TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.8K photos
1.61K videos
216 files
4.36K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ሀዋሳ~የሲዳማ ሪፈረንደም ሰልፍ🔝

ከነገ በስቲያ/ሀሙስ የካቲት 14/2011 ዓ.ም. የሲዳማ ሪፈረንደም ሰልፍ አስተባባሪ ኮሚቴ በሀዋሳ ከተማ የጠራው #ሰላማዊ_ሰልፍ በመንግስት ፍቃድ አግኝቷል።

ሰልፉ ህዝበ ውሳኔ #ተግባራዊ እንዲሆን የሚጠይቅ ሲሆን በሰልፉ ላይ ከሲዳማ የተለያዩ ወረዳዎች የተውጣጡ #ተሳታፊዎች ይካፈሉበታል ተብሏል። የሰልፉ ተሳታፊዎችም ህገ መንግስታዊ መብታቸው እንዲከበር ድምፃቸውን ያሰማሉ ተብሎ ይጠበቃል።

ሰላማዊ ሰልፉ የሚደረግበት ሰዓት፦
ከጥዋት 1 ሰዓት እስከ ቀን 6 ሰዓት

ሰላማዊ ሰልፉ የሚያካልላቸው የከተማይቱ ቦታዎች፦

•መነሻው፦ ሀዋሳ ቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ
•ሲዳማ ዞን አስተዳደር
•አሮጌው መናኸሪያ
•ተስፋዬ ግዛው ህንፃ
•መሳይ ሆቴል
•ማሳረጊያ፦ ሀዋሳ ዓለም አቀፍ ስታዲየም

ጥንቃቄ እና ማሳሰቢያ‼️

ሰላማዊ ሰልፉ ቤተክርስቲያናት፣ መስጊዶች፣ የፀሎት ቦታዎች፣ ሆስፒታሎች፣ መካነ መቃብሮች፣ የኤሌክትሪክ ማመንጫዎች የመሳሰሉት በሚገኙባቸው ቦታዎች 100 ሜትር ርቀት ውስጥ ሊደረግ የማይችል መሆኑን ከግምት ውስጥ በማስገባት የሰልፉ አስተባባሪዎች ተገቢውን ጥንቃቄ እና ቅድመ ዝግጅት እንዲያደርጉ ማሳሰቢያ ተሰጥቷል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia