TIKVAH-ETHIOPIA
#Update የጋራ መኖሪያ ቤቶች ዕጣ የማውጣት ሂደት ቀጥሏል። ከዛሬው የዕጣ አወጣጥ ጋር በተያያዘ የ20/80 ባለሶስት መኝታ ቆጣቢዎች ጥያቄ እየተነሳ ይገኛል። በ20/80 የባለ ሶስት መኝታ ቤት ያልተካተተው በ12ኛ ዙር በልዩ ሁኔታ ታይቶ እስከ 1500 ብር ቁጠባ ድረስ የተካተቱና በቦርድ ውሳኔ ባለሶስት መኝታ በወቅቱ የተዘጋ በመሆኑ ነው ተብሏል። ቆጣቢዎቹ ተስፋ ባለመቁረጥ ቁጠባቸው በመቀጠላቸው…
#ማብራሪያ👆
የ20/80 #ባለሶስት_መኝታ የጋራ መኖርያ ቤት እጣ አለመውጣትን አስመልክቶ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ዛሬ ምሽት ተጨማሪ ማብራሪያ ሰጥቷል።
የከተማ አስተዳደሩ ሙሉ ማብራሪያ ከላይ ተያይዟል።
@tikvahethiopia
የ20/80 #ባለሶስት_መኝታ የጋራ መኖርያ ቤት እጣ አለመውጣትን አስመልክቶ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ዛሬ ምሽት ተጨማሪ ማብራሪያ ሰጥቷል።
የከተማ አስተዳደሩ ሙሉ ማብራሪያ ከላይ ተያይዟል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
" እንወጣም " - ተቃዋሚዎች
የስሪላንካ ጉዳይ ዓለምን ማነጋገሩ ቀጥሏል።
የስሪላንካ ፕሬዜዳንት ከስልጣን ወርዳለሁ ቢሉም ተቃዋሚዎች ከመኖሪያ ቤታቸው ለቀን አንወጣም ብለዋል።
የስሪላንካ ፕሬዜዳንት ጎታባያ ራጃፓክሳ መኖሪያ ቤትን የተቆጣጠሩት ተቃዋሚዎች ዛሬም ፕሬዝዳንታዊ መኖሪያውን እንደማይለቁ ገልፀዋል።
ተቃዋሚዎቹ የፕሬዜዳንቱን መኖሪያን ከተቆጣጠሩ በኃላና ፕሬዝዳንቱ በባህር ኃይል ታግዘው ከሸሹ በኃላ ከስልጣን እወርዳለሁ ቢሉም ተቃዋሚዎች ግን እስካሁን አልተቀበሉትም።
የተማሪዎች ንቅናቄ መሪ የሆነው ላሂሩ ዋራሴካራ ለጋዜጣኞች በሰጠው መግለጫ " ትግላችን ግና አላበቃም እሱ እስካልተወገደ ድረስ ትግላችንን እናቆምም " ሲል ተደምጧል።
ተቃዋሚዎቹ በፕሬዜዳንቱ አቅም ማነስ በሀገሪቱ ኢኮኖሚ ላይ ውድቀት መከተሉን እና ሙስና መንሰራፋቱን ይገልፃሉ ፤ በሀገሪቱ ለተፈጠረው የመድሃኒት ፣ የነዳጅ፣ የምግብ እጥረት እና ለድሃው ህዝብ ኑሮ መመሰቃቀልም ፕሬዜዳንቱን ተጠያቂ ያደርጋሉ።
በሌላ በኩል የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን " የሩሲያ ወረራ " ሲሪላንካ ውስጥ ለተፈጠረው ቀውስ አስተዋጽኦ ሳይኖረው አይቀርም ብለዋል። ብሊንከን " የሩሲያ ወረራ ያስከተለው ችግር በየቦታው እየታየ ነው " ሲሉ ገልፀዋል።
መረጃው፦ ከአሶሼትድ ፕሬስ ፣ አርቲ እና ዶቼቨለ የተገኘ ነው።
@tikvahethiopia
የስሪላንካ ጉዳይ ዓለምን ማነጋገሩ ቀጥሏል።
የስሪላንካ ፕሬዜዳንት ከስልጣን ወርዳለሁ ቢሉም ተቃዋሚዎች ከመኖሪያ ቤታቸው ለቀን አንወጣም ብለዋል።
የስሪላንካ ፕሬዜዳንት ጎታባያ ራጃፓክሳ መኖሪያ ቤትን የተቆጣጠሩት ተቃዋሚዎች ዛሬም ፕሬዝዳንታዊ መኖሪያውን እንደማይለቁ ገልፀዋል።
ተቃዋሚዎቹ የፕሬዜዳንቱን መኖሪያን ከተቆጣጠሩ በኃላና ፕሬዝዳንቱ በባህር ኃይል ታግዘው ከሸሹ በኃላ ከስልጣን እወርዳለሁ ቢሉም ተቃዋሚዎች ግን እስካሁን አልተቀበሉትም።
የተማሪዎች ንቅናቄ መሪ የሆነው ላሂሩ ዋራሴካራ ለጋዜጣኞች በሰጠው መግለጫ " ትግላችን ግና አላበቃም እሱ እስካልተወገደ ድረስ ትግላችንን እናቆምም " ሲል ተደምጧል።
ተቃዋሚዎቹ በፕሬዜዳንቱ አቅም ማነስ በሀገሪቱ ኢኮኖሚ ላይ ውድቀት መከተሉን እና ሙስና መንሰራፋቱን ይገልፃሉ ፤ በሀገሪቱ ለተፈጠረው የመድሃኒት ፣ የነዳጅ፣ የምግብ እጥረት እና ለድሃው ህዝብ ኑሮ መመሰቃቀልም ፕሬዜዳንቱን ተጠያቂ ያደርጋሉ።
በሌላ በኩል የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን " የሩሲያ ወረራ " ሲሪላንካ ውስጥ ለተፈጠረው ቀውስ አስተዋጽኦ ሳይኖረው አይቀርም ብለዋል። ብሊንከን " የሩሲያ ወረራ ያስከተለው ችግር በየቦታው እየታየ ነው " ሲሉ ገልፀዋል።
መረጃው፦ ከአሶሼትድ ፕሬስ ፣ አርቲ እና ዶቼቨለ የተገኘ ነው።
@tikvahethiopia
ፎቶ ፦ ኤርትራ ያሉ የሶማሊያ ብሄራዊ ጦር አባላት ዛሬ በፎቶ ታይተዋል።
አዲሱ የሶማሊያ ፕሬዜዳንት ሀሰን ሼክ ሙሃሙድ ላለፉት 2 ዓመታት በኤርትራ ስልጠናቸውን እየተከታተሉ የሚገኙትን የሶማሊያ ብሄራዊ ጦር አባላትን ጎብኝተዋል።
ፕሬዜዳንቱ ኤርትራ ያሉ የሶማሊያ ጦር አባላትን ከኤርትራው ፕሬዜዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ጋር በመሆን ነው የጎበኙት ተብሏል።
የሶማሊያው ፕሬዜዳንት ከትላንት ጀምሮ በኤርትራ የስራ ጉብኝት እያደረጉ ይገኛሉ።
Photo Credit - Yemane G. Meskel
@tikvahethiopia
አዲሱ የሶማሊያ ፕሬዜዳንት ሀሰን ሼክ ሙሃሙድ ላለፉት 2 ዓመታት በኤርትራ ስልጠናቸውን እየተከታተሉ የሚገኙትን የሶማሊያ ብሄራዊ ጦር አባላትን ጎብኝተዋል።
ፕሬዜዳንቱ ኤርትራ ያሉ የሶማሊያ ጦር አባላትን ከኤርትራው ፕሬዜዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ጋር በመሆን ነው የጎበኙት ተብሏል።
የሶማሊያው ፕሬዜዳንት ከትላንት ጀምሮ በኤርትራ የስራ ጉብኝት እያደረጉ ይገኛሉ።
Photo Credit - Yemane G. Meskel
@tikvahethiopia
#ጋና
" የእኔን ጨምሮ የሁሉም ተሿሚዎች ደመወዝ በ30 በመቶ ቀንሷል " - የጋና ፕሬዜዳንት
የጋናው ፕሬዝደንት ናና አዶ ዳንኩዋ አኩፎ-አዶ በሀገሪቱ የኢኮኖሚ ቀውስ ሳቢያ የራሳቸውን ጨምሮ የሁሉም ተሿሚዎቻቸው ደመወዝ በ30 % እንዲቀንስ መደረጉን አስታውቀዋል።
ይህን ያስታወቁት ትላንትና የዒድ አል-አድሃ በዓል ሲከበር ባሰሙት ንግግር ነው።
የ30% ቅነሳው የሚኒስቴር መስሪያ ቤቶችን፣ የመንግስት ኤጀንሲዎችን እና መምሪያዎችን ወጪ ይነካልም ተብሏል።
ፕሬዜዳንቱ ፤ መንግስት እያሽቆለቆለ ያለውን ኢኮኖሚ ለመታደግ በሚያደርገው ጥረት ጋናውያን መስዋዕትነት እንዲከፍሉ ተማጽነዋል።
" አሁን ያለውን ችግር ለመቅረፍ ሁላችንም መስዋዕትነት መክፈል አለብን " ያሉት ፕሬዜዳንቱ " የሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች፣ መምሪያዎች እና ኤጀንሲዎች ወጪ በ30 በመቶ ቀንሷል። የእኔን ጨምሮ የሁሉም ተሿሚዎች ደመወዝም በ30 በመቶ ቀንሷል " ብለዋል።
የነዳጅ ኩፖን ምደባ በ50 % መቀነሱን እንዲሁም ሌሎች ወጪዎች መታገዳቸውን ገልፀዋል።
ኢኮኖሚውን ለማረጋጋት የተለያዩ እርምጃዎች እየተወሰዱ መሆኑን የገለፁት ፕሬዜዳንቱ ጋናውያን እንዲታገሷቸው አሳስበዋል።
ፕሬዝዳንት ናና አዶ አኩፎ አዶ እኤአ ሰኔ 1/2022 የገንዘብ ሚኒስትሩ ኬን ኦፎሪ-አታ ከዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) ጋር ይፋዊ ግንኙነቶችን እንዲጀምሩ አዘው ነበር።
የIMF ድጋፍ በኮቪድ-19 ወረርሽኝ እና በቅርቡ የሩስያ እና ዩክሬን ጦርነት ሳቢያ እያጋጠሙ ያሉ የኢኮኖሚ ችግሮችን ለመፍታት ከሚደረጉ ጥረቶች አንዱ ነው ተብሏል።
Video Credit : Citi TV, Ghana
@tikvahethiopia
" የእኔን ጨምሮ የሁሉም ተሿሚዎች ደመወዝ በ30 በመቶ ቀንሷል " - የጋና ፕሬዜዳንት
የጋናው ፕሬዝደንት ናና አዶ ዳንኩዋ አኩፎ-አዶ በሀገሪቱ የኢኮኖሚ ቀውስ ሳቢያ የራሳቸውን ጨምሮ የሁሉም ተሿሚዎቻቸው ደመወዝ በ30 % እንዲቀንስ መደረጉን አስታውቀዋል።
ይህን ያስታወቁት ትላንትና የዒድ አል-አድሃ በዓል ሲከበር ባሰሙት ንግግር ነው።
የ30% ቅነሳው የሚኒስቴር መስሪያ ቤቶችን፣ የመንግስት ኤጀንሲዎችን እና መምሪያዎችን ወጪ ይነካልም ተብሏል።
ፕሬዜዳንቱ ፤ መንግስት እያሽቆለቆለ ያለውን ኢኮኖሚ ለመታደግ በሚያደርገው ጥረት ጋናውያን መስዋዕትነት እንዲከፍሉ ተማጽነዋል።
" አሁን ያለውን ችግር ለመቅረፍ ሁላችንም መስዋዕትነት መክፈል አለብን " ያሉት ፕሬዜዳንቱ " የሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች፣ መምሪያዎች እና ኤጀንሲዎች ወጪ በ30 በመቶ ቀንሷል። የእኔን ጨምሮ የሁሉም ተሿሚዎች ደመወዝም በ30 በመቶ ቀንሷል " ብለዋል።
የነዳጅ ኩፖን ምደባ በ50 % መቀነሱን እንዲሁም ሌሎች ወጪዎች መታገዳቸውን ገልፀዋል።
ኢኮኖሚውን ለማረጋጋት የተለያዩ እርምጃዎች እየተወሰዱ መሆኑን የገለፁት ፕሬዜዳንቱ ጋናውያን እንዲታገሷቸው አሳስበዋል።
ፕሬዝዳንት ናና አዶ አኩፎ አዶ እኤአ ሰኔ 1/2022 የገንዘብ ሚኒስትሩ ኬን ኦፎሪ-አታ ከዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) ጋር ይፋዊ ግንኙነቶችን እንዲጀምሩ አዘው ነበር።
የIMF ድጋፍ በኮቪድ-19 ወረርሽኝ እና በቅርቡ የሩስያ እና ዩክሬን ጦርነት ሳቢያ እያጋጠሙ ያሉ የኢኮኖሚ ችግሮችን ለመፍታት ከሚደረጉ ጥረቶች አንዱ ነው ተብሏል።
Video Credit : Citi TV, Ghana
@tikvahethiopia
ፎቶ ፦ ነሲሓ የበጎ አድራጎትና የልማት ድርጅት (NCDO) በደብረ ብርሃን መጠለያ ካምፕ ውስጥ ለሚገኙ የወለጋ ተፈናቃዮች ድጋፍ አደረገ።
ድርጅቱ ፤ የዒደ አል አድሐ በዓልን በማስመልከት በሁለት ዙር ድጋፍ ያደረገ ሲሆን ፤ በመጀመሪያው ዙር 19 በሬዎችን ፣ በሁለተኛ ዙር 10 በሬዎችንና 100 በጎችን በደምሩ 1.8 ሚሊዮን ብር ገደማ የሚገመት ድጋፍ አድርጓል።
ድርጅቱ ለወደፊቱም በሚችለው ሁሉ እገዛውን ለሚሹ የማኅበረሰብ ክፍሎች የሚያደርገውን ድጋፍ #አጠናክሮ እንደሚቀጥል አሳውቋል።
Credit : NCDO
@tikvahethiopia
ድርጅቱ ፤ የዒደ አል አድሐ በዓልን በማስመልከት በሁለት ዙር ድጋፍ ያደረገ ሲሆን ፤ በመጀመሪያው ዙር 19 በሬዎችን ፣ በሁለተኛ ዙር 10 በሬዎችንና 100 በጎችን በደምሩ 1.8 ሚሊዮን ብር ገደማ የሚገመት ድጋፍ አድርጓል።
ድርጅቱ ለወደፊቱም በሚችለው ሁሉ እገዛውን ለሚሹ የማኅበረሰብ ክፍሎች የሚያደርገውን ድጋፍ #አጠናክሮ እንደሚቀጥል አሳውቋል።
Credit : NCDO
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update
ብፁዕ አቡነ አረጋዊ (ዶ/ር) የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽ/ቤትና የውጭ ጉዳይ መምሪያ የበላይ ኃላፊ የድሬዳዋና ጅቡቲ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል ሕክምናቸውን አጠናቀው ሐምሌ 8 ቀን 2014 ዓ.ም ወደ ሀገራቸው እንደሚመለሱ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሕክምና ማኅበር አስታውቋል።
ብፁዕ አቡነ አረጋዊ (ዶ/ር) ለከፍተኛ ሕክምና ወደ ክሊቭላንድ ክሊኒክ ሆስፒታል አቡዳቢ (Cleveland Clinic Abu Dhabi) በቅዱስ ሲኖዶስ እና በጠቅላይ ቤተክህነት ፈቃድ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሕክምና ማኅበር አስፈላጊውን የዝውውር ሂደት ከባለሙያዎች ጋር በማመቻቸት ግንቦት 3 ቀን 2014 ዓ.ም መጓዛቸውና ሕክምናቸውን በዚያው ሲከታተሉ ቆይተዋል።
ብፁዕ አቡነ አረጋዊ (ዶ/ር) ጤንነታቸው በአሁኑ ሰዓት #በመልካም ሁኔታ ላይ የሚገኝ ሲሆን ሕክምናቸውን በማጠናቀቅ ወደ ኢትዮጵያ ሐምሌ 8 ቀን 2014 ዓ.ም ላይ ከማኅበሩ የሕክምና ቡድን ጋር ይመለሳሉ መባሉን ከEOTC ያገኘነው መረጃ ያመልክታል።
@tikvahethiopia
ብፁዕ አቡነ አረጋዊ (ዶ/ር) የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽ/ቤትና የውጭ ጉዳይ መምሪያ የበላይ ኃላፊ የድሬዳዋና ጅቡቲ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል ሕክምናቸውን አጠናቀው ሐምሌ 8 ቀን 2014 ዓ.ም ወደ ሀገራቸው እንደሚመለሱ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሕክምና ማኅበር አስታውቋል።
ብፁዕ አቡነ አረጋዊ (ዶ/ር) ለከፍተኛ ሕክምና ወደ ክሊቭላንድ ክሊኒክ ሆስፒታል አቡዳቢ (Cleveland Clinic Abu Dhabi) በቅዱስ ሲኖዶስ እና በጠቅላይ ቤተክህነት ፈቃድ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሕክምና ማኅበር አስፈላጊውን የዝውውር ሂደት ከባለሙያዎች ጋር በማመቻቸት ግንቦት 3 ቀን 2014 ዓ.ም መጓዛቸውና ሕክምናቸውን በዚያው ሲከታተሉ ቆይተዋል።
ብፁዕ አቡነ አረጋዊ (ዶ/ር) ጤንነታቸው በአሁኑ ሰዓት #በመልካም ሁኔታ ላይ የሚገኝ ሲሆን ሕክምናቸውን በማጠናቀቅ ወደ ኢትዮጵያ ሐምሌ 8 ቀን 2014 ዓ.ም ላይ ከማኅበሩ የሕክምና ቡድን ጋር ይመለሳሉ መባሉን ከEOTC ያገኘነው መረጃ ያመልክታል።
@tikvahethiopia
" የተጭበረበራችሁ በስልክም ፤ በአካልም እየቀረባችሁ አመልክቱ " - የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ
የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ በተለያዩ የኦንላይን ማጭበርበሪያ ድርጊት ገንዘባቸውን ያጡ ሰዎች በ991 ወይም 987 ላይ መረጃ መስጠት ይችላሉ አለ።
ፌዴራል ፖሊስ ይህን ያለው ለኢቢሲ በሰጠው ቃል ነው።
የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ኮሚኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ጄይላን አብዲ ፤ " የማህበራዊ እና የኦንላይን ሚዲያዎችን በመጠቀም የበርካታ ሰዎችን ገንዘብ ከሰበሰቡ በኋላ አድራሻቸውን በማጥፋት የተሰወሩ አካላት መኖራቸውን ከደረሰ ጥቆማና ከተለያዩ ምንጮች መረዳት ችለናል " ብለዋል።
ይህን ጉዳይ አስመልከቶ ከተለያዩ የህግ አስከባሪ አካላት ጋር በመተባበር መረጃ የማጣራት እና የምርመራ ስራ እየተሰራ ይገኛል የማጭበርበር ድርጊት የተፈፀመባቸው እና የተመለከቱ ከላይ ባሉት ስልኮች እየደወሉ ማመልከት ይችላሉ ብለዋል።
ከስልክ በተጨማሪ ሜክሲኮ በሚገኘው የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ዋና መስሪያ ቤት 7ኛ ፎቅ የኢንተለጀንስ ቢሮ በመቅረብ መረጃ መስጠት እንደሚችሉ ኃላፊው ለኢቢሲ ተናግረዋል።
ልክ እንደ FIAS 777 አሁን ላይ የተመሳሳይ የማጭበርበር ስራ ከሚሰራባቸው ድረገፆች መካከል hulu61፣ HDU፣ workxo፣ Crowd 1፣ vemo1 እና ሌሎችም ተጠቃሽ መሆናቸው ተገልጿል።
ከዚህ ቀደም በFIAS 777 እና መሰል ድርጅት ነን ባዮች ከ1 ሺ ብር አንስቶ ከ100 ሺህ ብር በላይ የተጭበረበሩ የሚመለከተው አካል መፍትሄ ይፈልግላቸው ዘንድ ጥሪ ሲያቀርቡ እንደነበር አይዘነጋም።
(ማስታወሻ - https://t.iss.one/tikvahethiopia/71364)
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ በተለያዩ የኦንላይን ማጭበርበሪያ ድርጊት ገንዘባቸውን ያጡ ሰዎች በ991 ወይም 987 ላይ መረጃ መስጠት ይችላሉ አለ።
ፌዴራል ፖሊስ ይህን ያለው ለኢቢሲ በሰጠው ቃል ነው።
የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ኮሚኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ጄይላን አብዲ ፤ " የማህበራዊ እና የኦንላይን ሚዲያዎችን በመጠቀም የበርካታ ሰዎችን ገንዘብ ከሰበሰቡ በኋላ አድራሻቸውን በማጥፋት የተሰወሩ አካላት መኖራቸውን ከደረሰ ጥቆማና ከተለያዩ ምንጮች መረዳት ችለናል " ብለዋል።
ይህን ጉዳይ አስመልከቶ ከተለያዩ የህግ አስከባሪ አካላት ጋር በመተባበር መረጃ የማጣራት እና የምርመራ ስራ እየተሰራ ይገኛል የማጭበርበር ድርጊት የተፈፀመባቸው እና የተመለከቱ ከላይ ባሉት ስልኮች እየደወሉ ማመልከት ይችላሉ ብለዋል።
ከስልክ በተጨማሪ ሜክሲኮ በሚገኘው የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ዋና መስሪያ ቤት 7ኛ ፎቅ የኢንተለጀንስ ቢሮ በመቅረብ መረጃ መስጠት እንደሚችሉ ኃላፊው ለኢቢሲ ተናግረዋል።
ልክ እንደ FIAS 777 አሁን ላይ የተመሳሳይ የማጭበርበር ስራ ከሚሰራባቸው ድረገፆች መካከል hulu61፣ HDU፣ workxo፣ Crowd 1፣ vemo1 እና ሌሎችም ተጠቃሽ መሆናቸው ተገልጿል።
ከዚህ ቀደም በFIAS 777 እና መሰል ድርጅት ነን ባዮች ከ1 ሺ ብር አንስቶ ከ100 ሺህ ብር በላይ የተጭበረበሩ የሚመለከተው አካል መፍትሄ ይፈልግላቸው ዘንድ ጥሪ ሲያቀርቡ እንደነበር አይዘነጋም።
(ማስታወሻ - https://t.iss.one/tikvahethiopia/71364)
@tikvahethiopia