TIKVAH-ETHIOPIA
በፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን ቃሊቲ ከፍተኛ ጥበቃ ማረሚያ ማዕከል የቀጠሮ እስረኛ የነበሩት ሜ/ጄነራል ገ/መድህን ፍቃዱ (ወዲ ነጮ) በዛሬው ዕለት ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸው ተሰምቷል። በፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን ይፋ በተደረገው መረጃ ሜ/ጄነራል ገ/መድህን ከረፋዱ 3፡30 አካባቢ በቤተሰብ ጥየቃ ሠዓት ባለቤታቸው እና ልጃቸው አስጠርተዋቸው እያወሩ እያለ በድንገት ይወድቃሉ። ወዲያውኑ ከቤተሰቦቻቸው…
ፎቶ : የቃሊቲ ከፍተኛ ጥበቃ ማረሚያ ማዕከል የቀጠሮ እስረኛ የነበሩት ሜጀር ጄነራል ገ/መድህን ፍቃዱ (ወዲ ነጮ) ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸው መገለፁ ይታወሳል።
የሜ/ጄነራል ገ/መድህን ስርዓተ ቀብር ዛሬ ወዳጅ ዘመዶቻቸው በተገኙበት በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ስላሴ ካቴድራል ተፈፅሟል።
የኢትዮጵያ መንግስት ሜጀር ጀነራል ገብረመድህን ፈቃዱን (ወዲ ነጮ) ከሰሜን ኢትዮጵያው ጦርነት ጋር በተያያዘ በአገር ክህደት ወንጀል ነበር በቁጥጥር ስር ያዋላቸው።
ጥቅምት 24/2013 ዓ/ም ላይ የሰሜን ዕዝ ከማዕከል ጋር የሚኖረው የመገናኛ ሥርዓት እንዲቋረጥ በማድረግ የህወሃት ቡድን ጥቃት እንዲፈፅም አመቻችተዋል ተብለው ነበር ከነጓዶቻቸው በቁጥጥር ስር ውለው የነበሩት።
ሜ/ጄነራሉ ከቀናት በፊት ታስረውበት በሚገኘው ቃሊቲ ማረሚያ ቤት በቤተሰብ ጥየቃ ሠዓት ባለቤታቸው እና ልጃቸው አስጠርተዋቸው እያወሩ እያለ በድንገት እንደወደቁ በኃላም ወደ ህክምና ቦታ ቢወሰዱም ህይታቸው ማለፉ መግለፁ አይዘነጋም።
ይህን ተከትሎ የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን የሜጀር ጀነራል ገብረመድህን ፈቃዱ (ወዲ ነጮ) አስክሬን ለተጨማሪ ምርመራ ወደ ህክምና ተቋም መላኩን እና ውጤቱ እንደታወቀ እንደሚገለፅ ገልጾ የነበር ሲሆን እስካሁን በይፋ የተሰጠ መረጃ የለም።
@tikvahethiopia
የሜ/ጄነራል ገ/መድህን ስርዓተ ቀብር ዛሬ ወዳጅ ዘመዶቻቸው በተገኙበት በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ስላሴ ካቴድራል ተፈፅሟል።
የኢትዮጵያ መንግስት ሜጀር ጀነራል ገብረመድህን ፈቃዱን (ወዲ ነጮ) ከሰሜን ኢትዮጵያው ጦርነት ጋር በተያያዘ በአገር ክህደት ወንጀል ነበር በቁጥጥር ስር ያዋላቸው።
ጥቅምት 24/2013 ዓ/ም ላይ የሰሜን ዕዝ ከማዕከል ጋር የሚኖረው የመገናኛ ሥርዓት እንዲቋረጥ በማድረግ የህወሃት ቡድን ጥቃት እንዲፈፅም አመቻችተዋል ተብለው ነበር ከነጓዶቻቸው በቁጥጥር ስር ውለው የነበሩት።
ሜ/ጄነራሉ ከቀናት በፊት ታስረውበት በሚገኘው ቃሊቲ ማረሚያ ቤት በቤተሰብ ጥየቃ ሠዓት ባለቤታቸው እና ልጃቸው አስጠርተዋቸው እያወሩ እያለ በድንገት እንደወደቁ በኃላም ወደ ህክምና ቦታ ቢወሰዱም ህይታቸው ማለፉ መግለፁ አይዘነጋም።
ይህን ተከትሎ የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን የሜጀር ጀነራል ገብረመድህን ፈቃዱ (ወዲ ነጮ) አስክሬን ለተጨማሪ ምርመራ ወደ ህክምና ተቋም መላኩን እና ውጤቱ እንደታወቀ እንደሚገለፅ ገልጾ የነበር ሲሆን እስካሁን በይፋ የተሰጠ መረጃ የለም።
@tikvahethiopia
#ህንድ
በሰሜን ህንድ በቡድን ጾታዊ ጥቃት ተፈጽሞብኛል ብላ ለመክሰስ ፖሊስ ጣቢያ የሄደችው የ13 ዓመት ታዳጊ በፖሊስ መደፈሯ ቁጣን ቀስቅሷል።
አሁን ላይ ታዳጊዋን የደፈረው ፖሊስ ከስራው የተገደ ሲሆን ፤ በቁጥጥር ስርም ውሏል።
ታዳጊዋ ባለፈው ወር በ4 ወንዶች መደፈሯን ተናግራለች፡፡ የታዳጊዋ የመደፈር ዜና በመላ ህንድ ትልቅ ቁጣ ቀስቅሶ ነበር።
የታዳጊዋ ወላጅ ባቀረቡት ክስ፤ አራቱ ወንዶች ሴት ልጃቸውን የደፈሯት ለአራት ቀናት ያክል ማደያ ወደ ተባለ ግዛት ወስደው እቤት ውስጥ በመዝጋት ነበር ብሏል፡፡
አራቱም ወንዶች ለአራት ቀናት ከደፈሯት በኋላ ወደ መኖሪያ አከባቢዋ መልሰው ጥለዋት መሰወራቸውንም ነው ወላጅ አባቷ የገለጹት፡፡
በሚቀጠለው ቀን ታዳጊዋ ከአክስቷ ጋር በመሆን ክስ ለመመስረት ወደ ፖሊስ ጣቢያ የሄደች ቢሆንም፤ በፖሊስ ጣቢያው ኃላፊ እንደተደፈረች ኤን-ዲቲ-ቪ የተባለ የህንድ ቻናል ዘግቧል፡፡
ዜናውን ተከትሎ በግዛቱ ያሉትን ህጎች ጥያቄ ውስጥ መግባታቸው በመነገር ላይ ያለው፡፡
የህንድ ኮንግረስ ፓርቲ ከፍተኛ አመራር የሆኑት ፕሪያንካ ጋንዲ በትዊተር ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሁፍ ‘‘ ፖሊስ ጣቢያዎች ለሴቶች ደህንነት አስተማማኝ ካልሆኑ ፤ ሴቶች ታዲያ የት ሄደው ይከሳሉ? ’’ የሚል ትችት አዘል መልእክት አጋርቷል፡፡
ምንጭ፦ አል ዓይን ኒውስ /ND TV
@tikvahethiopia
በሰሜን ህንድ በቡድን ጾታዊ ጥቃት ተፈጽሞብኛል ብላ ለመክሰስ ፖሊስ ጣቢያ የሄደችው የ13 ዓመት ታዳጊ በፖሊስ መደፈሯ ቁጣን ቀስቅሷል።
አሁን ላይ ታዳጊዋን የደፈረው ፖሊስ ከስራው የተገደ ሲሆን ፤ በቁጥጥር ስርም ውሏል።
ታዳጊዋ ባለፈው ወር በ4 ወንዶች መደፈሯን ተናግራለች፡፡ የታዳጊዋ የመደፈር ዜና በመላ ህንድ ትልቅ ቁጣ ቀስቅሶ ነበር።
የታዳጊዋ ወላጅ ባቀረቡት ክስ፤ አራቱ ወንዶች ሴት ልጃቸውን የደፈሯት ለአራት ቀናት ያክል ማደያ ወደ ተባለ ግዛት ወስደው እቤት ውስጥ በመዝጋት ነበር ብሏል፡፡
አራቱም ወንዶች ለአራት ቀናት ከደፈሯት በኋላ ወደ መኖሪያ አከባቢዋ መልሰው ጥለዋት መሰወራቸውንም ነው ወላጅ አባቷ የገለጹት፡፡
በሚቀጠለው ቀን ታዳጊዋ ከአክስቷ ጋር በመሆን ክስ ለመመስረት ወደ ፖሊስ ጣቢያ የሄደች ቢሆንም፤ በፖሊስ ጣቢያው ኃላፊ እንደተደፈረች ኤን-ዲቲ-ቪ የተባለ የህንድ ቻናል ዘግቧል፡፡
ዜናውን ተከትሎ በግዛቱ ያሉትን ህጎች ጥያቄ ውስጥ መግባታቸው በመነገር ላይ ያለው፡፡
የህንድ ኮንግረስ ፓርቲ ከፍተኛ አመራር የሆኑት ፕሪያንካ ጋንዲ በትዊተር ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሁፍ ‘‘ ፖሊስ ጣቢያዎች ለሴቶች ደህንነት አስተማማኝ ካልሆኑ ፤ ሴቶች ታዲያ የት ሄደው ይከሳሉ? ’’ የሚል ትችት አዘል መልእክት አጋርቷል፡፡
ምንጭ፦ አል ዓይን ኒውስ /ND TV
@tikvahethiopia
#እንድታውቁት
ነገ ሚያዚያ 27/2014 ዓ.ም የሚከበረውን የኢትዮጵያ አርበኞች ቀን በዓልን በማስመልከት ከንጋቱ 12:00 ሰዓት 21 ጊዜ መድፍ የሚተኮስ መሆኑን መከላከያ ሚኒስቴር አስታውቋል።
@tikvahethiopia
ነገ ሚያዚያ 27/2014 ዓ.ም የሚከበረውን የኢትዮጵያ አርበኞች ቀን በዓልን በማስመልከት ከንጋቱ 12:00 ሰዓት 21 ጊዜ መድፍ የሚተኮስ መሆኑን መከላከያ ሚኒስቴር አስታውቋል።
@tikvahethiopia
ፎቶ፦ 81ኛው የድል በዓል 4 ኪሎ በሚገኘው የድል ሐውልት አባት አርበኞች፣ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች፣ ወጣቶች፣ ታዳጊዎች፣ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች እንዲሁም የተለያዩ አገራት አምባሳደሮች በተገኙበት ተከብሯል።
@tikvahethiopia
@tikvahethiopia
#Ethiopia #Djibouti
በጅቡቲ ከሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ እንደተገኘው መረጃ ኢትዮጵያ እና ጂቡቲ የነዳጅ ማከማቻ ተርሚናል በጋራ ለማልማት የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርመዋል።
የነዳጅ ማከማቻው በጂቡቲ ነጻ ወደቦች ቀጠና የሚካሄድ ነው።
የመግባቢያ ስምምነቱ ሃገራቱ ወደፊት በዘርፉ ለሚያካሂዱት ልማት ምቹ ሁኔታን ለመፍጠርና ተጨማሪ እድሎችን ለማየት የሚያስችል ነው ተብሏል።
ምንጭ፦ በጅቡቲ የኢትዮጵያ ኤምባሲ
@tikvahethiopia
በጅቡቲ ከሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ እንደተገኘው መረጃ ኢትዮጵያ እና ጂቡቲ የነዳጅ ማከማቻ ተርሚናል በጋራ ለማልማት የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርመዋል።
የነዳጅ ማከማቻው በጂቡቲ ነጻ ወደቦች ቀጠና የሚካሄድ ነው።
የመግባቢያ ስምምነቱ ሃገራቱ ወደፊት በዘርፉ ለሚያካሂዱት ልማት ምቹ ሁኔታን ለመፍጠርና ተጨማሪ እድሎችን ለማየት የሚያስችል ነው ተብሏል።
ምንጭ፦ በጅቡቲ የኢትዮጵያ ኤምባሲ
@tikvahethiopia
#ጥንቃቄ
የአሳማ መኖን ከሌሎች በዓድ ነገሮች ጋር በመቀላቀል የምግብ ዘይት ሲያመርቱ የተገኙ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ዋሉ፡፡
ግለሰቦቹ በቁጥጥር ስር የዋሉት የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣን የሰሜን ምዕራብ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ከአማራ ጤና ቢሮ እና ከደቡብ ጎንደር ዞን መስተዳደር ጋር በመሆን በማህበረሰቡ ጥቆማ መሰረት በተደረገው ክትትልና ፍተሻ ነው።
ለምግብነት ሊውል የማይችል ህገ-ወጥ የዘይት ምርቱ የተያዘው በደቡብ ጎንደር ዞን በወረታ ከተማ ሲሆን በጥሬ ግብዓትነት የሚጠቀሙት የአሳማ መኖ፣ የዘይት ተረፈ ምርትን (ፋጉሎን)፣ ሱፍን እና ሌሎች ለጊዜው ምንነታቸው ያልተለዩ በማዳበሪያ ታስረው የተቀመጡ ነገሮችን በመቀላቀልና በማፍላት በሰው እግር በመርገጥ ህገ-ወጥ የዘይት ምርቱን እንደሚያመርቱ ታውቋል፡፡
የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣን የሰሜን ምዕራብ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሙሉጌታ ቆየ እንደገለጹት የምርቱ ናሙና ተወስዶ በላብራቶሪ የተመረመረና ሦሰቱም ፓራሜትር የወደቀና ከፍተኛ የአሲድ ክምችት በውሰጡ መገኘቱን አስታውቀዋል፡፡
አክለው ምርቱ በምንም መመዘኛ ለምግብነት ሊውል የማይችል፣ለተለያዩ በሸታዎች የሚያጋልጥ እንደሆነ ህዝባችን እንዲገነዘብልን እንፈልጋለን ሲሉ ገልፃዋል፡፡
ህገ-ወጥ ምርቱ ምንም አይነት የብቃት ማረጋገጫ ያልተሰጠውና ምርቱን ለህብረተሰቡ የሚያከፋፍሉት ሳይታሸግ፣ ምንም የምርት መለያ ሳይለጥፉ ከበርሜል በመቅዳት እንደሚያሰራጩ ተደርሶባቸዋል ብለዋል።
በሀገርቱ የተከሰተውን የምግብ ምርቶች ዋጋ መናርን ተከትሎ ጥራትና ደህንነታቸው ያልተጠበቁ ምርቶች የጤና ጉዳት እንዳያደርሱ ህብረተሰቡ በየአካባቢውና በግብይት ወቅት ተገቢው ጥንቃቄ እንዲያደርግ አስገንዝበዋል።
ጥቆማ መስጫ፦ 8482
ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣን
@tikvahethiopia
የአሳማ መኖን ከሌሎች በዓድ ነገሮች ጋር በመቀላቀል የምግብ ዘይት ሲያመርቱ የተገኙ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ዋሉ፡፡
ግለሰቦቹ በቁጥጥር ስር የዋሉት የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣን የሰሜን ምዕራብ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ከአማራ ጤና ቢሮ እና ከደቡብ ጎንደር ዞን መስተዳደር ጋር በመሆን በማህበረሰቡ ጥቆማ መሰረት በተደረገው ክትትልና ፍተሻ ነው።
ለምግብነት ሊውል የማይችል ህገ-ወጥ የዘይት ምርቱ የተያዘው በደቡብ ጎንደር ዞን በወረታ ከተማ ሲሆን በጥሬ ግብዓትነት የሚጠቀሙት የአሳማ መኖ፣ የዘይት ተረፈ ምርትን (ፋጉሎን)፣ ሱፍን እና ሌሎች ለጊዜው ምንነታቸው ያልተለዩ በማዳበሪያ ታስረው የተቀመጡ ነገሮችን በመቀላቀልና በማፍላት በሰው እግር በመርገጥ ህገ-ወጥ የዘይት ምርቱን እንደሚያመርቱ ታውቋል፡፡
የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣን የሰሜን ምዕራብ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሙሉጌታ ቆየ እንደገለጹት የምርቱ ናሙና ተወስዶ በላብራቶሪ የተመረመረና ሦሰቱም ፓራሜትር የወደቀና ከፍተኛ የአሲድ ክምችት በውሰጡ መገኘቱን አስታውቀዋል፡፡
አክለው ምርቱ በምንም መመዘኛ ለምግብነት ሊውል የማይችል፣ለተለያዩ በሸታዎች የሚያጋልጥ እንደሆነ ህዝባችን እንዲገነዘብልን እንፈልጋለን ሲሉ ገልፃዋል፡፡
ህገ-ወጥ ምርቱ ምንም አይነት የብቃት ማረጋገጫ ያልተሰጠውና ምርቱን ለህብረተሰቡ የሚያከፋፍሉት ሳይታሸግ፣ ምንም የምርት መለያ ሳይለጥፉ ከበርሜል በመቅዳት እንደሚያሰራጩ ተደርሶባቸዋል ብለዋል።
በሀገርቱ የተከሰተውን የምግብ ምርቶች ዋጋ መናርን ተከትሎ ጥራትና ደህንነታቸው ያልተጠበቁ ምርቶች የጤና ጉዳት እንዳያደርሱ ህብረተሰቡ በየአካባቢውና በግብይት ወቅት ተገቢው ጥንቃቄ እንዲያደርግ አስገንዝበዋል።
ጥቆማ መስጫ፦ 8482
ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣን
@tikvahethiopia
#አቢሲንያ_ባንክ
የባንካችን የስራ መግቢያ እና መውጫ ሰዓት ሳያሳስብዎት 24 ሰዓት ከ እሁድ እስከ እሁድ በመረጡት የቨርቹዋል ባንኪንግ አገልግሎት መስጫ ማዕከል በመገኘት ገንዘብዎን ተቀማጭ ወይም ወጪ ማድረግ ይችላሉ።
የአቢሲንያ ባንክን ትክክለኛ የቴሌግራም ቻነል ይቀላቀሉ! https://t.iss.one/BoAEth
የባንካችን የስራ መግቢያ እና መውጫ ሰዓት ሳያሳስብዎት 24 ሰዓት ከ እሁድ እስከ እሁድ በመረጡት የቨርቹዋል ባንኪንግ አገልግሎት መስጫ ማዕከል በመገኘት ገንዘብዎን ተቀማጭ ወይም ወጪ ማድረግ ይችላሉ።
የአቢሲንያ ባንክን ትክክለኛ የቴሌግራም ቻነል ይቀላቀሉ! https://t.iss.one/BoAEth
" በኬንያ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ኬንያ ውስጥ እንደአገራቸው በነፃነት እንዲኖሩ እፈልጋለሁ " - ኡሁሩ ኬንያታ
የኬንያ ፕሬዚዳንት የሆኑት ኡሁሩ ኬንያታ በኬንያ የኢፌዲሪ ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር መለስ ዓለምን በጽ/ቤታቸው ዛሬ ተቀብለው አነጋገሩ።
በዚህም ወቅት ፤ ፕሬዜዳንቱ " ኢትዮጵያ የኬንያ የቁርጥ ቀን ወዳጅ ናት " ያሉ ሲሆን " ኢትዮጵያ ችግር ባጋጠማት ጊዜ ሁሉ እንደዚህ ቀደሙ ሁሉ ከጎኗ እንደምንቆም እናረጋግጣለን " ብለዋል።
በሁለቱ ሀገራት መካከል በኢኮኖሚው መስክ በመሠረተ-ልማት ትስስር፣ ንግድ፣ ኢንቨስትመንት ዘርፎች የተጀመሩ ትብብሮች ተጠናከረው እንደሚቀጥሉ ፕሬዚዳንቱ ተናግረዋል።
ፕሬዚዳንቱ ኡሁሩ በኬንያ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ-ኢትዮጵያውያን ኬንያ ውስጥ እንደአገራቸው በነፃነት እንዲኖሩም እፈልጋለሁ ብለዋል።
https://telegra.ph/Ethiopia-Kenya-05-05
Via Ethiopian Embassy in Kenya
@tikvahethiopia
የኬንያ ፕሬዚዳንት የሆኑት ኡሁሩ ኬንያታ በኬንያ የኢፌዲሪ ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር መለስ ዓለምን በጽ/ቤታቸው ዛሬ ተቀብለው አነጋገሩ።
በዚህም ወቅት ፤ ፕሬዜዳንቱ " ኢትዮጵያ የኬንያ የቁርጥ ቀን ወዳጅ ናት " ያሉ ሲሆን " ኢትዮጵያ ችግር ባጋጠማት ጊዜ ሁሉ እንደዚህ ቀደሙ ሁሉ ከጎኗ እንደምንቆም እናረጋግጣለን " ብለዋል።
በሁለቱ ሀገራት መካከል በኢኮኖሚው መስክ በመሠረተ-ልማት ትስስር፣ ንግድ፣ ኢንቨስትመንት ዘርፎች የተጀመሩ ትብብሮች ተጠናከረው እንደሚቀጥሉ ፕሬዚዳንቱ ተናግረዋል።
ፕሬዚዳንቱ ኡሁሩ በኬንያ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ-ኢትዮጵያውያን ኬንያ ውስጥ እንደአገራቸው በነፃነት እንዲኖሩም እፈልጋለሁ ብለዋል።
https://telegra.ph/Ethiopia-Kenya-05-05
Via Ethiopian Embassy in Kenya
@tikvahethiopia