TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.1K photos
1.5K videos
211 files
4.09K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#AnbesaCityBus

አንበሳ የከተማ አውቶብስ እስከ ለሊቱ 6 ሰዓት አገልግሎት ለመስጠት እየተዘጋጀ እንደሚገኝ አስታወቀ።

ድርጅቱ እስከ የለሊት አገልግሎትን ለመስጠት ተገልጋዮች የሚበዙባቸውን የአዲስ አበባ አካባቢዎች የመለየት ስራ እያከናወነ ሲሆን ጥናቱ ሲጠባቀቅ እስከ ምሽት 3 ሰዓት አገልግሎት የሚሰጡት አውቶብሶች እስከ ለሊት 6 ሰዓት ወደ ስራ እንደሚያስገባ ገልጿል።

የድርጅቱ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ምስክር ማንደፍሮ፥ " አሁን እስከ 3 ሰዓት ብቻ ነው አገልግሎት የሚሰጡት ከዚህ በኃላ በምንጀምረው አዲስ አገልግሎት እስከ ለሊት አጋማሽ ድረስ አገልግሎት እንዲሰጡ የትኞቹ መስመሮች ለእንደዚህ አይነት ስራ ተጋላጭ ናቸው / የትኞቹ መስመሮች አምሽተው የሚሰሩ በዛ በምናስበው ሰዓት ከስራቸው የሚወጡ ማህበረሰቦች አሉ የሚለውን ጥናት እያደረግን ነው፤ ጥናቱን ከጨረስን በኃላ የተወሰኑ እንደ ዲሞንስትሬሽን የምንጀምረው አሰራር ይኖራል " ብለዋል።

አንበሳ የከተማ አውቶብስ አገልግሎት የቀኑን የትራንስፖርት እጥረት ለመፍታት የአዲስ አበባ አስተዳደር ይገዛቸዋል የተባሉትን 3 ሺህ አውቶብሶች እየጠበቀ እንደሚገኝ እና አውቶብሶቹን እንደተረከበ በመጠሉ ችግሩን ለማቃለል እንሞክራለን ሲል አሳውቋል።

አሁን ላይ አምበሳ የከተማ አውቶብስ አገልግሎት ድርጅት 630 አውቶብሶች ያሉት ሲሆን በ125 መስመሮች በቀን ውስጥ እስከ 600 ሺ ያህል ሰዎችን እንደሚያጓጉዝ ገልጿል።

ምንጭ፦ ሸገር ኤፍ ኤም 102.1

@tikvahethiopia