TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.3K photos
1.51K videos
212 files
4.11K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#ICRC #Tigray የዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚቴ (ICRC) በተለያዩ ክልሎች በግጭት ለተጎዱ ወገኖች ድጋፍ ማድረጉን ቀጥሏል። ኮሚቴው #በትግራይ_ክልል በግጭት የተጎዱ አርሶ አደሮችን ምርታማነት ለማሳደግ ፦ 👉 በማዕከላዊ፣ 👉 በምስራቅ ፣ 👉 በደቡብ ምስራቅ እና በደቡብ ዞኖች ለሚገኙ ለ20,000 አባውራዎች (120,000 ግለሰቦች) የአፈር ማዳበሪያ በማከፋፈል ላይ እንደሚገኝ ዛሬ አሳውቋል።…
#ICRC

ICRC ለተፈናቃይ አባወራዎች የገንዘብ ድጋፍ አደረገ።

የዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚቴ ፤ በኢትዮጵያ ውስጥ በግጭት የተፈናቀሉ አብዛኛዎቹ ሰዎች በሕይወት ለመቆየት በሰብአዊ እርዳታ ላይ ጥገኛ መሆናቸውን አመልክቷል።

በመጠለያ ካምፖች ውስጥ ያሉ ተፈናቃይ ሰዎች ደግሞ ምንም አይነት አስተማማኝ የኢኮኖሚ ምንጭ የላቸውም ሲል ገልጿል።

በዚህም ምክንያት በአማራ ክልል ፦ ሰሜን ወሎ ዞን፣ ሃብሩ ወረዳ፣ ጃራ የተፈናቃዮች መጠለያ ካምፕ ለሚገኙ 3,674 #ተፈናቃይ_አባወራዎች (22,044 ግለሰቦች) መሰረታዊ ፍላጎቶችን ለማሟላት የሚያግዝ የገንዘብ ድጋፍ ማድረጉን አሳውቋል።

@tikvahethiopia