#update የህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ -ህወሓት ተወካይ አቶ #ጌታቸው_ረዳ በብአዴን 12ኛ ድርጅታዊ ጉባኤ መክፈቻ ላይ ካስተላለፉት የአጋርነት መልዕክት የተወሰዱ አንኳር ነጥቦች፦
o ጉባዔው የተጀመረውን የለውጥ ሂደት ዳር ለማድረስ ትልቅ ሚና አለው ብሎ ህወሓት ያምናል፡፡
o ሀገራችን ካለችበት አጓጊ ተስፋና ስጋት አሸንፋ የምትወጣበትን ውሳኔዎችን ብአዴን እንደሚያሳልፍ ተስፋ እናደርጋለን፡፡
o ህዝቡን ተጠቃሚ ለማድረግ ብዙ ተጉዘናል፣ አሁንም በተሻለ መልኩ ለመስራት የሚያስችል ቁመና እንደሚፈጠር እንጠብቃለን፡፡
o አንዳንዶቻችን በሂደት ህዝቡን ከመጥቀም ይልቅ ራሳችንን መጥቀም እያሸነፈን ሄዶ የህዝቡን ጥያቄዎች መመለስ ተስኖናል፡፡
o የበደልነውን ህዝብ መካስ ይኖርብናል፡፡
o የአማራ ህዝቦች ክቡር መስዋዕትነት የከፈሉ ኩሩ ህዝቦች ናቸው፡፡
o ከሌሎች ህዝቦች ጋር የሚጋጭ ፍላጎት እንደሌለውም እናምናለን፡፡
o በህዝቦቻችን መካከል #መጠራጠር እንዳንፈጥር መጠንቀቅ ይኖርብናል፡፡
o አልፎ አልፎ በአማራና በትግራይ ህዝቦች መካከል ልዩነት ለመፍጠር የሚደረገው ሙከራ #ሊወገዝ ይገባዋል፡፡
o ቁርኝቱን ይበልጥ ለማጠናከር ህወሓት ከብአዴንና ከአማራ ህዝብ ጋር አብሮ ለመስራት ዝግጁ ነው፡፡
o ብአዴን ከ12ኛው ድርጅታዊ ጉባኤ የክልሉን ህዝብ የተጠቃነት ጥያቄ ጭምር የሚያረጋግጡና ለውጡን የሚያጠናክሩ ውሳኔዎችን እንደሚያሳልፍ እና ህወሓትም ከብአዴን ጋር በጋር እንደሚሰራ አረጋግጣለሁ፡፡
ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን
@tsegabwolde @tikvahethiopia
o ጉባዔው የተጀመረውን የለውጥ ሂደት ዳር ለማድረስ ትልቅ ሚና አለው ብሎ ህወሓት ያምናል፡፡
o ሀገራችን ካለችበት አጓጊ ተስፋና ስጋት አሸንፋ የምትወጣበትን ውሳኔዎችን ብአዴን እንደሚያሳልፍ ተስፋ እናደርጋለን፡፡
o ህዝቡን ተጠቃሚ ለማድረግ ብዙ ተጉዘናል፣ አሁንም በተሻለ መልኩ ለመስራት የሚያስችል ቁመና እንደሚፈጠር እንጠብቃለን፡፡
o አንዳንዶቻችን በሂደት ህዝቡን ከመጥቀም ይልቅ ራሳችንን መጥቀም እያሸነፈን ሄዶ የህዝቡን ጥያቄዎች መመለስ ተስኖናል፡፡
o የበደልነውን ህዝብ መካስ ይኖርብናል፡፡
o የአማራ ህዝቦች ክቡር መስዋዕትነት የከፈሉ ኩሩ ህዝቦች ናቸው፡፡
o ከሌሎች ህዝቦች ጋር የሚጋጭ ፍላጎት እንደሌለውም እናምናለን፡፡
o በህዝቦቻችን መካከል #መጠራጠር እንዳንፈጥር መጠንቀቅ ይኖርብናል፡፡
o አልፎ አልፎ በአማራና በትግራይ ህዝቦች መካከል ልዩነት ለመፍጠር የሚደረገው ሙከራ #ሊወገዝ ይገባዋል፡፡
o ቁርኝቱን ይበልጥ ለማጠናከር ህወሓት ከብአዴንና ከአማራ ህዝብ ጋር አብሮ ለመስራት ዝግጁ ነው፡፡
o ብአዴን ከ12ኛው ድርጅታዊ ጉባኤ የክልሉን ህዝብ የተጠቃነት ጥያቄ ጭምር የሚያረጋግጡና ለውጡን የሚያጠናክሩ ውሳኔዎችን እንደሚያሳልፍ እና ህወሓትም ከብአዴን ጋር በጋር እንደሚሰራ አረጋግጣለሁ፡፡
ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን
@tsegabwolde @tikvahethiopia