TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.3K photos
1.51K videos
212 files
4.11K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update የህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ -ህወሓት ተወካይ አቶ #ጌታቸው_ረዳ በብአዴን 12ኛ ድርጅታዊ ጉባኤ መክፈቻ ላይ ካስተላለፉት የአጋርነት መልዕክት የተወሰዱ አንኳር ነጥቦች፦

o ጉባዔው የተጀመረውን የለውጥ ሂደት ዳር ለማድረስ ትልቅ ሚና አለው ብሎ ህወሓት ያምናል፡፡

o ሀገራችን ካለችበት አጓጊ ተስፋና ስጋት አሸንፋ የምትወጣበትን ውሳኔዎችን ብአዴን እንደሚያሳልፍ ተስፋ እናደርጋለን፡፡

o ህዝቡን ተጠቃሚ ለማድረግ ብዙ ተጉዘናል፣ አሁንም በተሻለ መልኩ ለመስራት የሚያስችል ቁመና እንደሚፈጠር እንጠብቃለን፡፡

o አንዳንዶቻችን በሂደት ህዝቡን ከመጥቀም ይልቅ ራሳችንን መጥቀም እያሸነፈን ሄዶ የህዝቡን ጥያቄዎች መመለስ ተስኖናል፡፡

o የበደልነውን ህዝብ መካስ ይኖርብናል፡፡
o የአማራ ህዝቦች ክቡር መስዋዕትነት የከፈሉ ኩሩ ህዝቦች ናቸው፡፡

o ከሌሎች ህዝቦች ጋር የሚጋጭ ፍላጎት እንደሌለውም እናምናለን፡፡

o በህዝቦቻችን መካከል #መጠራጠር እንዳንፈጥር መጠንቀቅ ይኖርብናል፡፡

o አልፎ አልፎ በአማራና በትግራይ ህዝቦች መካከል ልዩነት ለመፍጠር የሚደረገው ሙከራ #ሊወገዝ ይገባዋል፡፡

o ቁርኝቱን ይበልጥ ለማጠናከር ህወሓት ከብአዴንና ከአማራ ህዝብ ጋር አብሮ ለመስራት ዝግጁ ነው፡፡

o ብአዴን ከ12ኛው ድርጅታዊ ጉባኤ የክልሉን ህዝብ የተጠቃነት ጥያቄ ጭምር የሚያረጋግጡና ለውጡን የሚያጠናክሩ ውሳኔዎችን እንደሚያሳልፍ እና ህወሓትም ከብአዴን ጋር በጋር እንደሚሰራ አረጋግጣለሁ፡፡

ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን
@tsegabwolde @tikvahethiopia