TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.3K photos
1.51K videos
212 files
4.11K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#AtmafegedYilma

አንጋፋው ጋዜጠኛ እና ደራሲ አጥናፍሰገድ ይልማ ባደረባቸው ህመም በ86 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል።

በሚያዚያ 27/1929 ዓ.ም በቀድሞ አጠራር በአርሲ ጠቅላይ ግዛት ጢቾ ከተማ የተወለዱት ጋዜጠኛ እና ደራሲ አጥናፍሰገድ በ1950 በሀገር መከላከያ ሚኒስቴር የፅህፈት ኮርስ መምህር ሆነው ስራ መጀመራቸውን የህይወት ታሪካቸው ያስረዳል።

ጋዜጠኛ እና ደራሲ አጥናፍሰገድ ይልማ በዛሬይቱ ኢትዮጵያ እና በአዲስ ዘመን ጋዜጦች ከአንጋፋው ጋዜጠኛ ጳውሎስ ኞኞ ጋር በአዘጋጅነት የኢትዮጵያ ድምፅ ጋዜጣናና በመነን መፅሄት ላይም አገልግለዋል።

በደራሲነት የብደል ካሳ የተሰኘ ልብወለድ ፣ የአቤቶ ኢያሱ አነሳስ እና አወዳደቅ ፣ የህይወቴ ሚስጥር (የ50ኛ ዓመት የጋብቻ በዓላቸው ማስታወሻ) መፅሀፍትን አሳትመዋል።

ጋዜጠኛ እና ደራሲ አጥናፍሰገድ ይልማ በኢትዮጵያ ደራሲያን ማህበር በልዩ ልዩ ኮሚቴዎች ውስጥም አገልግለዋል።

ባለትዳር እና የ4 ወንዶች እና የአንዲት ሴት ልጅ አባት ነበሩ።

ስርዓተ ቀብራቸው ነገ 8 ሰዓት ሃያት በሚገኘው ሰአሊተ ምህረት ቤተክርስቲያን እንደሚፈፀም ሸገር ኤፍ ኤም ዘግቧል።

ፎቶ : የኢትዮጵያ ደራሲያን ማህበር

@tikvahethiopia