#AnbesaCityBus
አንበሳ የከተማ አውቶብስ እስከ ለሊቱ 6 ሰዓት አገልግሎት ለመስጠት እየተዘጋጀ እንደሚገኝ አስታወቀ።
ድርጅቱ እስከ የለሊት አገልግሎትን ለመስጠት ተገልጋዮች የሚበዙባቸውን የአዲስ አበባ አካባቢዎች የመለየት ስራ እያከናወነ ሲሆን ጥናቱ ሲጠባቀቅ እስከ ምሽት 3 ሰዓት አገልግሎት የሚሰጡት አውቶብሶች እስከ ለሊት 6 ሰዓት ወደ ስራ እንደሚያስገባ ገልጿል።
የድርጅቱ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ምስክር ማንደፍሮ፥ " አሁን እስከ 3 ሰዓት ብቻ ነው አገልግሎት የሚሰጡት ከዚህ በኃላ በምንጀምረው አዲስ አገልግሎት እስከ ለሊት አጋማሽ ድረስ አገልግሎት እንዲሰጡ የትኞቹ መስመሮች ለእንደዚህ አይነት ስራ ተጋላጭ ናቸው / የትኞቹ መስመሮች አምሽተው የሚሰሩ በዛ በምናስበው ሰዓት ከስራቸው የሚወጡ ማህበረሰቦች አሉ የሚለውን ጥናት እያደረግን ነው፤ ጥናቱን ከጨረስን በኃላ የተወሰኑ እንደ ዲሞንስትሬሽን የምንጀምረው አሰራር ይኖራል " ብለዋል።
አንበሳ የከተማ አውቶብስ አገልግሎት የቀኑን የትራንስፖርት እጥረት ለመፍታት የአዲስ አበባ አስተዳደር ይገዛቸዋል የተባሉትን 3 ሺህ አውቶብሶች እየጠበቀ እንደሚገኝ እና አውቶብሶቹን እንደተረከበ በመጠሉ ችግሩን ለማቃለል እንሞክራለን ሲል አሳውቋል።
አሁን ላይ አምበሳ የከተማ አውቶብስ አገልግሎት ድርጅት 630 አውቶብሶች ያሉት ሲሆን በ125 መስመሮች በቀን ውስጥ እስከ 600 ሺ ያህል ሰዎችን እንደሚያጓጉዝ ገልጿል።
ምንጭ፦ ሸገር ኤፍ ኤም 102.1
@tikvahethiopia
አንበሳ የከተማ አውቶብስ እስከ ለሊቱ 6 ሰዓት አገልግሎት ለመስጠት እየተዘጋጀ እንደሚገኝ አስታወቀ።
ድርጅቱ እስከ የለሊት አገልግሎትን ለመስጠት ተገልጋዮች የሚበዙባቸውን የአዲስ አበባ አካባቢዎች የመለየት ስራ እያከናወነ ሲሆን ጥናቱ ሲጠባቀቅ እስከ ምሽት 3 ሰዓት አገልግሎት የሚሰጡት አውቶብሶች እስከ ለሊት 6 ሰዓት ወደ ስራ እንደሚያስገባ ገልጿል።
የድርጅቱ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ምስክር ማንደፍሮ፥ " አሁን እስከ 3 ሰዓት ብቻ ነው አገልግሎት የሚሰጡት ከዚህ በኃላ በምንጀምረው አዲስ አገልግሎት እስከ ለሊት አጋማሽ ድረስ አገልግሎት እንዲሰጡ የትኞቹ መስመሮች ለእንደዚህ አይነት ስራ ተጋላጭ ናቸው / የትኞቹ መስመሮች አምሽተው የሚሰሩ በዛ በምናስበው ሰዓት ከስራቸው የሚወጡ ማህበረሰቦች አሉ የሚለውን ጥናት እያደረግን ነው፤ ጥናቱን ከጨረስን በኃላ የተወሰኑ እንደ ዲሞንስትሬሽን የምንጀምረው አሰራር ይኖራል " ብለዋል።
አንበሳ የከተማ አውቶብስ አገልግሎት የቀኑን የትራንስፖርት እጥረት ለመፍታት የአዲስ አበባ አስተዳደር ይገዛቸዋል የተባሉትን 3 ሺህ አውቶብሶች እየጠበቀ እንደሚገኝ እና አውቶብሶቹን እንደተረከበ በመጠሉ ችግሩን ለማቃለል እንሞክራለን ሲል አሳውቋል።
አሁን ላይ አምበሳ የከተማ አውቶብስ አገልግሎት ድርጅት 630 አውቶብሶች ያሉት ሲሆን በ125 መስመሮች በቀን ውስጥ እስከ 600 ሺ ያህል ሰዎችን እንደሚያጓጉዝ ገልጿል።
ምንጭ፦ ሸገር ኤፍ ኤም 102.1
@tikvahethiopia