#የሹፌሮችድምጽ
" የታገቱትን ሊፈልግ የሚወጣ የጸጥታ ሃይል የለም ሄዱበት በተባለው መንገድ የሚገባ የለም " - ጣና የከባድ መኪና ሹፌሮች ማህበር
በኢትዮጵያ በርካታ አካባቢዎች የከተማ አቋራጭ እና ሃገር አቋራጭ አሽከርካሪዎች ለእገታ እና ግድያ እየተጋለጡ መሆናቸውን በተደጋጋሚ ሲነገር ይደመጣል።
የጣና የከባድ መኪና ሹፌሮች ማህበር በአራት አመት ጊዜ ውስጥ ከ200 የሚበልጡ አሽከርካሪዎች ቢገደሉም ችግሩን ለመቅረፍ ግን ምንም እንቅስቃሴ እየተደረገ አለመሆኑን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።
" ሰው ታፈነ ሲባል ሰውን ያህል ነገር ታፍኖ የአካባቢው የጸጥታ ሃይል የት፣እንዴት ታፈነ የሚለውን ጠይቆ እና አነፍንፎ የሚንቀሳቀስ መንግስት አጥተናል" ሲሉ ስሜ አይጠቀስ ያሉ የማህበሩ አመራር ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
አክለውም " መታገትህን ትናገራለህ ምንም እንዳልተፈጠረ ዝም ይባላል የታገቱትን ሊፈልግ የሚወጣ ሃይል የለም ሄዱበት በተባለው መንገድ የሚገባ የለም " ነው ያሉት።
አጋቾች የሚደራደሩት በስልክ ነው ገንዘብም የሚገባው በባንክ ነው ያሉ ሲሆን እገታን እዚህ ደረጃ ያደረሰው መንግስት ለሚታገቱ እና ለሚገደሉ ሰዎች የሰጠው ትኩረት በማነሱ ምክንያት ነው ብለዋል።
እንደ ማህበሩ አመራር ገለጻ ህዳር አንድ ላይ አራት አሽከርካሪዎች መተሃራ እና አዋሽ ሰባት መሃል ታፍነው በታጣቂዎች ተወስደዋል።
በተደጋጋሚ የሹፌሮች መታገት እና መገደል የነበረባቸው አንደ ታች አርማጭሆ ያሉ አካባቢዎች ሚሊሻዎችን በየመንገዱ የማሰማራት እና መንገዱን የመጠበቅ እንቅስቃሴዎች መኖራቸውን የጠቀሱ ሲሆን በተጠቀሰው አካባቢ መሻሻል አለ ብለዋል።
" ከአይከል -ጭልጋ- ገንዳውሃ " ያለው መንገድ ግን አሁንም ለሹፌሮች እጅግ አስቸጋሪ ሆኖ መቀጠሉን ገልጸው ከመንግሥት ውጪ የሆነ እና በየመንገዱ የሚሰበሰብ እስከ 20 ሺ ብር የሚደርስ ህገወጥ ቀረጥ ሹፌሮችን እያማረረ ነው ብለውናል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
" የታገቱትን ሊፈልግ የሚወጣ የጸጥታ ሃይል የለም ሄዱበት በተባለው መንገድ የሚገባ የለም " - ጣና የከባድ መኪና ሹፌሮች ማህበር
በኢትዮጵያ በርካታ አካባቢዎች የከተማ አቋራጭ እና ሃገር አቋራጭ አሽከርካሪዎች ለእገታ እና ግድያ እየተጋለጡ መሆናቸውን በተደጋጋሚ ሲነገር ይደመጣል።
የጣና የከባድ መኪና ሹፌሮች ማህበር በአራት አመት ጊዜ ውስጥ ከ200 የሚበልጡ አሽከርካሪዎች ቢገደሉም ችግሩን ለመቅረፍ ግን ምንም እንቅስቃሴ እየተደረገ አለመሆኑን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።
" ሰው ታፈነ ሲባል ሰውን ያህል ነገር ታፍኖ የአካባቢው የጸጥታ ሃይል የት፣እንዴት ታፈነ የሚለውን ጠይቆ እና አነፍንፎ የሚንቀሳቀስ መንግስት አጥተናል" ሲሉ ስሜ አይጠቀስ ያሉ የማህበሩ አመራር ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
አክለውም " መታገትህን ትናገራለህ ምንም እንዳልተፈጠረ ዝም ይባላል የታገቱትን ሊፈልግ የሚወጣ ሃይል የለም ሄዱበት በተባለው መንገድ የሚገባ የለም " ነው ያሉት።
አጋቾች የሚደራደሩት በስልክ ነው ገንዘብም የሚገባው በባንክ ነው ያሉ ሲሆን እገታን እዚህ ደረጃ ያደረሰው መንግስት ለሚታገቱ እና ለሚገደሉ ሰዎች የሰጠው ትኩረት በማነሱ ምክንያት ነው ብለዋል።
እንደ ማህበሩ አመራር ገለጻ ህዳር አንድ ላይ አራት አሽከርካሪዎች መተሃራ እና አዋሽ ሰባት መሃል ታፍነው በታጣቂዎች ተወስደዋል።
በተደጋጋሚ የሹፌሮች መታገት እና መገደል የነበረባቸው አንደ ታች አርማጭሆ ያሉ አካባቢዎች ሚሊሻዎችን በየመንገዱ የማሰማራት እና መንገዱን የመጠበቅ እንቅስቃሴዎች መኖራቸውን የጠቀሱ ሲሆን በተጠቀሰው አካባቢ መሻሻል አለ ብለዋል።
" ከአይከል -ጭልጋ- ገንዳውሃ " ያለው መንገድ ግን አሁንም ለሹፌሮች እጅግ አስቸጋሪ ሆኖ መቀጠሉን ገልጸው ከመንግሥት ውጪ የሆነ እና በየመንገዱ የሚሰበሰብ እስከ 20 ሺ ብር የሚደርስ ህገወጥ ቀረጥ ሹፌሮችን እያማረረ ነው ብለውናል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
" ከታህሳስ 2 እስከ ታህሳስ 5 ቀን 2017 ዓ/ም ብቻ 6 ሹፌሮች ከነረዳታቸው በታጣቂዎች ተገድለዋል " - ጣና የከባድ መኪና አሽከርካሪዎች ማኅበር
🚨 " ሹፌርን ማገት የስራ ዘርፍ ሆኖ እየተኖረበት ነው !! "
የከባድ መኪና ሹፌሮች በሃገር አቋራጭ እና ከተማ አቋራጭ ጉዞዎቻቸው ወቅት በታጣቂዎች የሚደርስባቸው እገታ እና ግድያ ተባብሶ መቀጠሉን ጣና የከባድ መኪና አሽከርካሪዎች ማኅበር ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስታውቋል።
ባለፉት 5 አመታት በተለያዩ የኢትዮጵያ አካባቢዎች የተገደሉ ሹፌሮች ቁጥርም 230 መሻገሩን ስሜ አይጠቀስ ያሉ የማህበሩ አመራር ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
ከታህሳስ 2 እስከ 5 ቀን 2017 ዓ/ም ብቻ ስድስት ሹፌሮች ከነረዳታቸው በታጣቂዎች ተገድለዋል ብለዋል።
አራቱ ሹፌሬች የተገደሉት በመተማ ጎንደር መንገድ ጭልጋ አካባቢ ሲሆን ሁለቱ ደግሞ ከጎንደር ሳንጃ መንገድ ፈረስ መግሪያ አካባቢ ነው።
ፈረስ መግሪያ አካባቢ የተገደሉት ሹፌርና ረዳት ሲሆኑ ከታህሳስ 2 ጀምሮ አግተው ገንዘብ እንዲሰጣቸው ሲደራደሩ ቆይተው ታህሳስ 5/2017 ዓ/ም 120 ሺ ብር ከተቀበሉ በኋላ ገድለው እንደጧላቸው ሃላፊው አስረድተዋል።
የችግሩን ክብደት ሲያስረዱም " አንዳንድ ቦታዎች ላይ መኪና ሲበላሽ የመጀመሪያ ስራ ወርዶ ዝቅ ብሎ ማየት አልሆነም የመጀመሪያ ስራ ወርዶ መሮጥ ነው ምክንያቱም እንደቆምክ አንድ ታጣቂ መጥቶ ሊያግትህ ወይም ሊገድልህ ይችላል ምን ተበላሸ ብለህ የምታየው አንድ ሚሊሻ ይዘህ ተመልሰህ መጥተህ ነው " ብለዋክ።
ማዕከላዊ ጎንደር ታች አርማጭሆ ከሶረቃ እስከ ሳንጃ፣ ፈረስ መግሪያ ፣ ' ኢትዮጵያ ካርታ ' የሚባለው አካባቢ ድረስ ለሹፌሮች አስቸጋሪ ሆኖ መቀጠሉን ገልጸው ሳንጃ እና አሽሬ ባለው የመንገድ ክፍል ከህዳር 25 እስከ አሁን ድረስ 5 ሹፌሬች እንደታገቱ ተናግረዋል።
ሃላፊው ፤ " ሰው የሹፌሮችን እገታ እና ግድያ አሁን በክልሉ ከሚታየው የጸጥታ ችግር ጋር ያያይዘዋል ነገር ግን እገታ በጠቀስናቸው አካባቢዎች 7 እና 8 ዓመት አልፎታል ሹፌርን ማገት የስራ ዘርፍ ሆኖ እየተኖረበት ነው " ሲሉ አማረዋል።
" በብዛት የሹፌሮች እገታ ያለበት አካባቢ ግጭት ያለበት አካባቢ አይደለም " ያሉት አመራሩ " ታገትን ተገደልን ብለን ስንናገር : ግጭት ወዳለበት አካባቢ እያሽከረከራቹ በመሆኑ ነው ' እየተባለ ይደበሰበሳል እንባላለንም ነገር ግን ይህ ለወንበዴ ሽፋን መስጠት ነው " ብለዋል።
በመተማ እና ጎንደር መሃል ቦና ፣ መቃ እና ግንታ አካባቢ አንድ ሹፌር እስከ 40 እና 50 ሺ ብር እንዲከፍል እንደሚገደድ አንስተው በ05/04/17 ሳይከፍሉ ያለፉ ሹፌር እና ረዳት በዚሁ አካባቢ መገደላቸውን አስታውሰዋል።
ለምንድነው የምትሰበስቡት ? ስንልም " ከምናግታቹ ብለን ነው " የሚል መልስ ይሰጠናል ብለዋል።
እገታ የሚፈጸምባቸው አካባቢዎች የፀጥታ ኃይል ካምፕ ያለበት ቢሆንም ለሹፌር ጥበቃ የሚያደርግ ሆነ ወንበዴዎችን የሚያጸዳ ሃይል እንደሌለ ተናግረዋል።
በዚህ ምክንያት በሳንጃ ሶረቃ መንገድ 2 ሺህ ብር በመክፈል በአጃቢ ሚሊሻ ለመንቀሳቀስ መገደዳቸውን ጠቅሰዋል።
በዚህ ጉዳይ ላይ የአካባቢውን የጸጥታ አመራሮች ምላሽ እንዳገኘን የምናካትት ይሆናል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
“ የጸጥታ አካላት ጥበቃ ባለማድረጋቸው ለአጃቢ እስከ 2,000 ብር ለመክፈል ተገደናል። በቀናት ብቻ ከ12 በላይ ሹፌሮች ታግተዋል ” - ማኀበሩ
የጸጥታ መደፍረስ በሹፌሮችና ተሳፋሪዎች ግድያና እገታ ማስከተሉን፣ የጸጥታ አካላት ጥበቃ ባለማድረጋቸው አሽከርካሪዎች ለአጃቢ 2,000 ለመክፈል መገደዳቸውን ጣና የአሽከርካሪዎች ማኀበር ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጸ።
“ የጸጥታ አካላት ጥበቃ ባለማድረጋቸው ለአጃቢ እስከ 2,000 ብር ለመክፈል ተገደናል። በቀናት ብቻ ከ12 በላይ ሹፌሮች ታግተዋል ” ሲልም በሁነቱ ተማሯል።
በአማራ ክልል ከገንዳውሃ ወደ ጎንደር ባለው መንገድ ረቡዕ ጥር 28 ቀን 2017 ዓ/ም አንድ ሰው ተገድሎ፣ ሁለቱ ደግሞ መቁሰላቸውን ገልጿል።
“ በአስር ቀናት ደቡብ ጎንደር 3 ሹፌሮች፣ በደባርቅ ዙሪያ 2 ረዳቶችና 6 ሹፌሮች፣ ገንዳውሃ 2 ሹፌሮች፣ አብርሃጀራ አንድ ሹፌር በታጠቁ አካላት ታግተዋል። በአብርሃጅራ ሹፌር ተተኩሶበት አምልጧል፤ ሁለት ቦቴዎችን ወቅንና ገደብዬ መካከል አግተዋቸዋል ” ነው ያለው።
ማኀበሩ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጠው ቃል በዝርዝር ምን አለ ?
“ ከአሸሬ እስከ ሶረቃ የሚያስፈራ ቦታ አለ። በፈቃድ ለታጠቁ የአካባቢው ሰዎች 2,000 ብር እየከፈልን ነው የምናልፈው። በቅርቡ አንድ አጃቢ አጋች መትቷል ሹፌር ሊያግት ሲል ወርዶ ተኮሰበት።
ጨንቆን ነው እንጂ ይሄ ሂደት ደግሞ መጥፎ ነው። ህግ ባለመከበሩ ምክንያት ለሹፌሮች እለታዊ መፍትሄ ሆኗል። ግን የአጃቢነት ስራ እየሰሩ ያሉ ሰዎች እንዴት ነው የአካባቢ ሰላም እንዲመለስ የሚፈልጉት?
ስለዚህ እገታ ያለባቸው ቦታዎች ይታወቃሉ። በአርማጭሆ በኩል ከከተማው አፍንጫ ስር ከ10 ጊዜ በላይ እገታ ተፈጽሞበት ቦታው ላይ የጸጥታ አካል አይቀመጥም።
የጸጥታ ዘርፉ ትኩረት ቢሰጥ ችግሩን መቆጣጠር ይችላል። ምክንያቱም በአንድ አጃቢ ከፍለን የምናልፈው አካባቢ ነው። መዝረፊያ በሮች የሚታወቁ ናቸው” ብሏል።
ለአጃቢ ከመክፈል በተጨማሪ ሹፌሮች ከጸጥታ ስጋት አንጻር በ100ዎች የሚቆጠሩ ኪሎ ሜትሮችን ዙሪያ ጥምጥም እንዲጓዙ እየተገደዱ መሆኑም ተገልጿል።
ማኀበሩ በመንገዱ ዙሪያ ምን አለ ?
“ በደባርቅ በኩል ባለው መንገድ ከደብረ ታቦር ጋይንት መንገዱ ችግር ትልቅ አለበት። መንገዱ አማራ ክልል ከጅቡቲ የሚገናኝበት ነው። ማደበሪያ የሚገባው በጋይንት ነው። በሚሌ፣ ጭፍራ፣ ሃራ፣ ወልዲያ አድርጎ በደብረ ታቦር አድርጎ ይመጣል።
ግን ማዳበሪያ የሚጭኑ ተሽከሪካሪዎች በዚህ አመት በጸጥታው ችግር ምክንያት ተጨማሪ መንገድ እየተጓዙ በአዲስ አበባ በኩል ለመምጣት ተገደዋል። ከደጀን በእጀባ ነው የሚመጡት ወደ ጎጃምና ጎንደር ጭምር።
በጸጥታው ችግር ተሽከርካሪዎች ከ500 ኪሎ ሜትር በላይ ተጨማሪ መንገድ ለመሄድ ተገደዋል። ይህ ለአርሶ አደሩም ጉዳት አለው። 1,950 ብር ነው አንድ ኩንታል ማዳበሪያ ከጅቡቲ የሚመጣው። ትራንስፓርት ኮስቱ 1,900 ብር ሲሆን፣ የማዳበሪያው ዋጋ ይንራል።
በጋይንት ቦቴዎች ይሄዳሉ። ጭነው ይመጡና በጸጥታው ችግር መመለሻ ሲያጡ በደባርቅ፣ ዛሪማ፣ በሽሬ፣ ከሽሬ መቀሌ፣ ከመቀሌ አብዓላ አድርገው በአፍዴራ ይወጣሉ። ይሄ ማለት ከ600 በላይ ተጨማሪ ኪሎ ሜትር ይጓዛሉ።
በጎንደር መተማ መንገድ በመተማ በኩል ነው ኢምፖርት ኤክስፖርት የሚገባው። የመተማ ጎንደርን መንገድ የጸጥታ ችግሩን በመፍራት አሽከርካሪዎች በአብርሃጅራ ዙረው እየገቡ ነው።
180 ኪሎ ሜትር ሲጓዙ የነበሩ አሽከርካሪዎች 140 ኪሎ ሜትር በመጨመር 320 ኪሎ ሜትር ይጓዛሉ ” ብሏል።
(ስለጉዳዩ ለጸጥታ አካላት ጥያቄ የምናቀርብ ይሆናል)
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM