
1.61K videos
216 files
4.36K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ወጣት ታምራት...

ኢ/ር #ታከለ_ኡማ እና ኢ/ር #እንዳወቅ_አብቴ ከሶስት አመት በፊት ሜክሲኮ አከባቢ በተፈጠረ ከባድ የእሳት አደጋ ከተዘጋ ቤት ውስጥ ተራ በተራ እየተመላለሰ 12 ሰዎችን ከእሳት የታደገውን ወጣት ታምራት ጎሹ በስራ ቦታው ተገኝተው በመጎብኘት ላደረገው #ሰብዓዊነት ምስጋና ችረውታል።

ወጣቱ በዚህ ምግባሩ ሙሉ በሙሉ ሰውነቱ በእሳት ተቃጥሎ ሁለት አመት አልጋ ላይ ያሳለፈ ሲሆን በአሁኑ ሰዓትም የ8 ወር ነብሰጡር ከሆነችው ባለቤቱ ጋር በሚሰሩበት ምግብ ቤት ውስጥ እየኖሩ እንደሚገኙ ኢ/ር ታከለ በጉብኝታቸው ተመልክተዋል። ኢ/ር ታከለ ኡማ ወጣት ታምራት ጎሹ ላሳየው ሰብዓዊነት ያላቸውን አድናቆት ገልፀው ቀሪ ህይወቱን የሚመራበት የመኖሪያ ቤት እንደሚያገኝ ቃል ገብተዋል።

Via MayorofficeAA
@tsegabwolde @tikvahethiopia