TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.8K photos
1.61K videos
216 files
4.36K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#ድርድር ጠ/ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ስለ #ድርድር ምንድነው ያሉት ? " ከኦነግ ሸኔ ጋር የሚደረገው ድርድር ከነገ ወዲያ በታንዛኒያ ይጀመራል። ይህንን ድርድር የኢትዮጵያ መንግሥት እና ህዝብ አብዝቶ ይፈልገዋል። በዚህ ድርድር የሚሳተፉ ወገኖች ሁሉ የዛሬዋን ቀን እያሰቡ ፣ ከግጭት፣  ከጦርነት እንደማናተርፍ አውቀው ህግ እና ስርዓት ተከትለን ይቅር ተባብለን ሀገራችንን በጋራ ማነፅ እና መገንባት…
#ታንዛኒያ

የኢትዮጵያ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ዛሬ #ታንዛኒያ ገብተዋል።

አቶ ደመቀ በ4 የአፍሪካ ሀገራት ጉብኝት ያደርጋሉ የተባለ ሲሆን የመጀመሪያውን ጉብኝታቸውን በታንዛኒያ ጀምረዋል።

ከታንዛኒያ በመቀጠል በኮሞሮስ ፣ ቡሩንዲ እና ዩጋንዳ ጉብምት ያደርጋሉ ተብሏል።

አቶ ደመቀ ዛሬ ታንዛኒያ ከገቡ በኃላ #በዛንዚባር የሚገኘውን የአፄ ኃይለሥላሴ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤትን ጎብኝተዋል።

አቶ ደመቀ መኮንን ወደ ታንዛኒያ ለጉብኝት ያመሩት ትላንት የኢፌዴሪ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ " ኦነግ ሸኔ " ሲሉ ከተጠሩት የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት ጋር መንግሥት ነገ በታንዛኒያ ድርድር እንደሚጀምር ካሳወቁ በኃላ ነው።

አቶ ደመቀ የታንዛኒያ ጉዟቸው በ4 የአፍሪካ ሀገራት ለሚያደርጉት ጉብኝት የመጀመሪያ ሀገር ከመሆኑ በዘለለ ይደረጋል ከተባለው ድርድር ጋር ይገናኝ እንደሆነ ወይም በዚህ ድርድር ላይ ይገኙ/አይገኙ የታወቀም ሆነ ይፋ የተደረገ መረጃ #የለም

@tikvahethiopia
👍629👎45057🕊41🙏13🥰8😢8😱4