TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.2K photos
1.5K videos
211 files
4.1K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#CocaCola

ኮካ ኮላ ኩባንያ መንግሥት ለሽያጭ ከሚያቀርባቸው የስኳር ፋብሪካዎች መካከል የተወሰኑትን ለመግዛት መዘጋጀቱን አስታውቋል፡፡ የግዥ ፍላጎቱን ለመንግሥት በማስታወቅ የጨረታ ሒደቱ ይፋ የሚደረግበትን ጊዜ እየተጠባበቀ መሆኑ ገልጿል፡፡

(ሪፖርተር ጋዜጣ)

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#CocaCola

ዛሬ በኦሮሚያ ክልል በሰበታ ከተማ 100 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር የፈጀ የኮካኮላ ምርት ማምረቻ ፋብሪካ ተመርቋል።

ተገንብቶ የተጠናቀቀው የማምረቻ ፍብሪካ ኮካ-ኮላ ቤቭሬጅስ አፍሪካ-ኢትዮጵያን በአመት 100 ሚሊየን በላይ እሽግ ለስላሳ ለማምረት ያስችለዋል፡፡

ከዚህ በተጨማሪ የማምረቻ ግብዓቶችን እንደ የፕላስቲክ ጠርሙስ፣ የፕላስቲክ ጠርሙስ ክዳን እና ሌሎች የምርት ግብአቶችን በማምረት ከውጪ ወደ ሀገሪቷ የሚገቡ ምርቶችን በመቀነስ እንደ " ሚኒት ሜድ ጁስ " የመሳሰሉ አዳዲስ ምርቶችን ሀገር ውስጥ በማምረት ጠቅላላ ምርት ለመጨመር የሚረዳ ነው፡፡

ኮካ ኮላ " ሚኒት ሜድ " የተሰኙ የጁስ ምርቶቹን ወደ ኢትዮጵያ ገበያ እያመጣ መሆኑ ዛሬ በነበረው የፋብሪካው ምረቃ ስነስርአት ላይ ተሰምቷል።

የሚመረቱት የግብአት ምርቶቹ የሲ.ሲ ቢ.ኤን ፍላጎት ከማሳካት በተጨማሪ ለውጪ ገበያ በማቅረብ የውጨ ምንዛሬን ሀገሪቷ እንድታገኝ እና በዘርፉ ያለውን የምርት እጥረት ለመፍታት ለሀገር ውስጥ ገበያ ለማቅረብም ፋብሪካው እቅድ ይዞ እየሰራ ይገኛል፡፡

መረጃው የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር እና ካፒታል ነው።

@tikvahethiopia