TIKVAH-ETHIOPIA
#AddisAbaba የጋራ መኖሪያ ቤቶች ዕጣ የማውጣት ስነስርዓት ወደ ዓርብ ተሻገረ። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ14ኛ ዙር የጋራ መኖርያ ቤቶች እጣ አወጣጥ ስነስርዓት ነገ ሰኔ 30 ቀን 2014 ዓ/ም እንደሚካሄድ ገልጾ ነበር። ነገር ግን የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በጠራው ስብሰባ ምክንያት የእጣ አወጣጥ ስነስርዓቱ ወደ ዓርብ ሃምሌ 1 ቀን 2014 የተዛወረ መሆኑን አስተዳደሩ አሳውቋል። የአዲስ…
#አጭር_ማስታወሻ
ነገ ጥዋት በአዲስ አበባ ፤ የጋራ መኖሪያ ቤቶች ዕጣ ይወጣል፤ ከዚህ ጋር ተያይዞ አጭር የመረጃ ማስታወሻ ፦
⮕ ነገ የሚካሄደው የ3ኛ ዙር የ40/60 እና 14ኛ ዙር የ20/80 የጋራ መኖሪያ ቤቶች ዕጣ አወጣጥ ስነስርኣት ነው።
⮕ አጠቃላይ 25 ሺህ 491 የጋራ መኖሪያ ቤቶች ለነዋሪዎች በዕጣ ይተላለፋሉ።
⮕ በ20/80 ፕሮግራም 18 ሺ 648 ፤ በ40/60 መርኃ ግብር 6 ሺህ 843 ቤቶች በድምሩ 25 ሺህ 491 ቤቶች ለነዋሪዎች በእጣ ይተላለፋሉ።
⮕ በዕጣው የሚካተቱት በ1997 እና በ2005 ዓ.ም ተመዝግበው እስከ የካቲት 21 ቀን 2014 ዓ.ም ድረስ በአማካይ ለ60 ወራት የቆጠቡ የ20/80 እና 40 በመቶ እና ከዚያ በላይ የቆጠቡ የ40/60 ቤት ፈላጊዎች ናቸው።
⮕ 79 ሺ 794 ከሚሆኑ ቤት ፈላጊዎች መካከል 25 ሺህ 491 የሚሆኑት ዕድለኞች በነገው የዕጣ አወጣጥ ስነ-ስርዓት ይለያሉ።
⮕ በ40/60 የቤት ልማት ፕሮግራም ለባለዕድለኞች የሚተላለፉ ቤቶች የሚገኙት አያት 2፣ ቦሌ በሻሌ፣ ቡልቡላ ሎት ነው።
⮕ በ20/80 ለባለዕድለኞች የሚተላለፉ ቤቶች የሚገኙት በረከት፣ ቦሌ አራብሳ ሳይት 3 ሳይት 5 እና 6 ወታደር፣ የካ ጣፎ፣ ጀሞ ጋራ፣ ጎሮ ስላሴ ፣ ፉሪ ሀና እና ፋኑኤል ነው።
⮕ የመንግስት ሰራተኛ 20 በመቶ ፣ ሴቶች 30 በመቶ ፣ የአካል ጉዳተኞች 5 በመቶ በእጣው ተጠቃሚ ይሆናሉ።
(ሙሉ መረጃው ትላንት የአዲስ አበባ ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ ከተናገሩት የተወሰደ ነው/ENA)
@tikvahethiopia
ነገ ጥዋት በአዲስ አበባ ፤ የጋራ መኖሪያ ቤቶች ዕጣ ይወጣል፤ ከዚህ ጋር ተያይዞ አጭር የመረጃ ማስታወሻ ፦
⮕ ነገ የሚካሄደው የ3ኛ ዙር የ40/60 እና 14ኛ ዙር የ20/80 የጋራ መኖሪያ ቤቶች ዕጣ አወጣጥ ስነስርኣት ነው።
⮕ አጠቃላይ 25 ሺህ 491 የጋራ መኖሪያ ቤቶች ለነዋሪዎች በዕጣ ይተላለፋሉ።
⮕ በ20/80 ፕሮግራም 18 ሺ 648 ፤ በ40/60 መርኃ ግብር 6 ሺህ 843 ቤቶች በድምሩ 25 ሺህ 491 ቤቶች ለነዋሪዎች በእጣ ይተላለፋሉ።
⮕ በዕጣው የሚካተቱት በ1997 እና በ2005 ዓ.ም ተመዝግበው እስከ የካቲት 21 ቀን 2014 ዓ.ም ድረስ በአማካይ ለ60 ወራት የቆጠቡ የ20/80 እና 40 በመቶ እና ከዚያ በላይ የቆጠቡ የ40/60 ቤት ፈላጊዎች ናቸው።
⮕ 79 ሺ 794 ከሚሆኑ ቤት ፈላጊዎች መካከል 25 ሺህ 491 የሚሆኑት ዕድለኞች በነገው የዕጣ አወጣጥ ስነ-ስርዓት ይለያሉ።
⮕ በ40/60 የቤት ልማት ፕሮግራም ለባለዕድለኞች የሚተላለፉ ቤቶች የሚገኙት አያት 2፣ ቦሌ በሻሌ፣ ቡልቡላ ሎት ነው።
⮕ በ20/80 ለባለዕድለኞች የሚተላለፉ ቤቶች የሚገኙት በረከት፣ ቦሌ አራብሳ ሳይት 3 ሳይት 5 እና 6 ወታደር፣ የካ ጣፎ፣ ጀሞ ጋራ፣ ጎሮ ስላሴ ፣ ፉሪ ሀና እና ፋኑኤል ነው።
⮕ የመንግስት ሰራተኛ 20 በመቶ ፣ ሴቶች 30 በመቶ ፣ የአካል ጉዳተኞች 5 በመቶ በእጣው ተጠቃሚ ይሆናሉ።
(ሙሉ መረጃው ትላንት የአዲስ አበባ ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ ከተናገሩት የተወሰደ ነው/ENA)
@tikvahethiopia