#AhaduBank
አሐዱ ባንክ ሐምሌ 9 ቀን 2014 ዓ.ም ሥራውን በይፋ ይጀምራል።
ይህ አስመልክቶ ባንኩ ዛሬ መግለጫ ሰጥቶ ነበር።
የባንኩ የቦርድ ሰብሳቢ አቶ አንተነህ ሰብስቤ ፤ 10 ሺህ በሚደርሱ ባለአክሲዮኖችንና በ564 ሚሊዮን የተከፈለ ካፒታል እና በ702 ሚሊዮን በተፈረመ ካፒታል ተዋቅሯል ብለዋል።
ሀላፊው እስከ መስከረም 30 ቀን 2015 ዓ/ም የቅርንጫፎቹን ብዛት 50 እደሚያደርስም ተናግረዋል።
ባንኩ ፦
➡️ ከሚያቀርበው ብድር እስከ 15 በመቶ የሚሆውን ለስራ ፈጣሪዎች እና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ማቅረቡ ፤
➡️ ከተለመደዉ በሰራተኛ ከታገዘ የቅርንጫፍ አገልግሎት በተጓዳኝ ደንበኞች በራሳቸዉ የዲጂታል አገልግሎት የሚያገኙበት የቅርንጫፍ ዉስጥ አገልግሎት አደረጃጀት ማመቻቸቱ ፤
➡️ የገጠር የባንክ አገልግሎትን ለአርሶና አርብቶ አደሮች፣ የገበሬ ማህበራት ለማዳረስ መዘጋጅቱ ፤
➡️ የውስጥ አሰራሩን ወረቀት አልባ ማድረጉ ፤
➡️ ደንበኞች ካሉበትና ቦታ ሆነዉ ራሳቸዉን የባንኩ ደንበኛ ማድረግ የሚችሉበትን አሰራር ማምጣቱ ልዩ ያደርገዋል ተብሏል።
ባንኩ ከሀምሌ 2 እስከ ሀምሌ 7 /2014 የተለያዩ ማህበራዊ ግዴታዎች እንደሚያከናውን የገለፀ ሲሆን " አንድ ቅርንጫፍ ለአንድ ልጅ " በሚል ባንኩ በሚከፍታቸዉ ቅርንጫፎች ቁጥር ልክ ድጋፍ እና እገዛ ለሚያስፈልጋቸዉ ልጆች ዓመታዊ ወጪያቸዉን እንደሚሸፍን ገልጿል።
ባንኩ በተጨማሪም አዲሱ መለያ ሎጎውንም በይፋ አስተዋውቋል።
@tikvahethiopia
አሐዱ ባንክ ሐምሌ 9 ቀን 2014 ዓ.ም ሥራውን በይፋ ይጀምራል።
ይህ አስመልክቶ ባንኩ ዛሬ መግለጫ ሰጥቶ ነበር።
የባንኩ የቦርድ ሰብሳቢ አቶ አንተነህ ሰብስቤ ፤ 10 ሺህ በሚደርሱ ባለአክሲዮኖችንና በ564 ሚሊዮን የተከፈለ ካፒታል እና በ702 ሚሊዮን በተፈረመ ካፒታል ተዋቅሯል ብለዋል።
ሀላፊው እስከ መስከረም 30 ቀን 2015 ዓ/ም የቅርንጫፎቹን ብዛት 50 እደሚያደርስም ተናግረዋል።
ባንኩ ፦
➡️ ከሚያቀርበው ብድር እስከ 15 በመቶ የሚሆውን ለስራ ፈጣሪዎች እና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ማቅረቡ ፤
➡️ ከተለመደዉ በሰራተኛ ከታገዘ የቅርንጫፍ አገልግሎት በተጓዳኝ ደንበኞች በራሳቸዉ የዲጂታል አገልግሎት የሚያገኙበት የቅርንጫፍ ዉስጥ አገልግሎት አደረጃጀት ማመቻቸቱ ፤
➡️ የገጠር የባንክ አገልግሎትን ለአርሶና አርብቶ አደሮች፣ የገበሬ ማህበራት ለማዳረስ መዘጋጅቱ ፤
➡️ የውስጥ አሰራሩን ወረቀት አልባ ማድረጉ ፤
➡️ ደንበኞች ካሉበትና ቦታ ሆነዉ ራሳቸዉን የባንኩ ደንበኛ ማድረግ የሚችሉበትን አሰራር ማምጣቱ ልዩ ያደርገዋል ተብሏል።
ባንኩ ከሀምሌ 2 እስከ ሀምሌ 7 /2014 የተለያዩ ማህበራዊ ግዴታዎች እንደሚያከናውን የገለፀ ሲሆን " አንድ ቅርንጫፍ ለአንድ ልጅ " በሚል ባንኩ በሚከፍታቸዉ ቅርንጫፎች ቁጥር ልክ ድጋፍ እና እገዛ ለሚያስፈልጋቸዉ ልጆች ዓመታዊ ወጪያቸዉን እንደሚሸፍን ገልጿል።
ባንኩ በተጨማሪም አዲሱ መለያ ሎጎውንም በይፋ አስተዋውቋል።
@tikvahethiopia