TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.2K photos
1.5K videos
211 files
4.1K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ኬላ

የጉምሩክ ኬላ ካልሆነ በስተቀር አሁንም ገመድ አስሮ መኪና የሚያስቆሙ ህገ ወጥ ናቸው ተብሏል።

ከትላንት በስቲያ የንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ሚኒስትር ለህ/ተ/ም/ቤት የሚኒስቴሩን የ8 ወራት እቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ባቀረበበት ወቅት አንድ ጥያቄ ተጠይቆ ነበር።

ይኸውም በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ወቅት የተከፈቱት የቁጥጥር ኬላዎች አሁንም አዋጅ ከተነሳ በኃላ ገመድ በመዘርጋት እያስቆሙ የትራንስፖርት ሁኔታውን እያጓተቱ ነው በእዚህ ላይ ምን እየተሰራ ነው ? የሚል ነበር።

ይህንን በተመለከተ የንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ሚኒስትር አቶ ገ/መስቀል ጫላ የጉምሩክ ኬላ ካልሆነ በስተቀር አሁንም ገመድ አስሮ መኪና የሚያስቆሙ ህገ ወጥ ናቸው ብለዋል።

አቶ ገ/መስቀል ጫላ ፦

" ከስምንት ወራት በኃላ በሁሉም ክልሎች በሚባልበት ደረጃ ጉሙሩክ የሚያውቃቸው ኬላዎች ካልሆኑ በስተቀር ኬላዎች እንዲነሱ ተደርጓል።

የጉሙሩክ ኬላ ካልሆነ በስተቀር አሁንም ኬላ ገመድ አስሮ መኪና የሚያስቆሙ ካሉ ህገወጥ ናቸው። ይሄ በግልፅ መታወቅ አለበት። ህገወጥ ናቸው ግን እኛ ባለን መረጃ አብዛኛዎቹ ክልሎች ይሄንን ኬላ አንስተው የጉሙሩክ ኬላዎች ብቻ ገቢ እና ወጪ እቃዎችን የሚቆጣጠሩበት ሁኔታ አለ " ሲሉ ተናግረዋል።

@tikvahethiopia