TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
61.3K photos
1.55K videos
215 files
4.25K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#Asossa | የተባበሩት ማደያ ንግድ ፈቃድ ተሰረዘ።

በህገ ወጥ መንገድ ነዳጅና ቤኒዚን ሲያሰራጭ በተገኘው የተባበሩት ማደያ ላይ እርምጃ መወሰዱን የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ንግድና ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ አስታወቀ።

የማደያው ንግድ ፍቃድ ሙሉ በሙሉ የተሰረዘ መሆኑንም ቢሮው ገልጿል፡፡

ላለፉት ጊዜያት ከህጋዊ አሰራር ባፈነገጠ መልኩ ሲሰራ የነበረው የተባበሩት ማደያ ወደ ህጋዊ መስመር ገብቶ ህብረተሰቡን እንዲያገልገል በቃልና በጹሁፍ ማስጠንቀቂ ቢሰጠውም ማስጠንቀቂያውን ወደ ጎን በመተው በህገ-ወጥነት በመቀጠሉ የተነሳ የንግድ ፍቃዱ ሙሉ በሙሉ መሰረዙን ቢሮው አሳውቋል።

ከዚህ በፊት ለታፍ ማደያም ማስጠንቀቂያ መስጠቱ የተገለፀ ሲሆን ቢሮው በተሰጠው ስልጣን መሰረት በህገ-ወጦች ላይ የሚወስደውን ዕርምጃ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጿል።

አሶሳ ውስጥ 7 ማዳያዎች ያሉ ሲሆን በአገልግሎታቸው ህብረተሰቡን ማርካት አልቻሉም ተብሏል።

#BGMMA

@tikvahethiopia