TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.8K photos
1.61K videos
216 files
4.36K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
አዲስ አበባ‼️

በአዲስ አበባ በህገወጥ መንገድ የውጭ ሀገር ገንዘቦችን #በሚመነዝሩ ላይ በተደረገ ድንገተኛ ፍተሻ ከ2 ሚሊየን የሚበልጥ የኢትዮጵያ ብር እና የተለያዩ ሀገራት ገንዘቦችን #መያዙን የከተማዋ ፖሊስ ኮሚሽን ገለፀ።

ታህሳስ 26 እና 27 ቀን 2011 ዓመተ ምህረት በቂርቆስ ክፍለ ከተማ በተለምዶ ኢትዮጵያ ሆቴልና ጋንዲ አካባቢ የብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት እና የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን በጋራ ባደረጉት ድንገተኛ ፍተሻ ገንዘቦቹን መያዛቸውን ኮሚሽኑ ለfbc በላከው መግለጫ አስታውቋል።

ከዚህ በፊት በአካባቢዎቹ በተደረገ ድንገተኛ ፍተሻ ለምንዛሪ የተዘጋጁ የተለያዩ ሀገራት ገንዘቦችና የኢትዮጵያ ብር መያዙን ኮሚሽኑ በመግለጫው አስታውሷል።

ሁለቱ ተቋማት ባደረጉት ድንገተኛ ፍተሻ ተጠርጥረው የተያዙ አምስት ግለሰቦች በፖሊስ ቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተደረገባቸው መሆኑን ነው ያስታወቀው።
የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ህገወጥ የገንዘብ ዝውውርን ለመግታት ከባለድርሻ አካላት እና ከህብረተሰቡ ጋር በመሆን ተግባሩን እንደሚቀጥል በመግለፅ፥ የከተማው ነዋሪ ይህ ጥረት እንዲሳካ የበኩሉን አስተዋጽኦ እንዲወጣ ጠይቋል።

ምንጭ፦ ፋና ብሮድካሥቲንግ
@tsegabwolde @tikvahethiopia