TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.7K photos
1.61K videos
216 files
4.36K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ነዳጅ

በኢትዮጵያ ያሉ የነዳጅ ኩባንያዎች፣ ነዳጅ አመላላሽ ቦቴ ተሽከርካሪዎቻቸው ከጂቡቲ ነዳጅ ሲቀዱ ከዚህ በፊት የጫኑት ነዳጅ መዳረሻው ደርሶ ስለመራገፉ የርክክብ ሰነድ እንዲያመጡ ካልሆነ ግን ከነገ ከሐሙስ ሐምሌ 28 ቀን 2014 ዓ.ም. ጀምሮ ነዳጅ መጫን እንዳይፈቀድላቸው የነዳጅና ኢነርጂ ባለሥልጣን ትዕዛዝ ማስተላለፉን ሪፖርተር ጋዜጣ ዘግቧል።

ከዚህ በተጨማፊ ቦቴዎቹ ነዳጅ ቀድተው ሲወጡ ስለመዳረሻቸው ሙሉ መረጃ ለጥፈው መውጣት እንዳለባቸው በባለሥልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ሰሃረላ አብዱላሂ ሐምሌ 21 ቀን 2014 ዓ.ም. ተፈርሞ የወጣውና ለኢትዮጵያ ነዳጅ አቅራቢ ድርጅት የተጻፈ ደብዳቤ ያሳያል።

የኩባንያዎቹ ቦቴዎች የርክክብ ሰነድ የሚያገኙት በየማደያው አካባቢ ካሉ የወረዳ ንግድ ቢሮዎች ሲሆን፣ ይህም የሚሆነው የንግድ ቢሮዎች ባለሙያዎች ቦቴዎቹ ነዳጁን ለማደያዎች ሲያስረክቡ እዚያው ማረጋገጫቸውን በመስጠት ነው።

ስለቀጣይ መዳረሻዎቻቸው ሙሉ መረጃ በመስጠትና በመለጠፍ ይቀዳሉ ተብሏል።

የነዳጅ አቅራቢ ድርጅት በመመርያው ይህን እንዲያስቀድም የታዘዘ ሲሆን የነዳጅ ኩባንያዎቹ ይህን አውቀው የማይታዘዙ ከሆነ መጫን እንደማይችሉ ማወቅ አለባቸው ተብሏል።

ባለስልጣን መ/ቤቱ " ይህን ካላደረጉ ዳግም ነዳጅ ለመጫንና ሥምሪት ለማድረግ አይችሉም " ብሏል።

የነዳጅ አቅራቢ ድርጅት ተግባራዊ እንዲያደርግ ያዘዘው ደብዳቤ ዓላማ፣ ባለፈው ወር የወጣውን የነዳጅ ውጤቶች የሥርጭት፣ ርክክብና ሽያጭ አፈጻጻም መመርያ ተግባራዊ ለማድረግ ታስቦ ሲሆን በዚህም #ከጂቡቲ እስከ #ማደያ ድረስ ይፈጸማል የሚባለውን የኮትሮባንድ ንግድ ለማስቀረት ከፍተኛ አስተዋጾኦ እንደሚኖረው ታምኗል፡፡

ያንብቡ : https://telegra.ph/Reporter-08-03-2

Credit : ሪፖርተር

@tikvahethiopia
👍696👏34👎2114🥰7🙏7😢5