TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.2K photos
1.5K videos
211 files
4.1K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
በኮንሶ ያለው የምግብ እጥረት !

በደቡብ ክልል ውስጥ በሚገኘው ኮንሶ ዞን በተከሰተ የምግብ እጥረት ሳቢያ 13 ሕጻናት መሞታቸውን ተሰምቷል።

በኮንሶ ዞን ባለፉት ሦስት ተከታታይ ዓመታት የሚጥለው ዝናብ ወቅቱን የጠበቀ ባለመሆኑ እንዲሁም በተከታታይ በነበሩ ግጭቶች የተነሳ ለከፋ ረሃብ የተጋለጡ ሰዎች ቁጥር ጨምሯል።

አቶ ተስፋዬ ጫሬ የኮንሶ ዞን ዋና የመንግሥት ተጠሪ ለቢቢሲ በሰጡት ቃል ፤ " ከሐምሌ 01/2014 ዓ.ም. ጀምሮ ባሉት ስድስት ወራት በዞኑ አስቸኳይ የምግብ እርዳታ የሚያስፈልጋቸው ሰዎች ቁጥር 190 ሺህ 825 ይሆናል። " ብለዋል።

ከእነዚህ መካከል 122 ሺህ 735 በዝናብ እጥረት ምክንያት ለችግር የተጋለጡ ሲሆኑ፣ በግጭት ምክንያት ተፈናቅለው እርዳታ የሚጠብቁ ደግሞ 68,087 መሆናቸውን አመልከተዋል።

በካራት ሆስፒታል ሄድ ነርስ የሆነው እና በምግብ እጥረት የተጎዱ ሕጻናት ክፍል የሚሰራው ሰምበቶ በሪሻ እንደተናገረው ወደ ሆስፒታላቸው በምግብ እጥረት ተጎድተው የሚመጡ ሕጻናት ቁጥር በየጊዜው እየጨመረ ነው።

ከዚህ ቀደም በወር እስከ 40 ሕጻናት በምግብ እጥረት ተጎድተው ይመጡ እንደነበር አስታውሶ፣ በአሁን ሰዓት ግን ይህ ቁጥር በእጥፍ አድጎ እስከ 80 ሕጻናት በምግብ እጥረት ተጎድተው እንደሚመጡ ገልጿል።

ወደ ካራት ሆስፒታል የሚመጡ አብዛኞቹ ሕጻናት ከገጠር ቀበሌዎች መሆኑን ያስታወሰው አቶ ሰምበቶ፣ በግጭት ምክንያት ከሰገን ዙሪያ የተፈናቀሉ እንደሚገኙበትም ገልጿል።

ያንብቡ : https://www.google.com/amp/s/www.bbc.co.uk/amharic/articles/cyj71e3jd0lo.amp

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#እናት #መኢአድ #ኢሕአፓ " መንግስት በቅጡ ሐዘናችንን እንድንወጣ ባያውጅልንም በራስ ተነሳሽነት በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭ ሀገር የምትገኙ ኢትዮጵያውያን በመጪው ሰኞ፣ ሐምሌ 4 ቀን 2014 ዓ/ም ጥቁር ልብስ በመልበስ በቅርቡ በወለጋ፣ ቤኒሻንጉል እና ጋምቤላ ለተጨፈጨፉ ወገኖቻችን የተሰማችሁን ሐዘን እንድትገልጹ ጥሪያችንን እያስተላለፍን በዕለቱ ከቀኑ 6:30 ላይ ዅላችሁም በያላችሁበት የአንድ ደቂቃ…
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#Update

ሶስት ፓርቲዎች (እናት ፣ መኢአድ፣ ኢሕአፓ) ከቀናት በፊት ባወጡት መግለጫ ዛሬ ሰኞ ሐምሌ 4 በቅርቡ በወለጋ፣ ቤኒሻንጉል እና ጋምቤላ ለተጨፈጨፉ ወገኖች ኢትዮጵያውያን የተሰማቸውን ሐዘን እንዲገልፁ ጥሪ አቅርበው ነበር።

ፓርቲዎቹ በግፍ ለተጨፈጨፉት ወገኖች " መንግስት በቅጡ ሐዘናችንን እንድንወጣ አላወጀልንም " ያሉ ሲሆን በዚህም የተነሳ በራስ ተነሳሽነት የዛሬ ሐምሌ 4 መርሀግብር ማዘጋጀታቸውን ነበር የገለፁት።

በዛሬው ዕለትም በሀገር ውስጥ እና በውጭ ሀገራት የሚገኙ ኢትዮጵያውያን #ጥቁር_ልብስ በመልበስ ሐዘናቸው መግለፃቸውን ሚያስዩ ፎቶዎች በማህበራዊ ሚዲያ እያጋሩ ነው።

ከቀኑ 6:30 ላይ ኢትዮጵያውያን በያሉበት የአንድ ደቂቃ የሕሊና ጸሎት እንዲያደርጉም ፓርቲዎቹ ጥሪ አቅርበው የነበረ ሲሆን ይህንን የሚያሳዩ ፎቶዎች ደርሰውን ተመልክተናል።

የፓርቲዎች አመራሮችም በፅ/ቤታቸው ሻማ በማብራት ሀዘናቸውን መግለፃቸውን ተመልክተናል።

@tikvahethiopia
ፎቶ ፦ ዛሬ መዲናችን አዲስ አበባ ከጥዋት ጀምሮ በጭጋግ ተሸፍናለች።

የዛሬው የአየር ሁኔታ ከአዲስ አበባ ለሚነሱ እና አዲስ አበባ ለሚያርፉ አውሮፕላኖችም መዘግየት ምክንያት ሆኗል።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ አዲስ አበባ ላይ ባለው ጭጋጋማ የአየር ሁኔታ ምክንያት በቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ የበረራዎች መዘግየት እንዳጋጠመው ገልጿል።

አየር መንገዱ ፤ በአየር ሁኔታ ምክንያት ከአዲስ አበባ የሚነሱም ሆነ የሚያርፉ አውሮፕላኖች ለመዘግየት መገደዳቸውን ጠቅሶ መንገደኞችን ይቅርታ ጠይቋል።

ፎቶዎች ፦ ከማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች የተሰባሰቡ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update ትላንት አርብ በአደባባይ በአንድ የፖለቲካ ቅስቀሳ ላይ ንግግር ሲያደርጉ በጥይት ተመተገው የተገደሉት የቀድሞ የጃፓን ጠ/ሚ ሺንዞ አቤ አስክሬናቸው ቶክዮ ወደሚገኘው መኖሪያ ቤታቸው ገብቷል። አስክሬናቸው ቶኪዮን መኖሪያ ቤታቸው ሲደርስ ፤ የገዢው ፓርቲያቸው አባላት LDP ጥቁር በጥቁር ለብሰው የተቀበሉ ሲሆን የአሁኑ ጠ/ሚ ፉሚዮ ኪሺዳ ከሰዓት በኃላ ወደ ሺንዞ አቤ ቤት ይመጣሉ ተብሏል። …
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
" በፀጥታ አጠባበቁ ላይ ችግሮች እንደነበሩ መካድ አይቻልም " - ፖሊስ

የጃፓን ፖሊስ ባለፈው ዓርብ በደቡባዊቷ ናራ ከተማ የቀድሞው የጃፓን ጠቅላይ ሚኒስትር ሺንዞ አቤ ግድያ በተፈጸመበት ወቅት የፀጥታ ጥበቃ ክፍተቶች እንደነበሩ ገልጿጻ።

የናራ ፖሊስ አዛዥ ቶሞአኪ ኦኒዙካ ፤ " በፀጥታ አጠባበቁ ላይ ችግሮች እንደነበሩ መካድ አይቻልም " ሲሉ ተናግረዋል።

ተፈጥረዋል ያሏቸውን ክፍተቶች የት ላይ እንደሆኑ ግን ከመግለጽ ተቆጥበዋል።

በሺንዞ አቤ ላይ ግድያውን በመፈጸም የተጠረጠረው የ41 ዓመቱ ቴሱያ ያማጋሚ አንድ በስም ያልተጠቀሰ ተቋም ላይ ቂም ይዞ ነበር ሲል ፖሊስ ይፋ አድርጓል።

የጃፓን የመገናኛ ብዙኃን ፤ ለምርመራው ቅርብ የሆኑ ምንጮችን ጠቅሶ እንደዘገቡት ከሆነ ተጠርጣሪው ወላጅ እናቱን የገንዘብ ቀውስ ውስጥ ከከተተ አንድ የሃይማኖት ቡድን ጋር ሺንዞ አቤ ግንኙነት አላቸው ብሎ ያምናል።

ፖሊስ በተጠርጣሪውና በክስተቱ ላይ ጥልቅ ምርመራ እያካሄደ ይገኛል።

መረጃው የቢቢሲ ነው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ፎቶ ፦ ዛሬ መዲናችን አዲስ አበባ ከጥዋት ጀምሮ በጭጋግ ተሸፍናለች። የዛሬው የአየር ሁኔታ ከአዲስ አበባ ለሚነሱ እና አዲስ አበባ ለሚያርፉ አውሮፕላኖችም መዘግየት ምክንያት ሆኗል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ አዲስ አበባ ላይ ባለው ጭጋጋማ የአየር ሁኔታ ምክንያት በቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ የበረራዎች መዘግየት እንዳጋጠመው ገልጿል። አየር መንገዱ ፤ በአየር ሁኔታ ምክንያት ከአዲስ አበባ የሚነሱም ሆነ…
#Update

የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአዲስ አበባ በተከሰተው ጭጋጋማ የአየር ጸባይ ምክንያት ተቋርጦ የነበረው የአውሮፕላን በረራ በአብዛኛው መጀመሩን አሳውቋል።

ባለፉት ጥቂት ሰአታት በአዲስ አበባ የነበረው ጭጋጋማ የአየር ሁኔታ መሻሻል ማሳየቱንም ገልጿል።

በዚህም ወደ ኢትዮጵያ የሚደረጉና ከኢትዮጵያ የሚነሱ በረራዎች #በአብዛኛው መጀመራቸውን አሳውቋል።

አየር መንገዱ ፤ ለደንበኞቹ ተጨማሪ መረጃዎች ማድረሱን እንደሚቀጥል በማህበራዊ ትስስር ገፁ ላይ አስፍሯል።

@tikvahethiopia
#ትኩረት📣

ነዋሪዎችን ከፍተኛ ስጋት ላይ የጣለው የፀጥታ ችግር !

ከቲክቫህ ቤተሰብ አባል ከአጣዬ አካባቢ ፦

" እንደ ሁል ጊዜው ሁሉ አጣዬ ከተማ ዳግም ከፍተኛ የፀጥታ ስጋት ውስጥ ገብታለች።

ይሄም የሆነው በሰሜን ሸዋ እና በኦሮሞ ብሄረሰብ አስተዳደር አዋሳኝ ቦታዎች ዳግም ግጭት በመቀስቀሱ ነው።

ትላንት ማለትም በ02/11/2014 " የቤት እንሰሶች የተዘራ ሰብልን በሉብን " በማለት ልዩ ቦታው አርሶ አምባ የሚባል ስፍራ ፀብ የተነሳ ሲሆን አሁን ላይ አድማሱ ሰፍቶ በተለያየ አቅጣጫ ከባባድ ውጊያዎች ተከፍተዋል።

የተለያዩ የፀጥታ አካላትም ጉዳት ደርሶባቸው በአጣዬ ሆስፒታል ሲገቡም ተመልክተናል።

ቦታዎቹ ላይ ልዩ ሀይል እና ፌደራል ፖሊስ ያለ ቢሆንም እጅግ ብዙ ቁጥር ያለው ሀይል ነው ጥቃቱን እየሰነዘረ የሚገኘው።

ስለሆነም ለማብረድ እንደተቸገሩ እየተሰማ ነው የሚገኘው።

ከከሰአት ጀምሮ ከአዲስ አበባ ወደ ደሴ የሚወስደው መንገድም እንደተዘጋ እና ከወትሮው በተለየ መልኩ የመኪኖች እንቅስቃሴ ቀንሷል።

የፌደራል መንግሥቱ እና የሚመለከታቸው አካላት ይሄንን ነገር አሁን ካለበት ሳይባባስ ትኩረት ሊሰጡት ይገባል። "

በአካባቢው ግጭት መቀስቀሡን የሰሜን ሸዋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ የሆኑት አቶ ታደሰ ገብረፃዲቅ ለአል አይን ኒውስ ያረጋገጡ ሲሆን ግጭቱ ሳይባባስ ለማስቆም ተጨማሪ ሀይል ወደ ስፍራው ተልኳል ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" ምን አዲስ ነገር አለ ? " ትላንት ይፋ ከሆነው የጋራ መኖሪያ ቤቶች ዕጣ ጋር በተያያዘ አጠቃላይ የቤት ባለዕድለኞች ስም ዝርዝር ይፋ እንዳልተደረገ ይታወቃል። ይህን ተከትሎ ትላንት የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት በሰጠው መረጃ ዛሬ ቅዳሜ ወይም ነገ እሁድ አልያም ሰኞ ይፋ እንደሚደረግ ገልጾ ነበር። ኮርፖሬሽኑ ዝርዝሩ ይፋ የሚያደርገው በራሱ ድረገፅ እንዲሁም በአዲስ…
ቅሬታ !

የጋራ መኖሪያ ቤት ዕጣ ደርሷቸው እንደሆነ ለማወቅ የሚጠባበቁ ነዋሪዎች የስም ዝርዝር ይፋ ባለመደረጉ ቅሬታ እንዳላቸው ገለፁ።

የ20/80 እና 40/60 የጋራ መኖሪያ ቤት ዕጣ ዓርብ ቢወጣም እስካሁን የቤት ዕጣ የደረሳቸው ሰዎች ስም ዝርዝር በይፋ አልተገለፀም።

ይህም የቤት ዕጣ ደርሷቸው እንደሆን ለማወቅ እየተጠባበቁ ባሉ ነዋሪዎች ዘንድ ከፍተኛ ቅሬታን ፈጥሯል።

የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን አርብ ለቲክቫህ ቤተሰብ አባላት በሰጠው ቃል ፥ የቤት ዕጣ የወጣላቸው ነዋሪዎች ዝርዝር እስከ ዛሬ ሰኞ ድረስ ኦዲት ተደርጎ በኮርፖሬሽኑ ድረገፅ እንዲሁም በአዲስ ልሳን ጋዜጣ ታትሞ እንደሚወጣ ገልጾ ነበር።

እጥፍ ክፍያም ተከፍሎ ቢሆን በጋዜጣው ታትሞ እንዲወጣ እየተሰራ እንደነበር ኮርፖሬሽኑ መገለፁ አይዘነጋም።

የስም ዝርዝሩ ግን ዛሬ በድረገፁም ሆነ በጋዜጣው አልወጣም።

የስም ዝርዝር ይፋ ባለመደረጉ ቤት ደርሷቸው እንደሆነ ለማወቅ የሚጠባበቁ ነዋሪዎች ቅሬታ እንዳደረባቸው ገልፀዋል።

የደረሳቸው ሰዎች ከታወቁ ለምን ይህን ያህል ሊቆይ ቻለ ? በዲጂታል ሚዲያ ለምን ማሰራጨት አልተቻለም ? በኦንላይን ይታያል ተብሎ በአርቡ ስነስርዓት ላይ ተገልፆ ነበር ይህ ለምን አልሆነም ? ከተማ አስተዳደሩ ግልፅ ማባራሪያ ሊሰጥ ይገባል ሲሉ ጠይቀዋል።

ቅሬታዎችን ይዘን ዛሬ ከጥዋት ጀምሮ ለሚመለከታቸው አካላት ስልክ ብንደውልም ስልክ አይነሳም።

አሁንም ዕጣ የወጣላቸው ነዋሪዎች የስም ዝርዝር በተመለከተ ማብራሪያ ለማግኘት እየጣርን እንገኛለን ሲሳካልን እና ትክክለኛ መረጃ ሲደርሰን እንልክላችኃለን።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ቅሬታ ! የጋራ መኖሪያ ቤት ዕጣ ደርሷቸው እንደሆነ ለማወቅ የሚጠባበቁ ነዋሪዎች የስም ዝርዝር ይፋ ባለመደረጉ ቅሬታ እንዳላቸው ገለፁ። የ20/80 እና 40/60 የጋራ መኖሪያ ቤት ዕጣ ዓርብ ቢወጣም እስካሁን የቤት ዕጣ የደረሳቸው ሰዎች ስም ዝርዝር በይፋ አልተገለፀም። ይህም የቤት ዕጣ ደርሷቸው እንደሆን ለማወቅ እየተጠባበቁ ባሉ ነዋሪዎች ዘንድ ከፍተኛ ቅሬታን ፈጥሯል። የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት…
#ማብራሪያ የ20/80 እና 40/60 ጉዳይ 👆

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፦

" ... ከዕጣ አወጣጥ ስነ-ስርዓት በኋላ የተለያዩ ጥቆማዎች በመቅረባቸው የኦዲት ሥራ ስንጀምር በባንክ የተላከውና ለእጣ እንዲውል ወደ ኮምፒዩተር የተጫነው ዳታ ልዩነቶች ተግኝተዋል።

በመሆኑም በእስካሁኑ የማጠራት ስራ ላልቆጠቡ ሰዎች እጣ መውጣትን ጨምሮ የተለያዩ የተዓማኒነት ጉድለቶች ታይተዋል፡፡

ከዚህ በመነሳትም የቤት ማስተላለፉን ሂደት ግልፅነት ለማስፈን ሲባል እና ውጤቱን የሚያዛባ ተግባር ሲያጋጥም መልሰን ኦዲት እንዲደረግ በገባነው ቃል መሰረት የተፈጠረውን ችግር ከጉዳዩ ገለልተኛ በሆኑ በሚመለከታቸው ተቋማት የማጣራት ስራ በመከናወን ላይ የሚገኝ ሲሆን በጉዳዩ የተጠረጠሩ ባለሙያዎች እና አመራር #በቁጥጥር_ሥር ሆነው ምርመራ እየተደረገ ይገኛል።

ስለሆነም ሂደቱን በአጭር ጊዜ አጠናቀን ለቤት ተመዝጋቢዎችና ለመላው የከተማችን ነዋሪ የምናሳውቅ መሆኑን ስንገለጽ ተመዝጋቢዎች እንደተለመደው በከፍተኛ ትዕግስት እንድትጠባበቁ እናሳውቃለን፡፡

ለተፈጠረው ስህተት የከተማ አስተዳደሩ በዚህ አጋጣሚ ይቅርታ ይጠይቃል። "

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ትኩረት📣 ነዋሪዎችን ከፍተኛ ስጋት ላይ የጣለው የፀጥታ ችግር ! ከቲክቫህ ቤተሰብ አባል ከአጣዬ አካባቢ ፦ " እንደ ሁል ጊዜው ሁሉ አጣዬ ከተማ ዳግም ከፍተኛ የፀጥታ ስጋት ውስጥ ገብታለች። ይሄም የሆነው በሰሜን ሸዋ እና በኦሮሞ ብሄረሰብ አስተዳደር አዋሳኝ ቦታዎች ዳግም ግጭት በመቀስቀሱ ነው። ትላንት ማለትም በ02/11/2014 " የቤት እንሰሶች የተዘራ ሰብልን በሉብን " በማለት ልዩ ቦታው…
#Update

" የፀጥታ አካላት እና ንፁሃን አርሶአደሮች ህይወታቸው አልፏል "

በኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን ጅሌ ጥሙጋ ወረዳ እና በሰሜን ሸዋ ዞን ኤፍራታና ግድም ወረዳ አዋሳኝ አከባቢዎች መካከል በተከሰተው ግጭት በፀጥታ አካላት እንዲሁም በንፁሃን አርሶአደሮች ላይ የሕይወት መጥፋት እና የአካል ጉዳት ደርሷል፡፡

በንፁሃን ዜጎች እና በንብረት ላይም ጉዳት መድረሱ ተገልጿል።

በሰላም እና በተረጋጋ ሁኔታ በሚኖሩ ሰላማዊ ዜጎች ላይ አለመረጋጋት ተከስቷል፡፡

ይህን ተከትሎ በኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን ጅሌ ጥሙጋ ወረዳ በኩል የተለያዩ ክልከላዎች ተጥለዋል ፦

- ማንኛውም በወረዳው እና በከተማው ውስጥ የሚገኙ የሶስት እግር ተሽከርካሪዎችን (ባጃጆችን) ላልተወሰነ ጊዜያት በቀንም ሆነ በማታ ማሽከርከር አይችልም።

- ከመንግሥት የፀጥታ መዋቅር ውጭ ማንኛውንም አካል የጦር መሣሪያ ይዞ መንቀሳቀስ አይችልም።

- ከተፈቀደለት የፀጥታ አስከባሪ መዋቅር ውጭ ማንኛውም ግለሰብ ከቀበሌ ወደ ቀበሌ መንቀሳቀስ አይችልም።

- በህብረተሰቡ ውስጥ እና በማህበራዊ ሚዲያ ተጨባጭ ያልሆኑ መረጃዎችን የሚያናፍሱ አካላት ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ ጥብቅ ማሳሰቢያ ተላልፏል።

(የጅሌ ጥሙጋ ወረዳ ሙሉ መግለጫ ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ማብራሪያ የ20/80 እና 40/60 ጉዳይ 👆 የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፦ " ... ከዕጣ አወጣጥ ስነ-ስርዓት በኋላ የተለያዩ ጥቆማዎች በመቅረባቸው የኦዲት ሥራ ስንጀምር በባንክ የተላከውና ለእጣ እንዲውል ወደ ኮምፒዩተር የተጫነው ዳታ ልዩነቶች ተግኝተዋል። በመሆኑም በእስካሁኑ የማጠራት ስራ ላልቆጠቡ ሰዎች እጣ መውጣትን ጨምሮ የተለያዩ የተዓማኒነት ጉድለቶች ታይተዋል፡፡ ከዚህ በመነሳትም…
" ዕጣው ሙሉ ለሙሉ ተሰርዟል ብሎ መናገር አይቻልም " - የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን

የ20/80 እና የ40/60 የጋራ መኖሪያ ቤቶች ሙሉ ለሙሉ ተሰርዟል ብሎ መናገር አይቻልም ሲል የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን ገለፀ።

የኮርፖሬሽኑ የሥራ ሀላፊ አቶ ሽመልስ ታምራት " ዳታው ገብቶ ዕጣው ከወጣ በኋላ ያሉ ስህተቶች መኖራቸው ይታያል በተባለው መሰረት የተወሰኑ ክፍተቶች አሉ " ሲሉ ተናግረዋል፡፡

በዚህም መሰረት የከተማ አስተዳደሩ ምን ሊወስን እንደሚችል አልታወቀም ሲሉ ገልፀዋል።

አቶ ሽመልስ ጉዳዩና ውሳኔው ዛሬ ሊታወቅ ይችላል ሲሉም ጠቁመዋል።

ባለፈው ሳምንት ዓርብ 25,491 ሰው ዕጣ ወጥቶለታል ያሉት አቶ ሽመልስ ፤ ስህተት የፈጠረው ሰው እንደተለየው ሁሉ በስህተቱ እድሉ የተፈጠረለት ማነው የሚለው ተለይቶ ወደ ሚቀጥለው ደረጃ የሚያሻግረው አማራጭ ይታያል ተብሎ እንደሚታመን አስረድተዋል።

ከዚህ ቀደም የነበረው የተዝረከረከ አሰራር እንዳይኖር ቀድሞ ማጣራት ተደርጓል ያለው የቤቶች ኮርፖሬሽን ዳታው ከገባ እና ዕጣው ከወጣ በኋላ ያሉ ስህተቶች መኖራቸውን ገልጿል፤ ጉዳዩ እልባት ለማግኘት ተቃርቧል ሲልም አሳውቋል።

መረጃው የሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ነው።

@tikvahethiopia