TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.3K photos
1.5K videos
211 files
4.1K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#AhaduBank

አሐዱ ባንክ ሐምሌ 9 ቀን 2014 ዓ.ም ሥራውን በይፋ ይጀምራል።

ይህ አስመልክቶ ባንኩ ዛሬ መግለጫ ሰጥቶ ነበር።

የባንኩ የቦርድ ሰብሳቢ አቶ አንተነህ ሰብስቤ ፤ 10 ሺህ በሚደርሱ ባለአክሲዮኖችንና በ564 ሚሊዮን የተከፈለ ካፒታል እና በ702 ሚሊዮን በተፈረመ ካፒታል ተዋቅሯል ብለዋል።

ሀላፊው እስከ መስከረም 30 ቀን 2015 ዓ/ም የቅርንጫፎቹን ብዛት 50 እደሚያደርስም ተናግረዋል።

ባንኩ ፦

➡️ ከሚያቀርበው ብድር እስከ 15 በመቶ የሚሆውን ለስራ ፈጣሪዎች እና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ማቅረቡ ፤

➡️ ከተለመደዉ በሰራተኛ ከታገዘ የቅርንጫፍ አገልግሎት በተጓዳኝ ደንበኞች በራሳቸዉ የዲጂታል አገልግሎት የሚያገኙበት የቅርንጫፍ ዉስጥ አገልግሎት አደረጃጀት ማመቻቸቱ ፤

➡️ የገጠር የባንክ አገልግሎትን ለአርሶና አርብቶ አደሮች፣ የገበሬ ማህበራት ለማዳረስ መዘጋጅቱ ፤

➡️ የውስጥ አሰራሩን ወረቀት አልባ ማድረጉ ፤

➡️ ደንበኞች ካሉበትና ቦታ ሆነዉ ራሳቸዉን የባንኩ ደንበኛ ማድረግ የሚችሉበትን አሰራር ማምጣቱ ልዩ ያደርገዋል ተብሏል።

ባንኩ ከሀምሌ 2 እስከ ሀምሌ 7 /2014 የተለያዩ ማህበራዊ ግዴታዎች እንደሚያከናውን የገለፀ ሲሆን " አንድ ቅርንጫፍ ለአንድ ልጅ " በሚል ባንኩ በሚከፍታቸዉ ቅርንጫፎች ቁጥር ልክ ድጋፍ እና እገዛ ለሚያስፈልጋቸዉ ልጆች ዓመታዊ ወጪያቸዉን እንደሚሸፍን ገልጿል።

ባንኩ በተጨማሪም አዲሱ መለያ ሎጎውንም በይፋ አስተዋውቋል።

@tikvahethiopia