#ShabelleBank
የሸቤሌ ባንክ ምስረታ ስነ- ስርአት ተካሔደ።
የሸቤሌ ባንክ መመስረቻ ስነ ስርአት ዛሬ በጅግጅጋ ከተማ ተካሒዷል።
በ2011 የሶማሊ ማይክሮ ፋይናንስ ተቋም " ሄሎው ካሽ " በሚል የገንዘብ ግብይትና ዝውውር አገልግሎት መስጠት የጀመረው ተቋሙ ለመቶ ሺህ ለሚሆኑ የአካባቢው ዜጎች የስራ ዕድል ፈጥሮ እያገለገለ ይገኛል።
በማይክሮ ፋይናንስነት አገልግሎቱ እስከ አሁን 1 ሚሊየን 3 መቶ ሺህ በላይ የሚደርሱ ደንበኞችን እንዳሉት ይገለፃል።
ተቋሙ በእስከ አሁን ሒደቱ በ43 የተለያዩ የአገልግሎት ማዕከላት ሲኖረው 500 ቋሚ ሰራተኞችን ይዞ በ 3.7 ቢሊየን የኢትዮጵያ ብር ጠቅላላ የሐብት መጠን በማስመዝገብ በ2013 አመተ ምህረት ከብሔራዊ ባንክ ባገኘው እውቅና ወደ እስላሚክ ሸቤሌ ባንክነት ማደግ ችሏል።
በዛሬው የባንክ በምስረታ የሐገር ሽማግሌዎች ፣ የሶማሊ ክልል ፕሬዝዳንት አቶ ሙስጠፌ ሙሁመድ ፣ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኢብራሂም ኡስማን ፣ አምባሳደር ዶ/ር መሐሙድ ድሪር ፣ የባንኩ የቦርድ ሰብሳቢ አቶ ሐሰን መሐመድ፣ የተለያዪ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
#SRTV
@tikvahethiopia
የሸቤሌ ባንክ ምስረታ ስነ- ስርአት ተካሔደ።
የሸቤሌ ባንክ መመስረቻ ስነ ስርአት ዛሬ በጅግጅጋ ከተማ ተካሒዷል።
በ2011 የሶማሊ ማይክሮ ፋይናንስ ተቋም " ሄሎው ካሽ " በሚል የገንዘብ ግብይትና ዝውውር አገልግሎት መስጠት የጀመረው ተቋሙ ለመቶ ሺህ ለሚሆኑ የአካባቢው ዜጎች የስራ ዕድል ፈጥሮ እያገለገለ ይገኛል።
በማይክሮ ፋይናንስነት አገልግሎቱ እስከ አሁን 1 ሚሊየን 3 መቶ ሺህ በላይ የሚደርሱ ደንበኞችን እንዳሉት ይገለፃል።
ተቋሙ በእስከ አሁን ሒደቱ በ43 የተለያዩ የአገልግሎት ማዕከላት ሲኖረው 500 ቋሚ ሰራተኞችን ይዞ በ 3.7 ቢሊየን የኢትዮጵያ ብር ጠቅላላ የሐብት መጠን በማስመዝገብ በ2013 አመተ ምህረት ከብሔራዊ ባንክ ባገኘው እውቅና ወደ እስላሚክ ሸቤሌ ባንክነት ማደግ ችሏል።
በዛሬው የባንክ በምስረታ የሐገር ሽማግሌዎች ፣ የሶማሊ ክልል ፕሬዝዳንት አቶ ሙስጠፌ ሙሁመድ ፣ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኢብራሂም ኡስማን ፣ አምባሳደር ዶ/ር መሐሙድ ድሪር ፣ የባንኩ የቦርድ ሰብሳቢ አቶ ሐሰን መሐመድ፣ የተለያዪ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
#SRTV
@tikvahethiopia