" ... ሁሉም ወገን ቀውስን ከሚያባብስ ድርጊት ታቅቦ ግጭቱን ለመፍታት ሁልንተናዊ የሰላም መንገዶችን ሊጠቀም ይገባል " - ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ
የኢትዮጵያ 🇪🇹 ጠ/ሚ ዶክተር ዐቢይ አህመድ በዩክሬን ቀውስ ውስጥ ሁሉም ወገኖች ግጭትን ከሚያባብሱ ድርጊቶች እንዲቆጠቡ ጠየቁ።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ዩክሬን ውስጥ የተፈጠረውን ቀውስ በተመለከተ ዛሬ ባስተላለፉት መልዕክት " ኢትዮጵያ በቅርቡ ካለፈችበት ጦርነት ተነስታ ስለ ጦርነት ጉዳት የምታካፍለው ሰፊ ልምድ አላት " ብለዋል።
ዶ/ር ዐቢይ ፥ " የኢትዮጵያ ልምድ ጦርነት ቤተሰብን ፣ ማህበረሰብ ብሎም የሀገርን ኢኮኖሚን ክፉኛ የሚጎዳ፣ አጥፊ ነው " ሲሉ ገልፀዋል።
ጦርነት የሚያደርሰውን ቁሳዊ ጉዳት መጠገን ቢቻልም በማህበረሰብ ላይ ጥሎት የሚያልፈውን ጠባሳ ግን ለማከም ከባድ መሆኑን አመልክተዋል።
ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ፥ " ኢትዮጵያ #የዩክሬን ወቅታዊ ቀውስ በቅርበት እየተከታተለች ነው " ያሉ ሲሆን ግጭቱን የሚያባብሱ ሁኔታዎች እንደሚያሳስባት ገልፀዋል።
ሁሉም ወገኖች ቀውስን ከሚያባብስ ድርጊት ታቅበው ግጭቱን ለመፍታት ሁልንተናዊ የሰላም መንገዶችን እንዲጠቀሙ ጠይቀዋል።
በአካባቢው ላይ #ሰላም እንዲሰፍን ያላቸውን ምኞት መግለፃቸውን ኤፍ ቢ ሲ ዘግቧል።
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ 🇪🇹 ጠ/ሚ ዶክተር ዐቢይ አህመድ በዩክሬን ቀውስ ውስጥ ሁሉም ወገኖች ግጭትን ከሚያባብሱ ድርጊቶች እንዲቆጠቡ ጠየቁ።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ዩክሬን ውስጥ የተፈጠረውን ቀውስ በተመለከተ ዛሬ ባስተላለፉት መልዕክት " ኢትዮጵያ በቅርቡ ካለፈችበት ጦርነት ተነስታ ስለ ጦርነት ጉዳት የምታካፍለው ሰፊ ልምድ አላት " ብለዋል።
ዶ/ር ዐቢይ ፥ " የኢትዮጵያ ልምድ ጦርነት ቤተሰብን ፣ ማህበረሰብ ብሎም የሀገርን ኢኮኖሚን ክፉኛ የሚጎዳ፣ አጥፊ ነው " ሲሉ ገልፀዋል።
ጦርነት የሚያደርሰውን ቁሳዊ ጉዳት መጠገን ቢቻልም በማህበረሰብ ላይ ጥሎት የሚያልፈውን ጠባሳ ግን ለማከም ከባድ መሆኑን አመልክተዋል።
ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ፥ " ኢትዮጵያ #የዩክሬን ወቅታዊ ቀውስ በቅርበት እየተከታተለች ነው " ያሉ ሲሆን ግጭቱን የሚያባብሱ ሁኔታዎች እንደሚያሳስባት ገልፀዋል።
ሁሉም ወገኖች ቀውስን ከሚያባብስ ድርጊት ታቅበው ግጭቱን ለመፍታት ሁልንተናዊ የሰላም መንገዶችን እንዲጠቀሙ ጠይቀዋል።
በአካባቢው ላይ #ሰላም እንዲሰፍን ያላቸውን ምኞት መግለፃቸውን ኤፍ ቢ ሲ ዘግቧል።
@tikvahethiopia