TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.2K photos
1.5K videos
211 files
4.1K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#SafaricomEthiopia ሳፋሪኮም በሃምሌ ወር በድሬዳዋ አገልግሎት ይጀምራል። በሳፋሪኮም ኢትዮጵያ የኤክስተርናል አፌርስ እና ሬጉላተሪ ዋና ኃላፊ ማቲው ሀሪሰን ሀርቪ ፦ " ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ኔትወርኩን በማስጀመር አገልግሎቶችን ለመስጠት እየተዘጋጀ ነው። ይህንንም በድሬዳዋ በሐምሌ ወር 2014 ዓ/ም በመጀመር በቀጣይ ወራት በሁሉም የኢትዮጵያ ክፍሎች የሚገኙ 24 ከተሞች የሚስፋፋ ይሆናል።…
#SafaricomEthiopia

ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ እስካሁን ምን ምን ስራ ሰራ ?

በሰኔ 2013 ዓ.ም የቴሌኮም አገልግሎት ሰጪነት ፍቃድ ከተሰጠው ጀምሮ ፦

👉 የኔትወርክ እና የመሰረተ ልማቶች ግንባታዎች ላይ በማተኮር የሞባይል ሬድዮ ታወሮችን፤ ብሔራዊ የማሰራጫ ኔትወርኮን እና ለዓለም አቀፍ ግንኙነት የሚሆኑ ስምምነቶችን ጨምሮ መሠረተ ልማቶችን ገንብቷል።

👉 የቴሌኮም አገልግሎት ሰጪነት ፍቃድን ጨምሮ ለልዩ ልዩ ሥራዎች 1 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር ኢንቨስት አድርጓል።

👉 ከ300 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር በላይ ዋጋ የሚያወጡ መገልገያዎችን ወደ አገር ውስጥ አስገብቷል።

👉 ኮር ኔትወርዎርኩ፣ ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ (1) እንዲሁም ምርቶችን እና አገልግሎቶችን ማበልፀግ ጀምሯል።

👉 የደንበኞች ጥሪ ማስተናገጃን አደራጅቷል።

👉 ሁለት የመረጃ ቋት ማዕከላት (Data Centers) ገንብቷል።

👉 በቅርቡ የመሠረተ ልማት መጋራት እና #ከአንዱ_ወደ_ሌላው_ለመደወል የሚያስችሉ ስምምነቶችን ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር ተፈራርሞ ትግበራው በጥሩ መልኩ እየተካሔደ ነው።

#SafaricomEthiopia

@tikvahethiopia