TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.8K photos
1.61K videos
216 files
4.36K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#የህግ_ጉዳይ

ከክልል ፍርድ ቤቶች እስከ ፌዴሬሽን ደርሶ ወደ ከፍተኛ የተመለሰው የንብረት ክርክር መጨረሻ ምን ይሆን ?

(በሪፖርተር ጋዜጣ - አሳዬ ቀፀላ)

ከ10 ዓመታት በፊት ሐምሌ 1 ቀን 2006 ዓ.ም. በኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ ሸዋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ነበር ክርክሩ የተጀመረው።

የክርክሩ መነሻ፣ በኦሮሚያ ክልል በቢሾፍቱ ከተማ በሚገኘው ጌትእሸት ዲተርጀንት ማምረቻና ማሸጊያ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ኩባንያ ሽያጭ ነው፡፡

ድርጅቱ የእነ ጌታቸው እሸቱ (ኢንጂነር) አራት ሰዎች ሲሆን፣ ጠቅላላ የቦታው ስፋት 11,305 ካሬ ሜትር ነው፡፡

የዲተርጀንት ማምረቻና ማሸጊያ ፋብሪካው ያረፈው በ3,015 ካሬ ሜትር ላይ ሲሆን፣ ስመ ሀብቱ የተመዘገበው በጌታቸው እሸቴ (ኢንጂነር) ስም ነው፡፡

ቀሪው 8,290 ካሬ ሜትር ደግሞ ጅምር ግንባታ ያለበት ሆኖ፣ ስመ ሀብቱ (ካርታው) የተመዘገበው በጌትእሸት ዲተርጀንት ማምረቻና ማሸጊያ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር ስም ነው፡፡

ፋብሪካውንና ጅምር ግንባታ ያረፈበትን (በሁለት የተለያዩ ስሞች የተመዘገቡ ይዞታዎች) ሁለት ይዞታዎች እነ ጌታቸው (ኢንጂነር) (አራት ሰዎች) ለእነ ዶ/ር በዕውቀቱ ታደሰ ከአሥር ዓመታት በፊት ኅዳር 18 ቀን 2005 ዓ.ም. በ22,500,000 ብር ሸጠውላቸዋል፡፡

የሽያጭና የግዥ ውሎች የኢትዮጵያ ፍትሐ ብሔር ሕጎችን ሒደት በጠበቀ ሁኔታ ተፈጽመዋል፡፡

ያንብቡ : https://telegra.ph/Justice-08-06

@tikvahethiopia
👍308🙏11👎8🥰87👏6😢6